
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርኃኑ ጁላ ከዑጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ የሁለቱ አገሮች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡
ውይይታቸው የሁለቱ አገሮች የመከላከያ ዘርፍ ስምምነት ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ ስምምነቱን ለማደስ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ሥምምነቱን የማደስ ሥራ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲፈፀም መመሪያ ተሰጥተዋል ተብሏል፡፡
ሁለቱ ኃላፊዎች በዋናነት ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘገብ ስለነበረውና አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የሥልጠናና ሌሎች ድጋፎችን በአሜሪካ፣በግብጽና በደቡብ ሱዳን በመታገዝ በዑጋንዳ አማካኝነት እገዛ እያገኘ ነው የሚለውን ወሬ የዑጋንዳ መከላከያ ሚኒስትር ፈፅሞ ከዕውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
የመከላከያ ሚኒስትሩ ሀገራቸው ኢትዮጵያን የአፍሪካ እናት አድርጋ እንደምትመለከታትና ማንኛውም ፀረ-ኢትዮጵያ የሆነ ኃይል በዑጋንዳ ለመንቀሳቀስ ፈፅሞ እንደማይፈቀድለት አረጋግጠው አንዳንድ ወገኖች በኢትዮጵያና በዑጋንዳ መካከል ያለውን የረዥም ጊዜ የጠበቀ ግንኙነት ለማደፍረስ እየሰሩ በመሆኑ ከእነዚህ አፍራሽ ኃይሎች ድርጊት መጠንቀቅ እንደሚገባ ሚኒስትሩ ማሳሰባቸዉን ከዉጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ያገኘነዉ መረጃ አመልክቷል፡፡
የትህነግና የሸኔ ታጣቂዎች መሸሸጊያ የሆነችው ዩጋንዳ አሁንም በዚሁ ተግባሯ ቀጥላለች የሚል ክስ ይቀርብባታል። የመከላከያ ኃላፊዎቹም ውይይት ይህንን አጀንዳ እንዳደረገ ይገመታል።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
Leave a Reply