• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ

July 6, 2022 01:38 pm by Editor Leave a Comment

“የዘር ማጥፋት” ወንጀሎች የሚመረምር ልዩ አቃቤ ህግ እንዲቋቋም ጠየቀ

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅና የፌደራል የጸጥታ ኃይል እንዲሰማራም ጠይቋል

ጥቃቱን “ዘር ማጥፋት ብሎታል።

የአብን ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) እና የንቅናቄው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር መሐመድ ፤ በአማራ ተወላጆች ላይ በተፈጸመው “የዘር ማጥፋት” ዙሪያ ዛሬ በአዲስ አበባ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

አብን፤ በኦሮሚያ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈፀሙ “የዘር ማጥፋት” ወንጀሎች የሚመረምር ልዩ አቃቤ ህግ በአዋጅ እንዲቋቋም ጠይቋል፡፡ ይህንን ተከትሎም የወንጀል ፈፃሚዎች በግልፅ ችሎት መዳኘት እንዳለባቸው ንቅናቄው ጠይቋል፡፡

የፓርቲው ሊቀ መንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ፤ በአማራ ሕዝብ ላይ ባለፉት ዓመታት የተሰራው የተሳሳተ ትርክት አሁን ለሚካሄደው “የዘር ማጥፋት ወንጀል” ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 

የንቅናቄው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር መሐመድ፤ ዜጎች በማንነታቸው ምክንያት እየተጨፈጨፉ ባሉባቸው የወለጋ ዞኖች አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሊታወጅ እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡ አቶ ጣሂር ፤ ሕግ አውጭው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዋጁን እንዲያውጅና የፌደራል የፀጥታ ኃይሎችም በአካባቢው እንዲሰማሩ ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡

“የዘር ማጥፋት” ወንጀሉ ሰለባዎች ራሳቸውን እንዲከላከሉ ሊደረግ እንደሚገባም ነው ንቅናቄው የጠየቀው፡፡ በኦሮሚያ ክልል ማንነት ላይ ያተኮረ ጭፍጨፋ እንዲፈፀም ቅስቀሳ ሲያደርጉ እና እያደረጉ ያሉ አካላት እንዳሉም ነው ፓርቲው በመግለጫው የጠየቀው፡፡ 

የፓርቲው ሊቀመንበር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፤ የመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ አካላት በዚህ ውስጥ እጃቸው ቢኖርበትም በጅምላ ግን እነዚህ ናቸው ማለት እንደሚያስቸግር ተናግረዋል፡፡

የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ያስተላለፈው ውሳኔ ለአማራ ሕዝብ ያለውን ንቀት ያሳየበት ነው ሲልም ነው አብን የገለጸው፡፡ ከዚህ ባለፈም “የብሔር፣ ብሔረሰቦች ጠበቃ” እንደሆነ የሚገልጸው የፌዴሬሽን ም/ቤትም ይህንን ችግር ባለማስቆሙ “የዘር ማጥፋት ወንጀሉ” ተባባሪ ነው ሲል ንቅናቄው ከሷል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)፤ በቀጣይ ሀሙስ ባልታጠቁ ዜጎች (ሲቪሊያን) ላይ የተፈጸመውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል በሁሉም መዋቅሮቹ በተለያዩ መርሃ ግብሮች አስቦት እንደሚውል አስታውቋል፡፡ 

አብን የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች ለኦሮሞ ህዝብ ክብር ሲሉ በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት ጠይቋል።

በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ወለጋ በርካታ ንጽሃን ዜጎች ተገድለዋል፤ ግድያውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ጨምሮ የአማራ እና የኦሮሚያ ክልል መንግስታት አውግዘውታል። የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን(ኢሰመኮ) ግድያው በአማራ ብሔር ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ ነው ማለቱ ይታወሳል። (አል-ዐይን)

ዛሬ በተደረገው የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ስብሰባ ላይ የወለጋውን ጭፍጨፋ በተመለከተ ውሳኔ ሲተላለፍ ከአብን የተቃወሙት ዶር ደሳለኝ ጫኔ ብቻ መሆናቸው ታውቋል። ባለፈው የምክርቤቱን ስብሰባ ረግጠው ከወጡትም መካከል ያሉትም ሆኑ የኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ክርስቲያን ታደለ የተቃውሞ ድምጽ አላሰሙም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: olf shanee, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule