የትግራይ ዲያስፖራ የሳይበር ቡድን (Diaspora Cyber Team) ትላንት (Sep 5) ስብሰባ ነበራቸው።የእኛ ሰዎችም የሳይበር ውይይታቸውን ሰብረው በመግባት ታድመው ወጥተዋል። አጀንዳዎቹ:- 1- አለም አቀፍ ጫናዎችን በድጋሜ በአዲስ መልክ እንዴት እንፍጠር? 2- ትግራይ ውስጥ ቤተሰቦቻችን በርሃብ እያለቁ ነው። ለዚህስ መፍትሄው ምንድነው? 3- ህወሓት/የትግራይ መንግስት ምን ማድረግ አለበት? የሚሉ ናቸው። የተስማሙባቸው ነጥቦች:- 1ኛ) ጦርነቱ ትግራይ መሬት ላይ በነበረበት ወቅት ተዘረፍን ፣ ሴቶች ተደፈሩ ፣ በጅምላ ተገደልን ... ብለን የአለም አቀፍ መንግስታት ጫና እንዲፈጥሩ አድርገናል። አሁን ያንን መንገድ መከተል አዋጭ ስላልሆነ 5.2 ሚሊዮን ህዝብ በርሃብ እየተጎዳና እየሞተ እንደሆነ ፣ ወደ ትግራይ እየገባ ያለው የእርዳታ እህልም እጅግ … [Read more...] about የዳያስፖራ ትህነጎች ቀጣይ አጀንዳ
operation dismantle tplf
በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ ከ31 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይት ተያዘ
በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ ከ31 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶችን ከሁለት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉን የምዕራብ ወለጋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ህገ-ወጥ ጥይቶቹን በአይሱዙ የጭነት መኪና ሲጓጓዝ በተደረገ ክትትልና ፍተሸ መያዙን በምዕራብ ወለጋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የአከባቢ ጸጥታና ደህንነት ምክትል ዳይሬክተር ሳጅን ምትኩ ብርሃኑ ገልጸዋል። ዳይሬክተሩ ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ ተግባራትን በማጋለጥና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ማቅረባቸውን ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በምዕራብ ወለጋ ዞን ነጆ ከተማ ከ31 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይት ተያዘ
ስለ አገር ሰላምና አንድነት የ5 ቀናት ፀሎትና ምህላ ታወጀ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጳጉሜ ወር ለሀገር ሰላም እና አንድነት በመላው ዓለም በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፀሎት እና ምህላ ወስኗል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ፣ ጌዴኦ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፥ ቋሚ ሲኖዶሱ 5ቱን የጳጉሜ ቀናት በፀሎትና ምህላ እንዲታሰብ መወሰኑን ገልፀዋል። ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፥ 2013 ዓ.ም ብዙ ችግሮችን ያሳየ መሆኑን ያነሱ ሲሆን "በፈተናው ውስጥም ቢሆን ግን ብዙ በረከቶችን ያሳየን ነገሮች አሉ" ብለዋል። እንደሀገር፤ እንደዓለምም የተከሰቱ ችግሮች ወደቀጣይ ዓመት አብረው እንዳይተላለፉ እግዚአብሔርን በፀሎት መጠየቅ ስላለብን ይህ ውሳኔ ተላልፏል ሲሉ አስረድተዋል። አክለውም፥ "ቤተክርስቲያን በሀገራችን ውስጥ ያለው ጦርነቱ፣ ረሃቡ፣ ስደቱ፣ … [Read more...] about ስለ አገር ሰላምና አንድነት የ5 ቀናት ፀሎትና ምህላ ታወጀ
የስደተኛ መታወቂያ የያዙ የትህነግ ተዋጊዎች ተይዘዋል፤ ተመድ እያጣራ ነው ብሏል
“የስደተኞች መታወቂያን ይዘው ተገኝተዋል” የተባሉ ታጣቂዎችን ጉዳይ እያጣራ እንደሆነ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ከፍተኛ የስደተኞች ጉዳይ ኤጀንሲ ገለጸ። ኤጀንሲው “በሱዳን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የነበሩና የተመድ ስደተኞች ኤጀንሲ መታወቂያ የያዙ ታጣቂዎች ተገኙ” የሚሉ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘዋወሩና በተለያዩ የሚድያ አውታሮች ሲዘገቡ መመልከቱን ስለ ጉዳዩ ለጠየቀው አል ዐይን አማርኛ በላከው የኢ-ሜይል መልዕክት አስታውቋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር ሰሞኑን በሱዳን አቅጣጫ መጥተው “ሽንፋ የተባለ ቦታን ለመያዝ የተንቀሳቀሱ የቅማንትና ህወሃት ታጣቂዎች መደምሰሳቸው”ን የሚያሳውቅ ጽሁፍ በትዊተር ገጻቸው ማጋራታቸው የሚታወስ ነው። ዓለም አቀፍ ብዙሃን መገናኛዎች ‘ህወሓት ሰብዓዊ እርዳታን እየዘረፈ ነው’ መባሉን “ከዓለም … [Read more...] about የስደተኛ መታወቂያ የያዙ የትህነግ ተዋጊዎች ተይዘዋል፤ ተመድ እያጣራ ነው ብሏል
ባጠናቀቅነው ነሀሴ ወር በቁጥጥር ሥር የዋሉ ህገወጥ የጦር መሳሪያዎች
መነሻውን ከጋምቤላ ያደረገ በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-15074 አ/አ በሆነ ዶልፊን ህዝብ ማመላለሻ ሲዘዋወር የነበረ ህገወጥ መሳሪያ ከነተጠርጣሪዎቹ በዚህ ወር ተይዟል፤ የተያዘው መሳሪያ በቁጥር 12 ክላሽንኮቭ እና 5 ጥይት መያዣ ነው። የሰሌዳ ቁጥር A76390 በሆነ ቪትዝ መኪና 5 ክላሽንኮቭ ከ132 ጥይት ጋር ሲዘዋወር በድንገተኛ ፍተሻ ተይዟል (እንደ ጎንደር ከተማ ፖሊስ መረጃ) በሀመር ወረዳ በዚህ እያጠናቀቅን ባለነው ወር ውስጥ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 10 መሳሪያ፣ 14 ክላሽ ጥይት፣ 3 የክላሽ መጋዘን ተይዟል። በአዲስ አበባ ቦሌ ክ/ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው ውሃ ልማት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው አምባሳደር ፔንሲዮን ውስጥ 10 ባለሰደፍና 10 ታጣፊ ክላሽንኮቭ ጠብመንጃዎች እና 17 የክላሽንኮቭ ጥይት ካርታዎች ተይዘዋል። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 2 … [Read more...] about ባጠናቀቅነው ነሀሴ ወር በቁጥጥር ሥር የዋሉ ህገወጥ የጦር መሳሪያዎች
ሰሞኑን በተደረገው ጦርነት ከ10ሺህ በላይ የትህነግ ታጣቂዎች ተገድለዋል
የኢትዮጵያ መካለከያ ሠራዊት ቅዳሜ በሰጠው መግለጫ በከሃዲው ጄነራል ምግበይ ይመራል የሚመራው “አርሚ 1” የተባለ ኃይል ሙሉ በሙሉ መደምሰሱን በይፋ አሳወቀ። መግለጫውን የሰጡት የመከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊት ግንባታ ዋና አስተባባሪ ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ግዳጅ አፈጻጸምና ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። ህወሓት ህፃናትን አሰልፎ በአማራ ክልል ወረራ መፈፀሙን ያነሱት ሌ/ጄነራል ባጫ የቡድኑ ፍላጎት ኢትዮጵያ የምትባልን ሀገር መበታተን ነው ብለዋል። ህወሓት ስልጠና ያልወሰዱ ህፃናትን ወደ ጦርነት በመማገድ ላይ ነው ሲሉም አክለዋል። የትግራይ ወጣቶችን ከተቻለ ሁለት ቀን አሰልጥኖ አንድ ጠመንጃ ለአምስት ሰጥቶ ወደግምባር ካስገቡ በኋላ መሪዎቹ ውጊያውን ስለሚያውቁ ተኩስ ሲበዛባቸው ወደኋላ የሚሸሹትን እንደሚገድል ነው … [Read more...] about ሰሞኑን በተደረገው ጦርነት ከ10ሺህ በላይ የትህነግ ታጣቂዎች ተገድለዋል
“ኢትዮጵያ ጀግና ከመውለድ፤ ፀሀይም በምስራቅ ከመውጣት ቦዝነው አያውቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ኢትዮጵያ ጀግና ከመውለድ ፀሀይም በምስራቅ ከመውጣት ቦዝነው አያውቁም ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በዛሬው እለት በኢፌዴሪ መከላከያ ሰላም ማስከበር ማዕከል የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት በሶስተኛ ዙር በመሰረታዊ ውትድርና የሰለጠኑ ምልምል ወታደሮች ምረቃ ላይ ተገኝተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ምረቃ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ አገሬን አትንኳት ብለው ከመላ ኢትዮጵያ የዘመቱ ጀግኖች በግንባር አኩሪ ድል እያስመዘገቡ መሆኑን ገልፀው፤ የዛሬ ተመራቂዎችም ለአገር አንድነትና ክብር ለመዋደቅ የሰራዊቱ አባል ለመሆን መወሰናቸው የሚደነቅና የሚያኮራ ነው ብለዋል። አሸባሪው የህወሓት ቡድን የኢትዮጵያ እንቅርት … [Read more...] about “ኢትዮጵያ ጀግና ከመውለድ፤ ፀሀይም በምስራቅ ከመውጣት ቦዝነው አያውቁም” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን፤ ባለ 5 መታወቂያና 25 የባንክ ደብተሮች ባለቤት
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲስ አበባ አምስት የቀበሌ መታወቂያ እና 25 የተለያዩ የባንክ ደብተሮች ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። ግለሰቡ በያዛቸው የባንክ ደብተሮች ውስጥ 2 ሚሊየን 966 ሺህ 189 ብር እንደተገኘበት ኮሚሽኑ አስታውቋል። አቶ መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን የተባለው ግለሰብ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ስሙ ናሆም አደባባይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ምርመራ እየተካሄደበት እንደሚገኝ የፀጥታና ህግ-ማስከበር የቀጠና 1 ሻለቃ 2 ኃይል 1 አዛዥ ኢንስፔክተር አዲሱ ተሾመ ገልፀዋል። አሁን ያለውን ወቅታዊ የፀጥታ ችግር የአሸባሪው ህወሓት ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ለመፈፀም የተለያዩ ሰዎችን እየተጠቀመ መሆኑንም ተናግረዋል። ከዚህ አንጻርም የሽብር ቡድኑን ተግባር ለማስፈፀም … [Read more...] about መሃሪ ተከስተ ገብረኪዳን፤ ባለ 5 መታወቂያና 25 የባንክ ደብተሮች ባለቤት
የሰሞኑ የጦር ድሎች
የወገን ጦር በወሰደው የማጥቃት ርምጃ ፍላቂትን ከአሸባሪው ትህነግ ቡድን አስለቀቀ የመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኀይል፣ ሚሊሻና ፋኖ በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ላይ በጥመረት በወሰዱት እርምጃ ፍላቂትን አስለቅቀዋል። የወገን ጦር የማጥቃት እርምጃውን አጠናክሮ በመቀጠል ወደፊት እየገሰገሰ መሆኑ ተገልጿል። በአሁኑ ሰዓትም በደብረዘቢጥ እና አካባቢው የቀረው የአሸባሪ ርዝራዥ ቡድን ሙሉ በመሉ ተለቅሞ የአካባቢው ነዋሪዎች መደበኛ ሥራቸውን ቀጥለዋል ሲል አሚኮ ዘግቧል። በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን ተደመሰሰ በደባርቅ አካባቢ በብና ሜዳ ሾልኮ ለመግባት የሞከረው የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂ ቡድን በዛሬው ዕለት ተደምስሷል። ታጣቂ ቡድኑ በዝንጀሮ አፋፍ፣ ወርቅ አዝላ እና በቅሎ ማነቂያ ሾልኮ ለመግባት ተደጋጋሚ … [Read more...] about የሰሞኑ የጦር ድሎች
የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን ለመግባት የሞከረው የትህነግ ቅጥረኛ ኃይል ተደምስሷል
የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን በአልምሃል ሰርጎ ለመግባት የሞከረው የጁንታው ቅጥረኛ ኃይል መደምሰሱ የመከላከያ ሠራዊት አስታወቀ። የመተከል ዞን የተቀናጀ ግብረ ሃይል ኮማንድ ፖስት የኦፕሬሽን ዘርፍ አሰተባባሪ ኮሎኔል ሰይፈ ኢንጊ ቅጥረኛው ቡድን የተለያዩ ፀረ ሰው እና ፀረ ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን ለማጥመድ የሞከረ ቢሆንም መቋቋም ተስኖት ተበታትኗል ሲሉ ተናግረዋል። ጠላት አሳቻ ስአት ጠብቆ አካባቢውን ለማተራመስ ቢንቀሳቀስም የጠላትን እንቅስቃሴ ከመነሻው በንቃት ሲከታተሉ የነበሩት የመከላከያ ሰራዊታችን ክፍሎች ተቀናጅተው እርምጃ ወስደውበታል ብለዋል ። የጠላት ኃይል በጀግናው ሰራዊት የበላይነት ተወስዶበት ሀምሳ የሽብር መልዕክተኞች ሲደመሰሱ ፣ከሰባ በላይ መቁሰላቸውን አስተባባሪው ገልፀዋል ።የተረፈው ኃይል ደግሞ አግሬ … [Read more...] about የአባይን ግድብ ግንባታ ለማደናቀፍ ከሱዳን ለመግባት የሞከረው የትህነግ ቅጥረኛ ኃይል ተደምስሷል