
በዱሮ አስተሳሰብ እየኖሩ በአዲሱ ኃይል ጉልበት፤ ዕጣ ፋንታ፤ የወደፊት ራዕይ ላይ በመጫወት መስዋዕትነት የሚያስከፍሉት ፖለቲከኞች ጡረታ መውጣት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም ገለጹ።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የዓለም ፖለቲካ በጣም ተለዋዋጭ ነው። ትናንት የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ዛሬ አይሠራም፤ የለምም። በእኛ አገር ፖለቲካ ትናንት የሁልጊዜ ውሎ ነው። ገና ኃይለስላሴና ምኒልክ ዘመንን ያልተሻገረ ፖለቲከኛ ይዘን ቀጥለናል። ይህ ሁኔታ አገርን ስለማያሻግር እነዚህ ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል። በምትኩ የሚሠራ ኃይል ወንበሩን መረከብ አለበት።
እነዚህ አካላት በጊዜያቸው ወቅቱ የሚጠይቀውን መንገድ ሂደው ብዙ ሠርተዋል፤ ለአገርም ያበረከቱት ነገር አለ። ይሁንና “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አባባላቸው ዛሬም ቀጥሏል። ይህ ደግሞ ወጣቱን እንዳይሠራና አገሩን እነርሱ በሠሩት ላይ ጨምሮ እንዳያሻግር እንቅፋት ሆነውበታል ብለዋል። ሀገራዊ ፖለቲካውና ፖለቲከኛው እንዲሻሻል ከተፈለገ እነዚህ ዘመናቸው ያበቃ ፖለቲከኞች ለተተኪው ወንበር መለቀቅ እንደሚኖርባቸው አስታውቀዋል።
የቀድሞ ሀገራዊ የፖለቲካ አካሄድ መልካምም መጥፎም ታሪኮች እንደነበሩት የሚያነሱት አቶ ሙሳ፤ በዘመናቸው የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ይህንን እንዲያደርጉ አስገድዷቸዋልና አድርገውት አልፈዋል። አገርንም ለዛሬው ትውልድ ሠርተውለታል። ሆኖም ያንን ታሪክ አድርገን እንጂ ኑሯችን አድርገን መቀጠል የለብንም። ታሪኩ እንደ ታሪክነቱ ይነበብ፤ ይታወቅ፤ እውነታውን ሁሉም ይረዳው፤ ነገር ግን በዚያ ታሪክ እንድንኖር ሊፈረድብን አይገባም ብለዋል።
ትውልዱ ነገው እንዲበላሽ መፍቀድ የለበትም የሚሉት ሰብሳቢው፤ ዛሬ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። በዛሬው አካሄድ የዛሬው ትውልድ መሠራት አለበት። ነገን እያነሱ ትውልዱን ወደትናንት መውሰዱና ማበጣበጡ አገርን ወደኋላ ከመመለስ አይተናነስም። በተለይ ፖለቲከኛው የትናንቱን ለትናንት በመተው ዛሬ በራሱ መንገድ እንዲሻገር እና ለውጥ እንዲመጣ ለተተኪዎች ቦታውን መልቀቅ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።
አገሪቱ በርከት ያሉ በእውቀት መምራትና መሥራት የሚችሉ ወጣት ፖለቲከኞች አሏት፤ እነዚህን ወደ ሥራ ማስገባት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ የሚገልጹት አቶ ሙሳ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለፉት ዓመታትን የምንኖርበት ሊሆን አይገባምና ተሠርታ ያለቀችውን ኢትዮጵያን እንዲሠሩ ለትውልዱ እንፍቀድ ብለዋል።
የቀደሙት የትናንት ፖለቲከኞች ሌላ ሰው እንዲመጣባቸው አይፈልጉም፤ ወጣት ፖለቲከኛን ማየት ያማቸዋል ያሉት አቶ ሙሳ ፤ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ፖለቲከኛም ሆነ ፖለቲካው እንዳይፈጠር ከማድረጉም በላይ ወጣቱን የእሳት እራት እንጂ ባለተስፋ አላደረጉትም ብለዋል። የመሥራት ባህልን እንዲያዳብር እንዳልረዱትም አመልክተዋል።
እንደ አቶ ሙሳ ገለጻ፤ የተማረና የተመራመረ፤ የተሻለውን ለአገር ለማምጣት የሚጥር፤ ጉልበት ያለው ሯጭ ፖለቲከኛ አገር ያስፈልጋታል። እንደውም “የተማረ ይግደለኝ” እንደሚባለው የአገር ፖለቲካ መፈጠር የሚጀምረው ፖለቲከኛውም ፖለቲካውም በእውቀትና በአዲስ አስተሳሰብ ሲቃኝ ብቻ ነው። ስለሆነም የወቅቱን የፖለቲካ ጽንሰሃሳብ ያልተረዱ ሰዎች እየመሩ ግራ ከሚያጋቡ ጡረታ መውጣቱ ለነሱም ለሀገርም እንደሚበጅ ጠቁመዋል።
ፓርቲ የሚባለውም በዘመድ ተሰባስቦ የሚመሰረት ነው። ይህ ደግሞ አገር ለመምራት ሳይሆን ቤተሰብ ለማስተዳደር ብቻ የሚያስብ የሚያደርገው ተግባር ነው። እናም መሰረታዊ የፓርቲ ቁመና ያለው በሃሳብ ልዕልና የሚያምን ፓርቲ ከሌለ ፖለቲካም ፖለቲከኛም ሊፈጠር አይችልም።
ሁለቱም ያለመኖራቸው መንስኤ ነው አሁን ለአገር ፈተናና ዋጋ ማስከፈል ያበቃው ብለዋል። ፓርቲው እንደ ፓርቲ የሚሠራው ሥራ የለም። ህዝቡም ከፓርቲው የሚጠብቀውን እያገኘ አይደለም። ስለዚህም ህዝብ ከመጠቀም ይልቅ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ዓመታትን ዋጋ እየከፈለ እንዲኖር መደረጉንም አመልክተዋል።
ዘመኑን ያልዋጀ፤ አገርን ከፍ ለማድረግ በማያስችል ጉዳይ ላይ መስዋዕት እየከፈልን ነው የሚሉት አቶ ሙሳ፤ ትውልዱን በማደንቆር የተካኑ ፖለቲከኞች ጡረታ ይውጡና አዳዲስ የፖለቲካ አስተሳሰብና እውቀቱ ያላቸው አካላት ወንበሩን ይረከቡ ብለዋል።
ሀገራዊ የፖለቲካ አካሂዶች በመርህ፤ በፖሊሲ ላይ የተመሰረቱና ከአገርና ከህዝብ ጥቅም አንጻር የተቃኙ መሆን መቻልም አለባቸው። በዚህ ላይም በስፋት መሥራት መጀመር አለብን ሲሉም ነሐሴ 24፥ 2012 ለታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ተናግረዋል።
አቶ ሙሳ “ብሔሬን ውሰዱ ኢትዮጵያን ግን አትንኩ” በሚለው አስደማሚ ንግግራቸው ይታወቃሉ።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
አቶ ሙሳ ይህንን ዘመናዊ አስተሳብክን በነጠረ መልኩ በማስቀመጥህ አክበሮቴና አድናቆቴን እገልጽልሃሉ።አገሪቱ እኮ ወቅቱን በማይመጥን በታሪክ በለሙያተኞች ተጽፎ መቀመጥ ያለበትን ትሪክት እያነሱ ለዛሬው ችግራችን መፍትሄ የማይሆን ይልቁን አገራችንና ህዝቡን በክልል በዘር በጎሳ በቁዋንቀዋ እንዲሁም በሃይማኖት ከፋፍሎ እንዲፈጅ መርዛቸውን በውሰጥና በወጭ እየረጩ ያሉት እነዚህ የሥልጣን ጥማኞችና አዋቂ ከእኛ በላይ ለአሠር ብለወ በህዝቡ ጫንቃ ላይ የተጣበቁ ያረጁ ሰዎች ሊወገዱ ወይም ከመድረኩ ሊነሱ ይገባል።እነሱን ዘወትር በየመድረኩ የተጨመደደ ፊታቸውን ከማየትና ያረጀ ንግግራቸውን ከመስማት የበለጠ የሰለቸን ነገር የለምና።
It is good to think about the future. When we go forward should we need to forget what has been done yesterday. I don’t think so. When one group is always telling us the history of their kings and other we don’t share with them, how come Musa tells us to forget what these criminals done on our people and take them as our heroes unless these extremist accepts the crimes these kings did to us? Musa can accept and even he can change his ethnic background in favour of unity. But he can tell to others to deny their ethnic background and advocate unity without equality and national consensus.
ኣቶ ሙሳ የሚናገሩት፥ ሃቅን ያዘለ ነው።