• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኃይለሥላሴና ምኒልክ ዘመንን ያልተሻገ(ሩ)…ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል” አቶ ሙሳ

September 1, 2020 07:44 am by Editor 3 Comments


በዱሮ አስተሳሰብ እየኖሩ በአዲሱ ኃይል ጉልበት፤ ዕጣ ፋንታ፤ የወደፊት ራዕይ ላይ በመጫወት መስዋዕትነት የሚያስከፍሉት ፖለቲከኞች ጡረታ መውጣት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም ገለጹ።

የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የዓለም ፖለቲካ በጣም ተለዋዋጭ ነው። ትናንት የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ዛሬ አይሠራም፤ የለምም። በእኛ አገር ፖለቲካ ትናንት የሁልጊዜ ውሎ ነው። ገና ኃይለስላሴና ምኒልክ ዘመንን ያልተሻገረ ፖለቲከኛ ይዘን ቀጥለናል። ይህ ሁኔታ አገርን ስለማያሻግር እነዚህ ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል። በምትኩ የሚሠራ ኃይል ወንበሩን መረከብ አለበት።

እነዚህ አካላት በጊዜያቸው ወቅቱ የሚጠይቀውን መንገድ ሂደው ብዙ ሠርተዋል፤ ለአገርም ያበረከቱት ነገር አለ። ይሁንና “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አባባላቸው ዛሬም ቀጥሏል። ይህ ደግሞ ወጣቱን እንዳይሠራና አገሩን እነርሱ በሠሩት ላይ ጨምሮ እንዳያሻግር እንቅፋት ሆነውበታል ብለዋል። ሀገራዊ ፖለቲካውና ፖለቲከኛው እንዲሻሻል ከተፈለገ እነዚህ ዘመናቸው ያበቃ ፖለቲከኞች ለተተኪው ወንበር መለቀቅ እንደሚኖርባቸው አስታውቀዋል።

የቀድሞ ሀገራዊ የፖለቲካ አካሄድ መልካምም መጥፎም ታሪኮች እንደነበሩት የሚያነሱት አቶ ሙሳ፤ በዘመናቸው የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ይህንን እንዲያደርጉ አስገድዷቸዋልና አድርገውት አልፈዋል። አገርንም ለዛሬው ትውልድ ሠርተውለታል። ሆኖም ያንን ታሪክ አድርገን እንጂ ኑሯችን አድርገን መቀጠል የለብንም። ታሪኩ እንደ ታሪክነቱ ይነበብ፤ ይታወቅ፤ እውነታውን ሁሉም ይረዳው፤ ነገር ግን በዚያ ታሪክ እንድንኖር ሊፈረድብን አይገባም ብለዋል።

ትውልዱ ነገው እንዲበላሽ መፍቀድ የለበትም የሚሉት ሰብሳቢው፤ ዛሬ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። በዛሬው አካሄድ የዛሬው ትውልድ መሠራት አለበት። ነገን እያነሱ ትውልዱን ወደትናንት መውሰዱና ማበጣበጡ አገርን ወደኋላ ከመመለስ አይተናነስም። በተለይ ፖለቲከኛው የትናንቱን ለትናንት በመተው ዛሬ በራሱ መንገድ እንዲሻገር እና ለውጥ እንዲመጣ ለተተኪዎች ቦታውን መልቀቅ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።

አገሪቱ በርከት ያሉ በእውቀት መምራትና መሥራት የሚችሉ ወጣት ፖለቲከኞች አሏት፤ እነዚህን ወደ ሥራ ማስገባት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ የሚገልጹት አቶ ሙሳ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለፉት ዓመታትን የምንኖርበት ሊሆን አይገባምና ተሠርታ ያለቀችውን ኢትዮጵያን እንዲሠሩ ለትውልዱ እንፍቀድ ብለዋል።

የቀደሙት የትናንት ፖለቲከኞች ሌላ ሰው እንዲመጣባቸው አይፈልጉም፤ ወጣት ፖለቲከኛን ማየት ያማቸዋል ያሉት አቶ ሙሳ ፤ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ፖለቲከኛም ሆነ ፖለቲካው እንዳይፈጠር ከማድረጉም በላይ ወጣቱን የእሳት እራት እንጂ ባለተስፋ አላደረጉትም ብለዋል። የመሥራት ባህልን እንዲያዳብር እንዳልረዱትም አመልክተዋል።

እንደ አቶ ሙሳ ገለጻ፤ የተማረና የተመራመረ፤ የተሻለውን ለአገር ለማምጣት የሚጥር፤ ጉልበት ያለው ሯጭ ፖለቲከኛ አገር ያስፈልጋታል። እንደውም “የተማረ ይግደለኝ” እንደሚባለው የአገር ፖለቲካ መፈጠር የሚጀምረው ፖለቲከኛውም ፖለቲካውም በእውቀትና በአዲስ አስተሳሰብ ሲቃኝ ብቻ ነው። ስለሆነም የወቅቱን የፖለቲካ ጽንሰሃሳብ ያልተረዱ ሰዎች እየመሩ ግራ ከሚያጋቡ ጡረታ መውጣቱ ለነሱም ለሀገርም እንደሚበጅ ጠቁመዋል።

ፓርቲ የሚባለውም በዘመድ ተሰባስቦ የሚመሰረት ነው። ይህ ደግሞ አገር ለመምራት ሳይሆን ቤተሰብ ለማስተዳደር ብቻ የሚያስብ የሚያደርገው ተግባር ነው። እናም መሰረታዊ የፓርቲ ቁመና ያለው በሃሳብ ልዕልና የሚያምን ፓርቲ ከሌለ ፖለቲካም ፖለቲከኛም ሊፈጠር አይችልም።

ሁለቱም ያለመኖራቸው መንስኤ ነው አሁን ለአገር ፈተናና ዋጋ ማስከፈል ያበቃው ብለዋል። ፓርቲው እንደ ፓርቲ የሚሠራው ሥራ የለም። ህዝቡም ከፓርቲው የሚጠብቀውን እያገኘ አይደለም። ስለዚህም ህዝብ ከመጠቀም ይልቅ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ዓመታትን ዋጋ እየከፈለ እንዲኖር መደረጉንም አመልክተዋል።

ዘመኑን ያልዋጀ፤ አገርን ከፍ ለማድረግ በማያስችል ጉዳይ ላይ መስዋዕት እየከፈልን ነው የሚሉት አቶ ሙሳ፤ ትውልዱን በማደንቆር የተካኑ ፖለቲከኞች ጡረታ ይውጡና አዳዲስ የፖለቲካ አስተሳሰብና እውቀቱ ያላቸው አካላት ወንበሩን ይረከቡ ብለዋል።

ሀገራዊ የፖለቲካ አካሂዶች በመርህ፤ በፖሊሲ ላይ የተመሰረቱና ከአገርና ከህዝብ ጥቅም አንጻር የተቃኙ መሆን መቻልም አለባቸው። በዚህ ላይም በስፋት መሥራት መጀመር አለብን ሲሉም ነሐሴ 24፥ 2012 ለታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ተናግረዋል።

አቶ ሙሳ “ብሔሬን ውሰዱ ኢትዮጵያን ግን አትንኩ” በሚለው አስደማሚ ንግግራቸው ይታወቃሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Interviews, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yefa Bedane says

    September 2, 2020 02:30 am at 2:30 am

    አቶ ሙሳ ይህንን ዘመናዊ አስተሳብክን በነጠረ መልኩ በማስቀመጥህ አክበሮቴና አድናቆቴን እገልጽልሃሉ።አገሪቱ እኮ ወቅቱን በማይመጥን በታሪክ በለሙያተኞች ተጽፎ መቀመጥ ያለበትን ትሪክት እያነሱ ለዛሬው ችግራችን መፍትሄ የማይሆን ይልቁን አገራችንና ህዝቡን በክልል በዘር በጎሳ በቁዋንቀዋ እንዲሁም በሃይማኖት ከፋፍሎ እንዲፈጅ መርዛቸውን በውሰጥና በወጭ እየረጩ ያሉት እነዚህ የሥልጣን ጥማኞችና አዋቂ ከእኛ በላይ ለአሠር ብለወ በህዝቡ ጫንቃ ላይ የተጣበቁ ያረጁ ሰዎች ሊወገዱ ወይም ከመድረኩ ሊነሱ ይገባል።እነሱን ዘወትር በየመድረኩ የተጨመደደ ፊታቸውን ከማየትና ያረጀ ንግግራቸውን ከመስማት የበለጠ የሰለቸን ነገር የለምና።

    Reply
    • Iwunetu Yiwuta says

      September 3, 2020 08:45 pm at 8:45 pm

      It is good to think about the future. When we go forward should we need to forget what has been done yesterday. I don’t think so. When one group is always telling us the history of their kings and other we don’t share with them, how come Musa tells us to forget what these criminals done on our people and take them as our heroes unless these extremist accepts the crimes these kings did to us? Musa can accept and even he can change his ethnic background in favour of unity. But he can tell to others to deny their ethnic background and advocate unity without equality and national consensus.

      Reply
  2. Mulugeta Andargie says

    September 12, 2020 04:39 am at 4:39 am

    ኣቶ ሙሳ የሚናገሩት፥ ሃቅን ያዘለ ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ April 16, 2021 10:06 am
  • “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ April 16, 2021 08:45 am
  • “ተዋግተን አይደለም ስንተኛ ብንውል እንኳን መቀሌና አዲስ አበባ አይገቡም” ጄኔራል ባጫ April 14, 2021 09:06 am
  • የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ April 14, 2021 08:53 am
  • “ኤርትራዊ ነን” በማለት የመኖሪያ ፈቃድ ሲቀበሉ የኖሩ የትግራይ ሰዎችን መለየት ተጀመረ April 1, 2021 02:01 am
  • ምርጫ ቦርድ የኦነግን ጥያቄ ውድቅ አደረገ April 1, 2021 01:15 am
  • “እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ መንግሥት ኮሮጆ አይሰርቅም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ April 1, 2021 01:09 am
  • መንግሥት ካልደረሰልን አሁንም ግድያ ይኖራል – ነዋሪዎች April 1, 2021 01:04 am
  • በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ April 1, 2021 12:39 am
  • “በኢትዮጵያ ክብርና ጥቅም ከመጣችሁ አንገቴ ይቀላል እንጂ አልደራደርም” March 24, 2021 01:22 am
  • “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ March 23, 2021 11:28 pm
  • እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ March 23, 2021 10:23 pm
  • በርግጥ ኢትዮጵያ ዝናብ አዝንባለች? March 23, 2021 10:15 pm
  • አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች March 21, 2021 08:57 pm
  • ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ March 19, 2021 04:32 pm
  • ባልደራስና የአብን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ March 18, 2021 01:56 pm
  • ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም” March 17, 2021 09:54 pm
  • በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት March 17, 2021 04:54 am
  • ምርጫ ቦርድ ከፈቀደለት ኦነግ በምርጫው እንደሚወዳደር አስታወቀ March 17, 2021 04:30 am
  • በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው March 15, 2021 11:25 am
  • በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ March 15, 2021 10:13 am
  • የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ March 15, 2021 09:26 am
  • በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ March 15, 2021 09:04 am
  • በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ March 15, 2021 08:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule