በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሐመድ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከመውጣቱ አስቀድሞ የክልሉ ፖሊስ የተጠናከር የክትትል ስራ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ኮሚሽነሩ እንዳሉት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ወጥቶ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የጸደቀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የክልሉን ሠላም ለማስጠበቅ ለፀጥታ አስከባሪ ኃይሉ ተጨማሪ አቅም ሆኖታል። ግለሰቦቹ በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉት ከአሸባሪዎቹ ህወሓት እና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበራቸው ፖሊስ በደረሰው መረጃ መሰረት ከጥቅምት 21 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ባደረገው ኦፕሬሽን ነው ብለዋል፡፡ አሸባሪው … [Read more...] about በቤኒሻንጉል ከትህነግና ሸኔ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው 98 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
olf shanee
ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
የሽብር ተግባር ለመፈጸምና የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ የሸኔ ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢቢሲ በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፣ ሽብርተኛው ሸኔ በንፁሃን ዜጎች እና በፀጥታ አካላት ላይ ግድያ እንዲፈፅሙ መልምሎ እና ስልጠና ሰጥቶ ለጥፋት ተልዕኮ ካሰማራቸው ግለሰቦች መካከል በስሩ 5 የገዳይ ቡድን አባላትን በማደራጀት በህቡዕ ሲንቀሳቀሰ የነበረው ጃፋር መሐመድ ሳኒ የተባለው ተጠርጣሪ በተደረገበት ጥብቅ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡ ይህ የሸኔ ታጣቂ በቁጥጥር ስር የዋለው በስሩ ካደራጃቸው 5 ግብረ አበሮቹ ጋር በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ኦዳ ቡልቱም ወረዳ ሚደግዱ ቀበሌ እና ቦረማ ጫካ እንዲሁም ዳሮ ለቡ ወረዳ ሚጨታ እና በዴሳ ከተማ ውስጥ በንፁሃን ዜጎች እና በመንግሥት ፀጥታ … [Read more...] about ለሸኔ የጦር መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስተላለፍ የሞከሩ ተያዙ
በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
በምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ ከተማ ፅንፈኛው የአሸባሪ ቡድን ሸኔ ጥቅምት 1 እና 2 በንፁሃን ላይ በከፈተው ጥቃት በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን የኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል። ቡድኑ ከህውሃት የሽብረ ቡድን ጋር ህብረቱን ካረጋገጠ በኋላ በብሄር ብሄረሰቦች ላይ ትንኮሳ በማድረግ ግጭቶችም የብሄር መልክ እንዲይዙ እየሰራ ይገኛል ብለዋል የቢሮው ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ። ኃላፊው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ሸኔ በአካባቢው ከሚንቀሳቀስ ሌላ የሽፍታ ቡድን ጋር በመተባበር በሀሮ ከተማ በከፈተው ጥቃት የ15 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የንብረት ውድመት እንዳደረሰ እንዲሁም 967 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ተናግረዋል። የክልሉ መንግስት ተጨማሪ የፀጥታ ሀይል ወደ ስፍራው በማሰማራት ወረዳውን እና ከተማውን … [Read more...] about በወለጋ የሰፈሩ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ትህነጎችና የሸኔ ግፍ
በነሐሴ ወር ብቻ 180 የሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
በነሐሴ ወር ብቻ በተወሰደ ወታደራዊ ኦፕሬሽን 180 የሸኔ አባላት መደምሰሳቸውን በመከላከያ ሰራዊት የደቡብ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አሰታወቀ። የዕዙ የኋላ ደጀን አሰተባባሪ ኮለኔል ግርማ አየለ እንደገለጹት፣ በተያዘው ወር ቡድኑ ይንቀሳቀስባቸው በነበሩ ምዕራብ ጉጂ፣ ምሥራቅ ጉጂ እና በቦረና ዞኖች በተካሄደ አራት ወታደራዊ ዘመቻዎች 180 አባላቱ ሲደመሰሱ 94ቱ ቆሰለዋል፣ 2ቱ ደግሞ ተማርከዋል። እርምጃው ከተወሰደባቸው የሠራዊት አባላቱ ወስጥ የህወሓት የሽብር ቡድን ያሰለፋቸው ታጣቂዎች መገኘታቸውንም ኮለኔል ግርማ አስረድተዋል። በወታደራዊ ዘመቻው የተማረከው የሼ አባል ሞርከታ ጎበና በሸኔ ጉዳይ አሰፈፃሚዎች ተመልምሎ ኬንያ ሀገር ስልጠና ወስዶ መመለሱን እና በስሩ 50 የሸኔ ሚሊሻዎችን ይመራ እንደነበር ለኢቲቪ ገልጿል። ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት … [Read more...] about በነሐሴ ወር ብቻ 180 የሸኔ አባላት ተደምስሰዋል
ለትህነግና ሸኔ ገንዘብ ሲያስተላልፉና ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ሲፈጽሙ የነበሩ በቁጥጥር ሥር ዋሉ
ለአሸባሪዎቹ የህወሓትና ሸኔ ቡድኖች በተለያዩ ህገወጥ መንገዶች ገንዘብ ሲያሰባስቡና ሲያስተላልፉ የነበሩ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ አሻጥር በመፈጸም ህብረተሰቡን ለአመጽ ለማነሳሳት ሙከራ ሲያደርጉ የነበሩ በአዲስ አበባ 51 እንዲሁም በአፋር ክልል 6 በድምሩ 57 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡ ግብረሃይሉ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤አዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ተሰማርተው ከአሸባሪዎቹ ህወህትና ሸኔ ቡድን ጋር ሚስጥራዊ ግንኙነት በመፍጠር በህገወጥ መንገድ ገንዘብ ሲያሰባስቡና ሲያስተላልፉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ከተለያዩ ማስረጃዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥ አንድ አንድ ተጠርጣሪዎች በህግ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ በመሰማራት ለሸብርተኛው … [Read more...] about ለትህነግና ሸኔ ገንዘብ ሲያስተላልፉና ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ሲፈጽሙ የነበሩ በቁጥጥር ሥር ዋሉ
አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
በወሎ ግንባር የተገኙት በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር ዓለሙ ስሜ አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት ለኢትዮጵያ የማይጠቅሙ በመሆናቸው መደምሰስ አለባቸው ብለዋል። የወያኔ እና ሸኔ ጥምረት ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ነው ያሉት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ትህነግም ሸኔን በአንድ ላይ መደምሰስ አለባቸውም ነው ያሉት። የሸኔና የህወሓት ጋብቻ አዲስ ሳይሆን ህወሓት መንግሥት ሆኖም ሳለ ኦሮሞን ለማተራመስ ሲፈልግ ሸኔን ይመሩት እንደነበር ነው ያስታወሱት። አሸባሪው ህወሓት በግንባር ጀግንነት እንደሌለው የገለጹት ዶክተር ዓለሙ ለሚያሠራጨው የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ጆሮ ሳይሰጥ ህብረተሰቡ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። አሸባሪው ህወሓት ወጣቶችን በሀሽሽ እያደነዘዘ እየላከ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ብዙ የአሸባሪው … [Read more...] about አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
“ሸኔ ኦሮምኛ የሚናገር አሸባሪ ህወሓት ነው”
አሸባሪው ህወሓትን ለማጥፋት የሚደረገው ትግል በአሸባሪው ሸኔ ላይም ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚገባ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደአ አሳሰቡ። አቶ ታዬ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ አሸባሪው ህወሓትም ሆነ ሸኔ ለሀገር እና ለህዝብ ጠንቅ በመሆናቸው አሸባሪው ህወሓትን ለማጥፋት የሚደረገው ትግል ሁሉ በአሸባሪው ሸኔ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ሊተገበር ይገባዋል። የኦሮሞ ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለመጠበቅ፣ ሉዐላዊነቷን ለማስከበር፣ ብልጽግናዋን እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባዋል። የቡድኖቹ በጋራ ለመንቀሳቀስ መስማማት ‹‹በግልጽ አብረን ስንሰራ ነበር፣ ኦሮሞን ስናሰቃይ፣ ኢትዮጵያ ላይ ወንጀል ስንፈጽም የነበረው በጋራ ነው፣ ወንጀሎቹ ሁለታችንንም እኩል ይመለከቱናል የሚል መልዕክት አለው›› … [Read more...] about “ሸኔ ኦሮምኛ የሚናገር አሸባሪ ህወሓት ነው”
ዓለምአቀፉ አሸባሪ ትክክለኛ ስሙን አገኘ
ድልድይ በማፍረስ፤ መሠረተ ልማቶችን በማውደም ከየቦታው በተለቃቀሙ ወንበዴዎች መሪነት ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም በግፍ ሲገዛ የነበረው ህወሃት/ትህነግ ዛሬ ትክክለኛ ስሙን አገኘ። ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ከዚህ በታች የሚገኘው መረጃ በዓለምአቀፉ የአሸባሪዎች ቋት ተመዝግቦ የሚገኝ የህወሃት ወንጀል ዝርዝር ነው። የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ “ህወሓት” እና “ሸኔ” … [Read more...] about ዓለምአቀፉ አሸባሪ ትክክለኛ ስሙን አገኘ
“በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
በርካቶች 'ሸኔ' እያለ እራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት እንዴት አሸባሪ ተብሎ ይሰየማል ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ስያሜ አንዳች ነገር ለመሸፈን ተፈልጎ ነው በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚገልፁ ምሁራንም አልጠፉም። ለመሆኑ 'ሸኔ' ማነው? በዚህ ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት የተጠየቁት የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዮስ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል፦"በተለምዶ 'ሸኔ' የሚባለው እራሱን ደግሞ 'የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት' ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው። በምዕራብ ኦሮሚያ፣ በሌሎችም ክልሎች እየተንቀሳቀሰ ጥቃት የሚያደርስ ድርጅት ነው። እራሱ ለእራሱ የሰጠውን ስያሜ ግን እኛ የምናፀድቅበት ምክንያት የለንም፤ ተገቢም አይሆንም ብለን እናምናለን። ይህ ቡድን ከዚህ በፊት እንደ 'ህወሓት' ተመዝግቦ፣ ህጋዊ እውቅና፣ ህጋዊ ሰውነት እና ሰርተፊኬት ኖሮት የሚያውቅ አይደለም፤ … [Read more...] about “በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና
ውሳኔ ከመዘግየቱ በስተቀር ተገቢ ነው፤ የህግ ባለሙያዎች የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ተቀዳሚ ሊቀመንበር የሆኑት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ መንግስት “ሸኔ” እና “ህወሓት” ቡድንን በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ ለማድረግ መዘጋጀቱ መሰረታዊ ለውጥ አያመጣም ብለዋል፡፡ እንዲህ አይነት ፍረጃ የቀድሞ መንግስትም ሲያደርገው የነበረ ነዉ የሚሉት ፕሮፌሰሩ፣ ይህ ዓይነቱ ፍረጃ መሰረታዊ ለውጥ የሚያመጣ ቢሆን እዚህ ደረጃ ላይ አንደርስም ነበር፤ ይህም ተግባር ቀድሞ ከነበረው መንግስት የተለየ ነው ብዬ አላስብም ብለዋል ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፡፡ “ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ሀይሎችን በተዘዋዋሪ መጥራት ይመስለኛል የሚሉት ፕሮፌሰር መረራ በዚህ ስም ራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት፣ መንግስት ግን በኦሮሚያ አካባቢ በኦሮሞ ስም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ኢላማ … [Read more...] about ሸኔ የሚባል የፖለቲካ ፓርቲ የለም፣ ህወሃትና ሸኔ አሸባሪ መባላቸው ለውጥ አያመጣም፤ መረራ ጉዲና