• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት “ጭንቅላቱ ደርቋል” – ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

September 9, 2020 05:39 am by Editor 1 Comment

ህወሓት የተሰኘው የበረሃ ወንበዴዎች ስብስብ ላለፉት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ እስኪደነቁር ድረስ ሕገመንግሥት መናድ እያለ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ሲያሸማቅቅ እንዳልኖረ ዛሬ ያንኑ ሕገመንግሥት በመጻረር በትግራይ ሕገወጥ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።

ትላንት ማታ በETV በተላለፈው ቃለ ምልልስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ በትግራይ የሚካሄደውን ሕገወጥ ምርጫ ከጨረቃ ቤት ሥራ ጋር እንደሚያመሳስሉት ገለጹ። ጠያቂው “በትግራይ ክልል የሚካሄደውን ክልላዊ ምርጫ እንዴት ይመለከቱታል?” ብሎ ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ላቀረበላቸው ጥያቄ “የትግራይን (የዛሬ) ምርጫ እንደ ጨረቃ ቤት ነው የምመለከተው፤ እዚያ ያለው ኃይል ጭንቅላቱ ደርቋል፤ ኪሱ ሲደርቅ ይጠፋል። እኛ የትግራይ ሕዝብን በልማት እንደግፋለን እንጂ ጦር አናዘምተበትም” ብለዋል።

“የትግራይ ምርጫ የጨረቃ ምርጫ ነው! ኮሽ ባለ ቁጥር ይደነግጣሉ! ሲኖትራክ ሲያልፍ ዶዘር መጣ ሊያፈርሰን ነው ብለው ይፈራሉ ሕጋዊ ምርጫ አይደለም።

“የሚሊሻ ብዛት አሳሳቢ አይደለም አሁን ትግራይ የሚያስፈልጋት ጦርነት ሳይሆን ውሃ ነው፣ የህወሓት የቁራ ጩኸት አሳሳቢ አይደለም፣ እኔ ለትግራይ የፊት ማስክ እንጂ ጥይት አልክም” ብለዋል።

ሲቀጥሉም “የጨረቃ ቤት ካርታ አንደሌለው ሁሉ ይሄም ምርጫ ሕጋዊ ያልሆነ ምርጫ ቦርድ የማያውቀው ነው”። … አገራዊው ምርጫ ሲካሂድ እዚያ ያለው ቡድን ካልተሳተፈ ፓርላማ መቀመጫ አይኖረውም። ለዚህ ብለን ጦርነት አንከፍተም። ለትግራይ ሕዝብ ኮሮናን አንዲከላከል አፍ መሸፈኛን እንሰጣለን አንጂ፣ ውሃን እናስገባለን፣ እድገትን እናመጣለን እንጂ የሆኑ ቡድኖችን ለመዋጋት ጦርነት አንከፍትም ። እዛ ያለው ሀይል ጭንቅላቱ ደርቋል። ኪሱ ሲደርቅ ይጠፋል። በድሮ በሞተ ሀሳብ የሚንቀሳቀስ ነው” ብለዋል።

ሙሉው ቃለ ምልልስ እዚህ ላይ ይገኛል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, News, Right Column Tagged With: tigray tplf election, tplf, tplf fake election

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 10, 2020 02:15 pm at 2:15 pm

    አይ ምርጫ። አሁን ማን ይሙት በትግራይ ከወያኔ ውጭ ሰው መርጦ ቆሞ ይሄዳል? እንኳን አሁን አሰራራቸው ስር ሰዶ ይቅርና ድሮም በረሃ እያሉ ደንበር ገተር ሲሉ ፍትሃዊ ምርጫ ጭራሽ አድርገው አያውቁም። ሰው እንዴት ልብ ማለት አይችልም። ለትግራይ ህዝብ የሚያስቡ፤ ለኢትዮጵያ አንድነት የቆሙ የትግራይ ልጆች እኮ በደርግ ጥይት ሳይሆን በወያኔ ሴራ ነው አፈር የተመለሰባቸው። ግን ሆድ አምላካቸው ለሆነ፤ እኔ ከኖርኩ ሌላው ገደል ይግባ ለሚሉ ጭፍን የፓለቲካና የዘር አምላኪዎች ወያኔ ሰማያዊ እይታ አለው። በእነርሱ መስፈረት ወያኔ ለትግራይ ህዝብ ሲል ራሱን ጦም አሳድሮ በረሃ ለበረሃ የተንከራተተ ነው። ይህ ሁሉ ውሸት ነው። የሞተው የድሃው ልጅ። ዛሬም ና ታጠቅ የሚባለው የደሃው ገበሬ ልጅ ነው። የእነርሱ ልጆችና ቤተሰቦች በቻይና በአውሮፓ በአሜሪካ በተዘረፈ ሃብት ተንደላቀው ይኖራሉ። በሃገር የቀሩትም በተዘረፈ ሃብትና ንብረት ዘምነው ይንደላቀቃሉ። የትግራይ ልጆች ደም ለወያኔ የመነገጃ ብልሃት ነው።
    እኔ የሚገርመኝ ግን ሰው በኮሮና ቫይረስ እየተፈተነ፤ የአዲስ አመት መለወጫ ቀን በራፍ ላይ ቆሞ ሰውን የግድ ውጡና ምረጡ እያሉ ማጎሳቆል ለትግራይ ህዝብ ማሰብ ነው? በጭራሽ። የአቶ ስብሃት ነጋ ፓለቲካ መግደልና ማሰር፤ ማስፈራራትና የቆመን ማፍረስ በመሆኑ ህዝባችን በአዲስ ዓመት ዋዜማ እንኳን እፎይ ብሎ ከቤተሰቡ ጋር ያለውን እንዳይቀምስ ወያኔ በምርጫ ሰበብ ያዋክበዋል። ራሱ ወያኔ ያረቀቀውን የህገ መንግሥት ደንብ የሚጥስ እንዲህ ያለ ዘንዶ በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ በቅሎ አያውቅም። ችግሩ እነርሱ የፈጠሩት የዘር ፓለቲካ ሃገሪቱን ከከፋ ደረጃ ላይ እያደረሳት መሆኑ ያሳዝናል። የአምልኮ ቤቶችን ዘግቶ፤ ቄሳውስትን ማሰር የጣሊያኑ ሞሶሎኒ ከሰራው ልዪነቱ ምንድን ነው? እንዴት ብለው ነው የትግራይ ልጆች ወያኔን የሚደግፉት? ተገደው/ፍርፋሪ ለቃሚ ሆነው/ወይስ እኔ ምን ቸገረኝ በሚሊ ግዴለሽነት? ግራ ያጋባል። አዲስ አበባ ላይ በትረ መንግስቱን ይዘው አራጊ ፈጣሪ በነበሩ ጊዜ ዞር ብለው ያላዪት የትግራይ ህዝብ አሁን ከስልጣን ሲሽቀነጠሩ አለንልህ ማለታቸው መደበቂያ ፍለጋ እንጂ ለትግራይ ህዝብ ደህንነት እና ሰላም ደንታ አይሰጣቸውም። የወያኔ ቋንቋ ትግርኛ አይደለም። ጦርነት እንጂ! ለመኖር እሳት ማንደድ፤ ክራር እየከረከሩና ቀረርቶ እያሰሙ መጡባቹሁ እያሉ የትግራይን ሰፊ ህዝብ ማዋከብ ነው። የትላንትም የፓለቲካ ታሪካቸው ይህ ነበር፤ አሁንም የሚጠቀሙበት የስልጣን መቆያ ብልሃታቸው ማምታት ነው። ጌታቸው ረዳ ከፓለቲከኞች ሁሉ ሙት ነው። የሚናገረውን እንኳን አያውቅም። ለመሆኑ ሰውና ሰውን በማናከስ እንዴት ሰላም ማምጣት ይቻላል? አሁን ማን ይሙት አቶ ኢሳያስ የትግራይን ህዝብ ሊያጠቁ ተነስተዋል? የውሸት ቱልቱላ ማለት ይሄ ነው። እኔ ሳየው የኤርትራው መሪ በዘመናቸው ማለቂያ ልብ ለመግዛት የከጀሉ፤ ጦርነትን የተጸየፉ ሆነው ነው የማያቸው። ግን ወያኔ ዛሬም የጦርነት ታምቡር እየመታ ለመሆኑ ወያኔ አፍቃሪ ድህረ ገጾችንና የወያኔን የቴሌቪዥንና የሬዲዪ ጣቢያዎችን ማዳመጥ በቂ ነው።
    ጠ/ሚ አብይ የወያኔን ተንኮል ጠንቅቆ ያውቀዋል። ያው ከወያኔ የፓለቲካ ጥምር ኮሮጆ አፈትልኮ የወጣ በመሆኑ። ግን ወያኔ ሰው ለመግደል፤ ሃገር ለማተራመስና ለመሸጥ ተኝቶ አያውቅም። ራሱ ባንዳ ሆኖ እያለ ተው ልብ ግዙ የትግራይ ህዝብ በእናንተ ተጨቆነ የሚሉ የትግራይና ሌሎች ኢትዮጵያዊያንና/ዊትን ድምጾችን ባንዳ እያለ የሚጠራ የማያፍር ወራዳ ድርጅት ነው። በእኔ እይታ ምንም አይነት ትንኮሳ ወያኔ ቢሞክርም ትግራይ ውስጥ ጦርነት አያስፈልግም። ራሱ ህዝቡ በጊዜው ሆ ብሎ በመነሳት አይቀጡ ቅጣት እንደሚሰጣቸው እርግጠኛ ነኝ። ያኔ ወያኔን አያርገኝ። ችሎ ችሎ የተነሳ ህዝብ የሚያቆመው ምንም ሃይል አይኖርም። መኖርና መሞቱ ልዪነት የለውምና! የወያኔ ምርጫ ፌዝ እንጂ ለትግራይ ህዝብና ለሃገራችን የሚያክለው ብጣቂ ነገር አይኖርም። ግን እኮ እንዴት ሰው ህይወቱን ሙሉ የፓለቲካ የፈጠራ ገድል እንደተጫወተ አለምን ይሰናበታል? የምችለው ሰጠኝ አለ ሸክም የጨነቅው። አታድርስ ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule