
ህወሓት የተሰኘው የበረሃ ወንበዴዎች ስብስብ ላለፉት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ እስኪደነቁር ድረስ ሕገመንግሥት መናድ እያለ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ ሲያሸማቅቅ እንዳልኖረ ዛሬ ያንኑ ሕገመንግሥት በመጻረር በትግራይ ሕገወጥ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል።
ትላንት ማታ በETV በተላለፈው ቃለ ምልልስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ በትግራይ የሚካሄደውን ሕገወጥ ምርጫ ከጨረቃ ቤት ሥራ ጋር እንደሚያመሳስሉት ገለጹ። ጠያቂው “በትግራይ ክልል የሚካሄደውን ክልላዊ ምርጫ እንዴት ይመለከቱታል?” ብሎ ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ላቀረበላቸው ጥያቄ “የትግራይን (የዛሬ) ምርጫ እንደ ጨረቃ ቤት ነው የምመለከተው፤ እዚያ ያለው ኃይል ጭንቅላቱ ደርቋል፤ ኪሱ ሲደርቅ ይጠፋል። እኛ የትግራይ ሕዝብን በልማት እንደግፋለን እንጂ ጦር አናዘምተበትም” ብለዋል።
“የትግራይ ምርጫ የጨረቃ ምርጫ ነው! ኮሽ ባለ ቁጥር ይደነግጣሉ! ሲኖትራክ ሲያልፍ ዶዘር መጣ ሊያፈርሰን ነው ብለው ይፈራሉ ሕጋዊ ምርጫ አይደለም።
“የሚሊሻ ብዛት አሳሳቢ አይደለም አሁን ትግራይ የሚያስፈልጋት ጦርነት ሳይሆን ውሃ ነው፣ የህወሓት የቁራ ጩኸት አሳሳቢ አይደለም፣ እኔ ለትግራይ የፊት ማስክ እንጂ ጥይት አልክም” ብለዋል።
ሲቀጥሉም “የጨረቃ ቤት ካርታ አንደሌለው ሁሉ ይሄም ምርጫ ሕጋዊ ያልሆነ ምርጫ ቦርድ የማያውቀው ነው”። … አገራዊው ምርጫ ሲካሂድ እዚያ ያለው ቡድን ካልተሳተፈ ፓርላማ መቀመጫ አይኖረውም። ለዚህ ብለን ጦርነት አንከፍተም። ለትግራይ ሕዝብ ኮሮናን አንዲከላከል አፍ መሸፈኛን እንሰጣለን አንጂ፣ ውሃን እናስገባለን፣ እድገትን እናመጣለን እንጂ የሆኑ ቡድኖችን ለመዋጋት ጦርነት አንከፍትም ። እዛ ያለው ሀይል ጭንቅላቱ ደርቋል። ኪሱ ሲደርቅ ይጠፋል። በድሮ በሞተ ሀሳብ የሚንቀሳቀስ ነው” ብለዋል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
አይ ምርጫ። አሁን ማን ይሙት በትግራይ ከወያኔ ውጭ ሰው መርጦ ቆሞ ይሄዳል? እንኳን አሁን አሰራራቸው ስር ሰዶ ይቅርና ድሮም በረሃ እያሉ ደንበር ገተር ሲሉ ፍትሃዊ ምርጫ ጭራሽ አድርገው አያውቁም። ሰው እንዴት ልብ ማለት አይችልም። ለትግራይ ህዝብ የሚያስቡ፤ ለኢትዮጵያ አንድነት የቆሙ የትግራይ ልጆች እኮ በደርግ ጥይት ሳይሆን በወያኔ ሴራ ነው አፈር የተመለሰባቸው። ግን ሆድ አምላካቸው ለሆነ፤ እኔ ከኖርኩ ሌላው ገደል ይግባ ለሚሉ ጭፍን የፓለቲካና የዘር አምላኪዎች ወያኔ ሰማያዊ እይታ አለው። በእነርሱ መስፈረት ወያኔ ለትግራይ ህዝብ ሲል ራሱን ጦም አሳድሮ በረሃ ለበረሃ የተንከራተተ ነው። ይህ ሁሉ ውሸት ነው። የሞተው የድሃው ልጅ። ዛሬም ና ታጠቅ የሚባለው የደሃው ገበሬ ልጅ ነው። የእነርሱ ልጆችና ቤተሰቦች በቻይና በአውሮፓ በአሜሪካ በተዘረፈ ሃብት ተንደላቀው ይኖራሉ። በሃገር የቀሩትም በተዘረፈ ሃብትና ንብረት ዘምነው ይንደላቀቃሉ። የትግራይ ልጆች ደም ለወያኔ የመነገጃ ብልሃት ነው።
እኔ የሚገርመኝ ግን ሰው በኮሮና ቫይረስ እየተፈተነ፤ የአዲስ አመት መለወጫ ቀን በራፍ ላይ ቆሞ ሰውን የግድ ውጡና ምረጡ እያሉ ማጎሳቆል ለትግራይ ህዝብ ማሰብ ነው? በጭራሽ። የአቶ ስብሃት ነጋ ፓለቲካ መግደልና ማሰር፤ ማስፈራራትና የቆመን ማፍረስ በመሆኑ ህዝባችን በአዲስ ዓመት ዋዜማ እንኳን እፎይ ብሎ ከቤተሰቡ ጋር ያለውን እንዳይቀምስ ወያኔ በምርጫ ሰበብ ያዋክበዋል። ራሱ ወያኔ ያረቀቀውን የህገ መንግሥት ደንብ የሚጥስ እንዲህ ያለ ዘንዶ በኢትዮጵያ የፓለቲካ ታሪክ ውስጥ በቅሎ አያውቅም። ችግሩ እነርሱ የፈጠሩት የዘር ፓለቲካ ሃገሪቱን ከከፋ ደረጃ ላይ እያደረሳት መሆኑ ያሳዝናል። የአምልኮ ቤቶችን ዘግቶ፤ ቄሳውስትን ማሰር የጣሊያኑ ሞሶሎኒ ከሰራው ልዪነቱ ምንድን ነው? እንዴት ብለው ነው የትግራይ ልጆች ወያኔን የሚደግፉት? ተገደው/ፍርፋሪ ለቃሚ ሆነው/ወይስ እኔ ምን ቸገረኝ በሚሊ ግዴለሽነት? ግራ ያጋባል። አዲስ አበባ ላይ በትረ መንግስቱን ይዘው አራጊ ፈጣሪ በነበሩ ጊዜ ዞር ብለው ያላዪት የትግራይ ህዝብ አሁን ከስልጣን ሲሽቀነጠሩ አለንልህ ማለታቸው መደበቂያ ፍለጋ እንጂ ለትግራይ ህዝብ ደህንነት እና ሰላም ደንታ አይሰጣቸውም። የወያኔ ቋንቋ ትግርኛ አይደለም። ጦርነት እንጂ! ለመኖር እሳት ማንደድ፤ ክራር እየከረከሩና ቀረርቶ እያሰሙ መጡባቹሁ እያሉ የትግራይን ሰፊ ህዝብ ማዋከብ ነው። የትላንትም የፓለቲካ ታሪካቸው ይህ ነበር፤ አሁንም የሚጠቀሙበት የስልጣን መቆያ ብልሃታቸው ማምታት ነው። ጌታቸው ረዳ ከፓለቲከኞች ሁሉ ሙት ነው። የሚናገረውን እንኳን አያውቅም። ለመሆኑ ሰውና ሰውን በማናከስ እንዴት ሰላም ማምጣት ይቻላል? አሁን ማን ይሙት አቶ ኢሳያስ የትግራይን ህዝብ ሊያጠቁ ተነስተዋል? የውሸት ቱልቱላ ማለት ይሄ ነው። እኔ ሳየው የኤርትራው መሪ በዘመናቸው ማለቂያ ልብ ለመግዛት የከጀሉ፤ ጦርነትን የተጸየፉ ሆነው ነው የማያቸው። ግን ወያኔ ዛሬም የጦርነት ታምቡር እየመታ ለመሆኑ ወያኔ አፍቃሪ ድህረ ገጾችንና የወያኔን የቴሌቪዥንና የሬዲዪ ጣቢያዎችን ማዳመጥ በቂ ነው።
ጠ/ሚ አብይ የወያኔን ተንኮል ጠንቅቆ ያውቀዋል። ያው ከወያኔ የፓለቲካ ጥምር ኮሮጆ አፈትልኮ የወጣ በመሆኑ። ግን ወያኔ ሰው ለመግደል፤ ሃገር ለማተራመስና ለመሸጥ ተኝቶ አያውቅም። ራሱ ባንዳ ሆኖ እያለ ተው ልብ ግዙ የትግራይ ህዝብ በእናንተ ተጨቆነ የሚሉ የትግራይና ሌሎች ኢትዮጵያዊያንና/ዊትን ድምጾችን ባንዳ እያለ የሚጠራ የማያፍር ወራዳ ድርጅት ነው። በእኔ እይታ ምንም አይነት ትንኮሳ ወያኔ ቢሞክርም ትግራይ ውስጥ ጦርነት አያስፈልግም። ራሱ ህዝቡ በጊዜው ሆ ብሎ በመነሳት አይቀጡ ቅጣት እንደሚሰጣቸው እርግጠኛ ነኝ። ያኔ ወያኔን አያርገኝ። ችሎ ችሎ የተነሳ ህዝብ የሚያቆመው ምንም ሃይል አይኖርም። መኖርና መሞቱ ልዪነት የለውምና! የወያኔ ምርጫ ፌዝ እንጂ ለትግራይ ህዝብና ለሃገራችን የሚያክለው ብጣቂ ነገር አይኖርም። ግን እኮ እንዴት ሰው ህይወቱን ሙሉ የፓለቲካ የፈጠራ ገድል እንደተጫወተ አለምን ይሰናበታል? የምችለው ሰጠኝ አለ ሸክም የጨነቅው። አታድርስ ነው። በቃኝ!