• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የጥላቻው ምንጭ … ፖለቲከኞች፣ ብሔረተኞች፣ የጥላቻ ሰለባዎችና ጽንፈኞች የሚተፉት መርዝ ነው” ኦባንግ

August 9, 2020 01:35 am by Editor Leave a Comment

“በኦሮሚያ ክልል በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት  ከሰውነት፣ አብሮነትና ኢትዮጵያዊነት ይልቅ በሃሰተኛ ትርክትና በማንነት ጥላቻ ላይ ለበርካታ ዓመታት ሲሰራ የነበረ ስራ ውጤት ነው፤ ሊወገዝ የሚገባው የከፋ ድርጊት ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ ተናገሩ።

በኢትዮጵያዊነትና ሰብዓዊነት ላይ የሚሰሩ ድርጅችን በማቋቋም የሚንቀሳቀሱት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ አባንግ ሜቶ ከሰሞኑ በዝዋይና ሻሸመኔ ተዘዋውረው ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦች አነጋግረዋል።

ከጉብኝታቸው መልስ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታም ሰኔ 22 ሌሊት ጀምሮ በተፈጠረው ጥፋት የተጎዱ የ17 ግለሰቦችን ቃል መቀበላቸውን ተናግረዋል። በተፈጸመው ድርጊት የደረሰው ጉዳት ልብ የሚነካ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ይደረጋል ተብሎ የማይጠበቅ አሰቃቂ አገዳድል የተፈጸመበት አሳዛኝ ክስተት ነው ሲሉ ገልጸውታል።

የጉብኝታቸው ዓላማም ለሰብዓዊ መብት ድርጅቶች መሬት ላይ ያለ ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ብሎም ተጎጂዎች ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እንደነበር አውስተው፤ ድርጊቱ በተራ ግርግር የተፈጸመ እንዳልሆነ ማረጋገጣቸውን ገልፀጸዋል።

ከዚያ ይልቅ በአርቲስት ሃጫሉ ሰበብ ሆነ ተብሎ በተደራጀ አካል ስም ዝርዝር የወጣባቸው ሰዎች እየተመረጡ ግድያ እንደተፈጸመ ቤት ንብረታቸውም ከጎረቤት በተለየ ተመርጠው እንዲወድሙ መደረጉን ተናግረዋል።

በተለይም “ነፍጠኛ” በሚል ቃል የተለዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ ያነጣጠረ መሆኑን እንዳረጋገጡ ነው የተናገሩት። “ድርጊቱ የትናንት ውጤት ነው” ያሉት አቶ ኦባንግ፤ ትናንት ኢትዮጵያዊነት፣ አብሮነትና አንድነት ላይ ሳይሆን ‘ነፍጠኛ’ በሚል በአንድ ህዝብ ላይ ላይ ያነጣጠሩ ዘር ተኮር የጥላቻ ስራዎች ሲሰሩ እንደነበር አስታውሰዋል።

“በተለይም ህወሃት የሐሰት ታሪክ በመፍጠር፣ ሰዎች ከሰውነት ወጥተው ማንነታቸው ብሔር ብቻ እንዲሆን መደረጉ፣ እኔና እነሱ በሚል ክልል በመፍጠር እርስ በርስ የጥላቻ ስራዎች መሥራቱ ነው” ሲሉ ለአብነት አንስተዋል።

“የተዘራው ኢትዮጵያዊነት፣ ሕብረት፣ እኩልነት፣ ሰላም፣ መከባበር ሳይሆን ዘረኝነት፣ ጥላቻ፣ ቂም በቀልና የሃሰት ትርክት” እንደሆነ ገልጸዋው፤ የተዘራው መጥፎ ዘርም መጥፎ ፍሬ አፍርቷል” ብለዋል።

በተለያዩ ጊዜያት የተፈጠሩ አሰቃቂ ጥቃቶች በማስታወስም “ሰዎች ሰውነታቸውን እንዲረሱ፣ በትምህርት ስርዓቱም ጥላቻ ያነገቡ፣ የአገር ፍቅር የማያውቁ፣ ንቃተ ህሊና የሌላቸው ወጣቶች በማፍራት ለጥፋት መጠቀሚያ መሳሪያ ተደርገዋል” ሲሉም ያብራራሉ።

መንግስት በተለያዩ አካባቢዎች ከተከሰቱ ድርጊቶች ትምህርት ሊወስድ እንደሚገባ መክረው፤ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች ግጭት በሚል ሳይታለፉ፤ በጉዳዩ ላይ በግልጽ በመነጋገርምር ጥፋተኞችን ተጠያቂ ማድረግ ይገባል ይላሉ።

“ለሰው እንጂ ለብሔር አልወግንም” የሚሉት አቶ ኦባንግ ሰዎች በታዋቂነት ብቻ ሳይሆን በሰውነታቸው ሊከበሩ፣ ሲሞቱም እኩል እንዲታዘንና ክብር እንዲሰጥ፤ መላው ኢትዮጵያዊም ድርጊቱን በጋራ እንዲያወግዝ አሳስበዋል።

መንግሥት በሺዎች የሚቆጠሩ ተጠርጣሪዎች መያዙን ቢገልጽም፤ ጥፋቱ ተራ ግጭት ባለመሆኑ በማንና እንዴት እንደተፈጸመ ግልጽ መረጃ መስጠት አለበት ብለዋል። ይህ ካልሆነ ፍትህ ሊሰፍንም ሆነ የተጎጂዎች ህሊና ቁስል ሊሽር አይችልም ብለው ወደፊት ሌላ ተመሳሳይ ድርጊት ላለመፈጸሙ ዋስትና የለም ሲሉም በአጽንኦት ተናግረዋል።

ድርጊቱ መላውን የኦሮሞ ህዝብና የእስልምና እምነት ተከታዮችን እንደማይወክል ገልጸው፤ በጥፋቱ ወቅት ስም ዝርዝር ወጥቶ ሲፈለጉ የነበሩ ተጠቂዎችን ህይወት እየደበቁ ያተረፉ ጎረቤቶች እንደነበሩ ማረጋገጣቸውን ተናግረዋል።

“የጥላቻው ምንጭ ከታችኛው ህዝብ ሳይሆን ሥልጣን ላይ ለመውጣት በሚፈልጉ ፖለቲከኞች፣ ብሄርተኞች፣ የጥላቻ ሰለባዎችና ጽንፈኛ ቡድኖች የሚተፉት መርዝ ነው” ሲሉም አብራርተዋል።

ሰው ከመሆን ውጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለ የሚገልጹት አቶ ኦባንግ፣ በየትኛውም ቦታ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያወግዘው እንደሚገባ አብራርተዋል።

መንግሥት የችግሩን ምንጭ ከሥሩ በመረዳት “ሕገ መንግሥት ከማሻሻል ጀምሮ፣ በዘር ላይ የተመሰረተ ፖለቲካን ማከም፣ ተደራጅተው ሰዎችን የገደሉ አካላትም በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ተጠያቂ ማድረግ ይገባዋል” ሲሉም አሳስበዋል።

ለአንድ ህዝብ ተለይተው የሚሰጡ “ነፍጠኛ” የመሳሰሉ ቃላትም ሰዎችን ከሰውነታቸው የሚነጥሉና ለጥቃት የሚያጋልጡ መሆናቸውን በመግለጽ ሊወገዱ እንደሚገባ ነው አቶ ኦባንግ ሜቶ የተናገሩት ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule