ጃዋር የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙ ሕገወጥ ነው ሲል የዳውድ ኦነግ ከሰሰ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው አንዱ ኦነግ ጃዋር መሐመድ ገለቶማ በሚለው የአውሮጳና የአሜሪካ ስብሰባ ላይ የኦነግን ባንዲራ መጠቀሙን ኮነነ። ከእንግዲህ ወዲህ እንዳይጠቀም ትዕዛዝ አዘል ደብዳቤ ለኦፌኮ ጻፈ። በዳውድ ኢብሳ የሚመራውና በምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተብሎ የተመዘገው ፓርቲ ባንዲራዬን ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀመ ነው ሲል መረራ ጉዲና ለሚመራው ኦፌኮ ቅሬታውን አሰምቷል። ከሁለት ቀናት በፊት በተጻፈውና በዳውድ ኢብሳ በተፈረመው ደብዳቤ ጉዳዩ በሚለው ርዕስ ሥር በሕጋዊ መልኩ በምርጫ ቦርድ የተመዘገበውን የኦነግን ባንዲራ የኦፌኮ ምክትል ሊቀመንበር ጃዋር መሐመድ በሕገወጥ መልኩ መጠቀሙን ስለማስቆም የሚል ነው። ደብዳቤው ሲያጠናቅቅም ከረር ያለ ማስጠንቀቂያ … [Read more...] about ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት
olf shanee
የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርኃኑ ጁላ ከዑጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ የሁለቱ አገሮች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይታቸው የሁለቱ አገሮች የመከላከያ ዘርፍ ስምምነት ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ ስምምነቱን ለማደስ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ሥምምነቱን የማደስ ሥራ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲፈፀም መመሪያ ተሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሁለቱ ኃላፊዎች በዋናነት ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘገብ ስለነበረውና አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የሥልጠናና ሌሎች ድጋፎችን በአሜሪካ፣በግብጽና በደቡብ ሱዳን በመታገዝ በዑጋንዳ አማካኝነት እገዛ እያገኘ ነው የሚለውን ወሬ የዑጋንዳ መከላከያ ሚኒስትር ፈፅሞ ከዕውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሀገራቸው ኢትዮጵያን የአፍሪካ እናት … [Read more...] about የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
166, 800 የአሜሪካን ዶላር፤ 19,850 ዩሮና ለሸኔ ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያ ተያዘ
መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ ያደረገ አንድ ህገወጥ የገንዘብ አዘዋዋሪ ግለሰብ ዶላር እና ዩሮ በመኪና ጭኖ ወደ ጅቡቲ በጉዞ ላይ እያለ በቁጥጥር ስር ውሏል። ግለሰቡ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ3-68991 በሆነ ኮንቴነር ተሽከርካሪ ላይ 166 ሺህ 800 የአሜሪካን ዶላር እና 19 ሺህ 850 ዩሮ በመጫንና መዳረሻውን ጅቡቲ በማድረግ በመጓዝ ላይ እያለ በተደረገ ጥብቅ ክትትል መያዙን የኢፕድ ምንጮች ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ላይ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በደረሰው ጥቆማ አዘዋዋሪውን ከነ ገንዘቡ በቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉንም ነው ምንጮቻችን ጨምረው የገለጹት፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ መነሻቸውን ሀረሪ ክልል ሀረር ከተማ ያደረጉ ሶስት ህገወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪ ግለሰቦችም ከእነጦር መሳሪያቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እነዚሁ … [Read more...] about 166, 800 የአሜሪካን ዶላር፤ 19,850 ዩሮና ለሸኔ ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያ ተያዘ
ትህነግንና ሸኔን በአፍሪካ ደረጃ አሸባሪ አድርጎ ለማስፈረጅ እየተሠራ ነው
ድልድይ በማፍረስ፤ መሠረተ ልማቶችን በማውደም ከየቦታው በተለቃቀሙ ወንበዴዎች መሪነት ኢትዮጵያን በ“ነጻ አውጪ” ስም በግፍ ሲገዛ የነበረው ትህነግ በአፍሪካ በትክክለኛ መጠሪያ ስሙ ሊጠራ ዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ህወሓትና ተላላኪዎቹ በአሸባሪነት እንዲሰየሙ ተጠየቀ አሸባሪው ህወሓት በሕገወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር በሕግ መታገድ፤ መሪዎቹም በኃላፊነት መጠየቅ አለባቸው አሸባሪው … [Read more...] about ትህነግንና ሸኔን በአፍሪካ ደረጃ አሸባሪ አድርጎ ለማስፈረጅ እየተሠራ ነው
ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት ከተበታተነ በኋላ ንፁሃን ላይ ጥቃት እየፈፀመ ያለውን አሸባሪው ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ። ጠንካራ የህዝብ አደረጃጀት በመፍጠር በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሰራው ኦፕሬሽን የሽብር ቡድኑ ከበፊት ቁመናው እና ይዞታው መዳከሙን የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል። ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት የተበታተነው አሸባሪው ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ንፁሃንን የማጥቃት የተለመደ የጥፋት ድርጊቱን እየፈፀመ ነው ብለዋል። ይህን የጥፋት ድርጊቱን ለማስቆም በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መልኩ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በመንግሥት መዋቅር ላይ ሆነው ከአሸባሪው ሸኔ ጋር በማበር በህዝብ እና … [Read more...] about ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
“በሸኔ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ከፍተኛ ግጭት ተሸጋግሯል”
በአሸባሪው ሸኔ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ከፍተኛ ግጭት መሸጋገሩንና መንግስት በቡድኑ ላይ የሚወስደው እርምጃም አጠናክሮ መቀጠሉን የኦሮሚያ ኮሚንኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ አስታወቁ። አቶ ሀይሉ የክልሉን ሰላምና ልማት አስመልክተው ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ የክልሉን ሰላም እያናጋ ያለው የሸኔ ሽብር ቡድን ከሁሉም በማስቀደም በሰላማዊ መንገድ እንዲመለሱ በአባ ገዳዎችና በሀዳ ሲንቄዎች በተደረገው ጥሪ 312 የቡድኑ አባላት ተመልሰዋል። 540 የሚሆኑት ደግሞ በህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ከታህሳስ 16 እስከ 30 ዓ.ም በተወሰደው እርምጃ 876 አባላት ሲደመሰሱ ኮማንድ ፖስቱ ስራ ከጀመረ ወዲህ በጥቅሉ ሁለት ሺህ 439 የቡድኑ አባላት ተደምስሰዋል ብለዋል። በተመሳሳይ መልኩ ወደ ሰላማዊ መልኩ ወደ ሰላማዊ … [Read more...] about “በሸኔ አባላት መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ወደ ከፍተኛ ግጭት ተሸጋግሯል”
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወዲህ ከ2 ሺህ 400 በላይ የኦነግ ሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
በሁለት ሳምንት ውስጥ ብቻ 876 በሚሆኑ የየኦነግ ሸኔ አባላት ላይ ተወስዷል የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሃይሉ አዱኛ በክልሉ የልማትና የፀጥታ ስራዎች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። የአሸባሪውን ሸኔ አጥፊ ቡድን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተቀላቀሉ ወጣቶች ከአባገዳዎች ጋር በመነጋገር 312 ወጣቶች እጅ እንዲሰጡ መደረጉ ተነግሯል። የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ባለው ስራም በሁለት ሳምንት ብቻ 876 የሚሆኑ የቡድኑ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱም በመግለጫው ተነስቷል ። ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወዲህም ከ2 ሺህ 400 በላይ የቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ፥ በህብረተሰቡ ጥቆማ 540 የሚሆኑት በቁጥጥር ስር ውለዋል ነው የተባለው። የአካባቢ ጥበቃ ስራን በተመለከተም፥ ለምርትና ምርታማነት ወሳኝ ሚና የሚጫወተው የአካባቢ ጥበቃ ስራ በኦሮሚያ ክልል ደረጃ … [Read more...] about ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወዲህ ከ2 ሺህ 400 በላይ የኦነግ ሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሐመድ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ አስቀድሞ የክልሉ ፖሊስ የተጠናከር የክትትል ስራ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ኮሚሽነሩ እንዳሉት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ወጥቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የክልሉን ሠላም ለማስጠበቅ ለፀጥታ አስከባሪ ኃይሉ ተጨማሪ አቅም ሆኖታል። ግለሰቦቹ በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበራቸው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሰረት ከጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባደረገው ኦፕሬሽን ነው ብለዋል፡፡ አሸባሪው … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የሽብር ተግባር ለመፈጸምና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ የሸኔ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ ሽብርተኛው ሸኔ በንፁሃን ዜጎች እና በፀጥታ አካላት ላይ ግድያ እንዲፈፅሙ መልምሎ እና ስልጠና ሰጥቶ ለጥፋት ተልዕኮ ካሰማራቸው ግለሰቦች መካከል በስሩ 5 የገዳይ ቡድን አባላትን በማደራጀት በህቡዕ ሲንቀሳቀሰ የነበረው ጃፋር መሐመድ ሳኒ የተባለው ተጠርጣሪ በተደረገበት ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ይህ የሸኔ ታጣቂ በቁጥጥር ስር የዋለው በስሩ ካደራጃቸው 5 ግብረ አበሮቹ ጋር በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ኦዳ ቡልቱም ወረዳ ሚደግዱ ቀበሌ እና ቦረማ ጫካ እንዲሁም ዳሮ ለቡ ወረዳ ሚጨታ እና በዴሳ ከተማ ውስጥ በንፁሃን ዜጎች እና በመንግሥት ፀጥታ … [Read more...] about ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ ከተማ ፅንፈኛው የአሸባሪ ቡድን ሸኔ ጥቅምት 1 እና 2 በንፁሃን ላይ በከፈተው ጥቃት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ቡድኑ ከህውሃት የሽብረ ቡድን ጋር ህብረቱን ካረጋገጠ በኋላ በብሄር ብሄረሰቦች ላይ ትንኮሳ በማድረግ ግጭቶችም የብሄር መልክ እንዲይዙ እየሰራ ይገኛል ብለዋል የቢሮው ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ። ኃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ሸኔ በአካባቢው ከሚንቀሳቀስ ሌላ የሽፍታ ቡድን ጋር በመተባበር በሀሮ ከተማ በከፈተው ጥቃት የ15 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የንብረት ውድመት እንዳደረሰ እንዲሁም 967 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ተጨማሪ የፀጥታ ሀይል ወደ ስፍራው በማሰማራት ወረዳውን እና ከተማውን … [Read more...] about በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ