የክልል መስተዳድሮችም በየደረጃው ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ተነግሯቸዋል ሙስና ሀገርን የሚበላ ነቀዝ ነው፡፡ የሀገርን አንጡራ ሀብት እየቦረቦረ ጥሪቷን ባዶ ለማስቀረት ሌት ተቀን የሚማስን ተባይ ነው። ዋልጌ ባለሥልጣናት፣ በፍቅረ ነዋይ የታወሩ ደላሎች እና ባለሃብቶች አንድ ላይ ሲገጥሙ፤ ከነዚህ የሌብነት ፊታውራሪዎች ጀርባ ብዛት ያላቸው ዜጎች መሰለፍ ሲጀምሩ ሙስና የተባለው ነቀዝ ሀገርን እንደ ወረርሽኝ ያጠቃታል፡፡ ሙስና በየትኛው ቦታና በየትኛውም ዘመን ሊኖር ይችላል፡፡ ነገር ግን የሀገርን ልማት አጥንቱ ድረስ እስከ መጋጥ ከደረሰ ሙስና አንድ አደገኛ ወረርሽኝ ሆኗል ማለት ነው፡፡ ሙስና ሀገርን ሊያፈርስ የሚችል የደኅንነት ሥጋት መሆኑን ያስመሰከሩ ሀገሮችን በዘመናችን አይተናል፡፡ የአደንዛዥ ዕጽ፣ የኮንትሮባንድ፣ ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ንግድ፣ … [Read more...] about በሌብነት “አደገኛ ወረርሽኝ” ላይ አገራዊ ጦርነት ታወጀ
Archives for November 2022
መፍትሔ የሚሹ የኢትዮጵያ የጎን ውጋቶች
ኢትዮጵያ ባለፉት አራት በላይ በሆኑ ዓመታት ከባድ ጫናዎችን ተሸክማ ቆይታለች። ይልቁንም የሰሜኑ ጦርነት በውስጥም በውጭም ገፊና ሳቢ ምክንያቶችን ፈጥሮ ሲያናውጣት ቆይቷል። ይኸው ጦርነት ኹለት ዓመት ሊደፍን የዋዜማው እለት የተደረሰው የሰላም ስምምነት በጉዳዩ ላይ የብዙዎች ተስፋ እንዲያንሰራራ አድርጓል። ኢትዮጵያን ችግሮቿ ሁሉ የተቀረፉ ያህል ብዙዎች ተሰምቷቸዋል። ሆኖም አሁንም ኢትዮጵያ የጎን ውጋት የሆኗት ችግሮች አሉ። የወሰንና አስተዳደር ጥያቄዎች፣ የታጣቂ ኃይሎች እንቅስቃሴ፣ የምጣኔ ሀብት መዳከም፣ ማንነትን መሠረት ያደረጉ የተለያዩ ጥቃቶች አሁንም ይስተዋላሉ። እናም ኢትዮጵያ ችግሮቿን ቁልቁል ደርድራ አንድ በአንድ በማስተካከል፣ እንደ ሰሜኑ ጦርነት ሁሉ በኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል እና ጋምቤላ እንዲሁም በሌሎች ክልሎችም ሌሎቹንም ችግሮች እንድትቀርፍ ይጠበቅባታል። በሰብአዊ … [Read more...] about መፍትሔ የሚሹ የኢትዮጵያ የጎን ውጋቶች
የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ነው
"እናንተ የመለስናችሁ ለእረፍት እንጂ ጥያቂያችን መቋጫ አግኝቶ ትግል ስላበቃ አይደለም ። የወልቃይት-ጠገዴ ነፍጥ ገና ይጠብቃል እንጂ አይወርድም። እኔ በዚህ እድሜዬ ጋቢ ለብሼ ከዘራ ይዤ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ነበር የሚያምርብኝ። ነገር ግን አሁንም በዚህ እድሜዬ ጠበንጃ ተሸክሜ የምታዩኝ የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ስለሆነ ነው። ጥያቄው እልባት ሲያገኝ እናንተም በሙሉ ልብ ወደ ልማታችሁ እኔም ገዘራ ይዤ ጋቢ ለብሸ የምሄድ ይሆናል"ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱየወ/ጠ/ሰ/ሁ/ዞን ም/አስተዳዳሪና ሰላምና ደህንነት ሃላፊ "የወልቃይት-ጠገዴ ህዝብ ሲኖርም በምክንያት ሲሞትም በምክንያት ነው። አሁን እየተዳደርን ያለነው በምንፈልገው የቤጌምድር አማራ ማንነት ነው። በዚህም እንቀጥላለን። በህግ ጥያቄ ያለው ካለ በህግ ይጠይቀን።በህዝብ ፍላጎት መሰረት እስከሆነ ድረስ አስተዳደራችንም ድሮም … [Read more...] about የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ነው
በፓርላማው ውሎ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሾች
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሰጡት ማብራሪያ ዋና ዋና ነጥቦች‼️ የምክር ቤት አባላቱ ፦- የስምምነቱ ሂደት እንደምታውና ፋይዳው ምንድነው ?- በጦርነቱ የተጐዱ አካባቢዎችን ፍትሃዊ በሆነ መልኩ የመልሶ ለመገንባት ምን ዝግጅት ተደርጓል ?- አንዳንዶቹ ስምምነቱ ከTPLF እንጂ ከTDF ጋር አይደለም ? ... ወዘተ የሚሉ የተለያዩ ሃሳቦችን እየሠነዘሩ ይገኛሉ ፤ የእነኚህ አካላት ፍላጎት ምንድን ነው ? ውሳኔዎችንስ ተግባራዊ ለማድረግ እነቅፋት አይሆንም ወይ?- የምክክር ኮሚሽን የእስካሁኑ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ እንዲሁም በውይይት ሂደቱ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ምቹ ሁኔታዎችና ስጋቶች ምንድን ናቸው?- ውይይቱ ተሳክቶ መላው የሀገራችን ሕዝቦች ወደ ሚናፍቁት ልማት ፊታቸውን እንዲያዞሩ ከባለድርሻ አካላት ማለትም ከምሁራ፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ወጣቶችና ከመላው … [Read more...] about በፓርላማው ውሎ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሾች
“ወልቃይቴ፤ ወልቃይቴ ነው፤ ይታወቃል” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
በዛሬው የፓርላማ ውሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ስለ ወልቃይት የተናገሩት፤ “ወልቃይትን በሚመለከት የሚነገሩ ሽረባዎች፣ ሴራዎች፣ conspiracies ብዙ እሰማለሁ። የኢትዮጵያ መንግስት በእነዚህ ሽረባዎች ውስጥ እጁ የለበትም። የወልቃይት ህዝብ እንዲገነዘብ የምንፈልገው፤ የሚወራው፣ የሚናፈሰው አሉባልታ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት እጁ የለበትም።” “እኛ ደቡብ አፍሪካ የሄድንው ወልቃይት ወደ አማራ ይሁን ወደ ትግራይ ይሁን የሚለውን ለመወሰን አይደለም። የፕሪቶሪያው ‘ሰሚትም’ ይኸን ለመወሰን ስልጣን የለውም። ምን አገባው እና ነው የኢትዮጵያን መሬት እዚያ ሂድ እዚህ ሂድ የሚለው? እኛ እዚያ የሄድንው እንዴት ሰላም አምጥተን በንግግር ችግሮቻችንን እንፍታ ለማለት ነው። ለምን ወልቃይት ተስቦ እዚያ ውስጥ እንደሚገባ አላውቅም።” “ወልቃይት ብቻ አይደለም፤ ሰሜን ሸዋ ላይ ኦሮሚያ … [Read more...] about “ወልቃይቴ፤ ወልቃይቴ ነው፤ ይታወቃል” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
“(ላለፉት 4 ዓመታት) ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ” ወ/ሮ መዓዛ
የመንግሥት ሥራ አስፈጻሚ አካል የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ ማክበር ካልቻለ ሥርዓት ተሰብሯል ማለት እንደሆነ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ተናገሩ። ላለፉት አራት ዓመታት ሪፖርት ሊያቀርቡ ባለመቻላቸው አፈጉባዔውን ወቅሰዋል። ፕሬዚዳንቷ ይህን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ፣ እንዲሁም የሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ ክንውን ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በገመገመበት ወቅት ነው። ምክር ቤቱ ባካሄደው የአንድ ቀን የፍርድ ቤቶች ግምገማ ከምክር ቤት አባላትና ከሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች፣ ፍርድ ቤት ከወሰነላቸው በኋላ ውሳኔ የማይከበርላቸውን አካላት በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበዋል። የሕግ … [Read more...] about “(ላለፉት 4 ዓመታት) ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ” ወ/ሮ መዓዛ
ትጥቅ ማስፈታቱ ተግባራዊ መሆን ጀመረ፣ ክልሉም ስምምነቱን በይፋ ተቀበለ
አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን እደግፋለሁ አለች ረቡዕ ይፋ በሆነው የፕሪቶርያ ስምምነት መሰረት የትጥቅ ማስፈታቱ ሥራ መጀመሩ ታወቀ። በቅርቡ የሽግግር አስተዳደር የሚቋቋምለት የትግራይ ክልል ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤትም ስምምነቱን መቀበሉን በይፋ አረጋግጦ መግለጫ አሰራጨ። “… ይህ ስምምነት በተፈረመ በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ የሁለቱ ወገኖች ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተገናኝተው ይነጋገራሉ” በሚለው ግልጽና በፊርማ የጸደቀ ውል መሰረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ኢታማዦር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና የትህነግ ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት አዛዥ የሚባሉት ታደሰ ወረደ በዛሬው ዕለት ተገናኝተው መናገራቸውን ኢ.ኤም.ኤስ. የተሰኘው የእነ ሲሳይ አጌና ሚዲያ ቀድሞ ቢገልጽም የኢትዮ 12 የአዲስ አበባ ዘጋቢ የዜናውን ትክክለኛነት ማረጋገጡን ገልጿል። የትህነግ ጦር ሌላ አዛዥ የሆኑት ባለሃብቱ ጻድቃንና … [Read more...] about ትጥቅ ማስፈታቱ ተግባራዊ መሆን ጀመረ፣ ክልሉም ስምምነቱን በይፋ ተቀበለ
ስምምነቱን በማይቀበሉ ወይም ዕንቅፋት በሚፈጥሩ ላይ አሜሪካ ዕርምጃ ትወስዳለች
በተጀመረ በአስረኛው ቀን ይፋ የሆነውን የሰላሙን ስምምነት ማክበር ለአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እንደሆነ በተለያዩ ኃላፊነት ላይ ያሉ ባለሥልጣኖች ቢናገሩም፣ ስምምነቱ ከመፈረሙ ከቀናት በፊት የስምምነቱን ውጤት በተመለከተ አሜሪካ አስቀድማ ውጤት አመላካች የሆነ ማስጠንቀቂያዋ ከወትሮው የከረረ ነበር። ይኸው ማስጠንቀቂያ ዛሬ የተገላቢጦሽ የሚሠራ መሆኑ ደግሞ ዜናውን ትኩስ አድርጎታል። ለትህነግ ያላትን ወገንተኝነት ያለ ኃፍረት በዓለምአቀፍ መድረኮች ስታስተጋባና አጀንዳ እየተከለች ኢትዮጵያ ላይ ጫናዋን ስታበረታ የነበረችው አሜሪካ፣ የሰላሙ ንግግር ከመጀመሩ ቀናት በፊት ውጤቱን አስመልክታ ያወጣቸውን መግለጫ ወይም አቋም ቁጣ ቀላቅለው ያስታወቁት በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ነበሩ። ከትህነግ ጋር ቤተሰባዊ ግንኙነት እንዳላቸው በሥፋት በፎቶ … [Read more...] about ስምምነቱን በማይቀበሉ ወይም ዕንቅፋት በሚፈጥሩ ላይ አሜሪካ ዕርምጃ ትወስዳለች
የፕሪቶሪያው ስምምነት ትርጉም 360 ለዞረባችሁ
በመጀመሪያ ደረጃ መተማመን ያለብህ በራስህ አቅም ነው። አቅም አልባ ከሆንክ ማንም የማይፈልግህ ውዳቂ ትሆናለህ። የራስህን አቅም በሚገባ ከገመገምክ በኋላ ማን ነው አጋሬ ወደሚለው ትዞራለህ። አጋርህ ከጠላትህ እና ከአንተ ጋር ያለውን መስተጋብር ትገመግማለህ። አጋርህ ከጠላትህ ይልቅ አንተን ለምን እንደመረጠ አንተም ለምን እንደመረጥከው በተጨባጭ መረጃ ላይ ተንተርሰህ መገምገም የአንተ ድርሻ ነው። አንተም ለምን አጋርህ እንዳደረከው ማወቅ ይኖርብሃል። ታማኝ አጋር እንደምትሻ ሁሉ ለአጋርህ ታማኝ መሆንም የግድ ነው። እዚህም እዚያም የምትዘል ከሆነ ለአጋርነት አትመጥንም ብሎ ሜዳ ላይ ያሰጣሃል አንዳንዴ የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው የሚለው ብሂል ገዥ ነው። ዘላቂ ጠላትም ሆነ ዘላቂ ወዳጅ እንደሌለ ተረድተህ ግምገማህን በየጊዜው መተንተን ግን ከአንተ የሚጠበቅ ነው። ያልተተነተነ ፖለቲካ … [Read more...] about የፕሪቶሪያው ስምምነት ትርጉም 360 ለዞረባችሁ
ጥቅምት 24 “የክህደት ቀን” ተብሎ በግንቦት 20 መቃብር ላይ ይተከልልን!
በራሳቸው ሕዝብ ላይ ሲደርስ ሰማይ የሚደፋባቸውና ዓለም ሁሉ አብሯቸው እንዲያለቅስ የሚፈልጉት ምዕራባውያን በሌሎች ላይ ለሚደርሰው ሰቆቃ ቅንጣት ታህል ግድ አይላቸውም። አንድ ማሳያ እንጥቀስ፤ የዛሬ 80 ዓመት አካባቢ ጃፓን የአሜሪካንን ድንበር ጥሳ ከሐዋይ ደሴቶች አንደኛዋ ላይ የሚገኘውን ወታደራዊውን የፐርል ወደብ ገና በጠዋቱ በድንገት አጠቃች፤ በወደቡ ላይ የነበሩት 8 መርከቦች ጉዳት ደረሰባቸው፤ አራቱ ሰጠሙ፤ በአጠቃላይ ወደ 20 የሚደርሱ መርከቦችና ጀልባዎች ከጥቅም ውጪ ሆኑ፤ ከ300 በላይ የሚሆኑ አውሮፕላኖች፣ ጀቶችና ሔሊኮፕተሮች ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባቸው፤ ከሁሉ በላይ ከ2,400 በላይ የሚሆኑ ባሕረኞች፣ ወታደሮችና ሰላማዊ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ፤ ከ1,000 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆሰሉ። በቀጣዩ ቀን ዲሴምበር 8፣ 1941 የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት … [Read more...] about ጥቅምት 24 “የክህደት ቀን” ተብሎ በግንቦት 20 መቃብር ላይ ይተከልልን!