• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ትጥቅ ማስፈታቱ ተግባራዊ መሆን ጀመረ፣ ክልሉም ስምምነቱን በይፋ ተቀበለ

November 4, 2022 04:56 pm by Editor 1 Comment

አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን እደግፋለሁ አለች

ረቡዕ ይፋ በሆነው የፕሪቶርያ ስምምነት መሰረት የትጥቅ ማስፈታቱ ሥራ መጀመሩ ታወቀ። በቅርቡ የሽግግር አስተዳደር የሚቋቋምለት የትግራይ ክልል ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤትም ስምምነቱን መቀበሉን በይፋ አረጋግጦ መግለጫ አሰራጨ።

“… ይህ ስምምነት በተፈረመ በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ የሁለቱ ወገኖች ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ተገናኝተው ይነጋገራሉ” በሚለው ግልጽና በፊርማ የጸደቀ ውል መሰረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ኢታማዦር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና የትህነግ ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት አዛዥ የሚባሉት ታደሰ ወረደ በዛሬው ዕለት ተገናኝተው መናገራቸውን ኢ.ኤም.ኤስ. የተሰኘው የእነ ሲሳይ አጌና ሚዲያ ቀድሞ ቢገልጽም የኢትዮ 12 የአዲስ አበባ ዘጋቢ የዜናውን ትክክለኛነት ማረጋገጡን ገልጿል። የትህነግ ጦር ሌላ አዛዥ የሆኑት ባለሃብቱ ጻድቃንና ሌሎች የትህነግ ሰዎች በንግግሩ አዲስ አበባ ሆነው ተሳትፈዋል።

ይህ የሆነው እነ ዘ-ጸዓትን ጨምሮ በርካቶች የሰላም ስምምነቱ በተገለጸው መሰረት መፈረሙ ”ክህደት ነው” በሚል በሥፋት እየገለጹ ባለበት ወቅት ነው። በግልጽ ቋንቋ የትህነግ ደጋፊዎች ሳይቀሩ የስምምነቱን ይዘት ሳይወዱ አምነው በተቀበሉበት ወቅት ስምምነቱን ከግል ስሜትና ፍላጎት፣ እንዲሁም “ለምን ስልጣን አልያዝኩም” ከሚል ቁጣና ቂም በመነሳት እያጣመሙ ለማቅረብ የሚሞክሩ ቢኖሩም ተግባራዊነቱ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት እስካሁን ሳይዛነፍ እየተከናወነ መሆኑንን መረጃዎች ሊካድና ሊሸፋፈን በማይቻልበት ሁኔታ እያረጋገጡ ነው።

”ትህነግ ትጥቅ አይፈታም፣ የትጥቅ መፍታቱ ሂደትም ብዙ ጊዜ የሚፈጅ ነው። ዝርዝር ስምምነቱ ገና አልተፈረመም” በሚል ሰላም ለጠማው ህዝብ ሌላ የጦርነት ድግስና የእልቂት ከበሮ እየመቱ ላሉት መልስ ይሆን ዘንዳ ቢቢሲ ዘግይቶም ቢሆን በዝርዝር አፈጻጸሙ ላይ ፊርማ መቅመጡን ሮይተርስ ጉዳዩን ሲያከናውኑ ከነበሩት እንዳረጋገጠ ዘግቧል።

ራሱን “የትግራይ መንግሥት” በሚል ስያሜ ሲጠራ የከረመርው ትህነግ ስሙንና መለያውን አስተካክሎ “ስምምነቱን ተቀብያለሁ” ሲል በገሃድ አስታውቋል። ይህም መግለጫ የስምምነቱ አካል እንደሆነ ታውቋል። ገና ተጨማሪ መግለጫዎችና የተግባር ውሳኔዎች እንደሚከታተሉ ስምምነቱን ጠቅሰው ያስታወቁ ”በመሬት ላይ ያለውን እውነታ አለመቀበል፤ ተራ መወተርተር ካልሆነ የሚያመጣው ለውጥ የለም” ብለዋል።

ትህነግ ለህግ፣ ለህገመንግሥት መከበርና የበላይነት ሲል ወደ ጦርነት መግባቱን የደጋፊዎቹን ስሜት በሚጠብቁ ቃላቶች አዋዝቶ የተደረሰበትን ውሳኔ እንደሚቀበል ማስታወቁ

  • በስምምነቱ መሰረት ትጥቅ እፈታለሁ
  • ይህንኑም በ24 ሰዓት ውስጥ ተግባራዊ አደርጋለሁ
  • ፈርሼ የፌደራል መንግሥት ለሚያቋቁመው ህጋዊ የሽግግር አስተዳደር ወንበሬን እሰጣለሁ (ሊካተትም ይችላል)
  • ሁለተኛ በሽብር ዙሪያ አልገኝም
  • ወረራ በመፈጸም አልተኩስም
  • ኢትዮጵያ ላይ እንዲተኩሱ አላደራጅም፣ አልረዳም፣ አላስታጥቅም
  • መንግሥትን ዘልዬ የውጭ ግንኙነት አላደርግም
  • የክልል አስተዳደር መሆኔን አምኛለሁ
  • በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል ውስጥ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አማፂ ቡድኖችን አልደግፍም
  • ሁለተኛ ለሽብርና አመጽ ተግባር ምልመላ ሥልጠና አላደርግም
  • በተቀመጠው ቀነ ገደብ የፌደራል መንግሥት መቀሌን እንዲቆጣጠር አመቻቻለሁ
  • በጥቅሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መቶ በመቶ ለኢትዮጵያ ተወስኗል ያሏዋቸውን ነጥቦች አንድ በአንድ ይተገብራል። ይቀጥላል …

በተመሳሳይ መንግሥትም የተቋረጡ አገልግሎቶችን ከማስጀመር አንስቶ በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋምና የማደስ፣ ሕዝብ በፍጥነት ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴው እንዲመለስ በውሉ ከተቀመጠው ባለፈ መንግሥታዊ ሃላፊነቱን እንደሚወጣ፣ ሪፎርሙ በደንብ እንዳይካሄድ ማነቆ የሆኑትን ጉዳዮች በማስወገድ ሪፎርሙን ማጠናከር፣ ለሰላም ማበልጸግ ይረዳሉ የሚባሉ ጉዳዮችን ማከናወንና ድንበርን የመጠበቅ ሃላፊነቱን ይወጣል። ተረጂዎች በተሳካ ሁኔታ በቀጥታ እርዳታ እንዲደርሳቸው ይሰራል።

አሜሪካ “ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወይም ሞት” መሰል ድጋፏን ሰጠች 

ስምምነቱን ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለተገባራዊነቱ አስፈላጊውን ሁሉ መንግሥታቸው እንደሚያከናውን፣ ይህንንም ከልብ እንደሚያደርገው መግለጻቸውን ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ”ከጎንዎት ነን” ሲል መግለጫ ማውጣቱን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።

  • ስምምነቱን በማይቀበሉ ወይም ዕንቅፋት በሚፈጥሩ ላይ አሜሪካ ዕርምጃ ትወስዳለች

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያቤትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አንቶኒ ብሊንከን እስትንፋስ ሁሉ የግንባር ዜናቸው የሚያደርጉት በኢትዮጵያዊያን የሚመሩ ሚዲያ አውታሮች ዜናውን ዝም ብለውታል። “በክህደትና በባንዳነት ታሪክ የዘገባቸው አብዛኞቹ የውጭ ሚዲያ ተቀጣሪዎች የተሰማሩበት የክህደት ዘመቻ በመንጠፉ ከገቡበት ኮማ እስከሚነቁ ይህ የሚጠበቅ ነው” ሲሉ አስተያየት የሰጡ አሉ።

ጫና ስታሳድር የነበረችው አሜሪካ ”ሁሉንም አድርጌ ሞክሪአያለሁ አልተሳካም። ህዝቡ አገሩን ይወዳል። ከዚህ በላይ ጫና ማድረግ አንችልም” ስትል ድርድሩ ከመጀመሩ በፊት ለትህነግ ሰዎች መንገሯን ኢትዮ12 መዘገቧ ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    November 6, 2022 05:39 pm at 5:39 pm

    Held at a Distance: My Rediscovery of Ethiopia በተሰኘው መጽሃፏ ላይ Rebecca G. Haile እንዲህ ትለናለች። የተረዳሁት በአማርኛ ተናጋሪ ሰዎች ላይ ያለውን ጥላቻ ነው። ላሊበላ ላይ ወደ ሱቅ ቀረብ ብዬ የታሸገ ውሃ በአማርኛ በመጠየቄ ከጎኔ ያለው/ችው ሰው ከከፈሉት በላይ 50% አስከፈሉኝ ትላለች። ይህ ቀኑ ለሚያሮጠው የቀን ጅብ ምንም መስሎ ላይታየው ይቻላል። ልብ ላለ ግን የወያኔን ክፋትና ክርፋት የሚያሳይ አንድ መመዘኛ ነው። አሁን የሰላሙ ፊርሚያ ያ ሁሉ ሰውና ንብረት ከወደመ በህዋላ ለይስሙላም ቢሆን መፈረሙ እስኪ እንየው ያሰኛል እንጂ ጮቤ አያስረግጥም። እብድ ቤቱን አቃጥሎ ለምን ሲባል ለትኋኑ እንደሚለው አይነት ነው አሁን እየሆነ ያለው ነገር። ወያኔን የሚፋረደው እውነተኛ ኢትዮጵያዊያንና ኢትዪጵያዊት ይሁን እንጂ ቀዳሚዎቹ ተፋራጆች ልጆቻችሁን አምጡ እየተባሉ ልጅ አልባ የቀሩት የትግራይ እናትና አባት ናቸው። አረመኔው ወያኔ ለሰው ህይወት ደንታ የለውም። በረሃ እያለ የፓለቲካ አዝማሚያቸውን የሞገቱ የትግራይ ልጆች በይፋ ተረሽነዋል፤ ከደርግ ጋር ውጊያ ሲያደርጉ ከህዋላ ተተኩሶ ተገድለዋል፤ ተይዘው ተዘቃይተውም ከእነ ህይወታቸው ተቀብረዋል። የድርጅት ሚስጢር አይወጣም በሚል የጅል ስሌት ብዙዎች የሚያውቁትን እውነት ለህዝባችን ሳያካፍሉና ለታሪክ ሳይተው እነርሱም አፈር ሆነዋል። የወያኔ የአማራ ጥላቻ አጥንቱ ውስጥ የገባ በውሸት የተለወሰ የማይድን በሽታ ነው። በምንም ሂሳብ ወያኔ ቆሞ እየሄደ የአማራ ህዝብ ከትግራይ ህዝብ ጋር በሰላም መኖር አይችልም። በሁለቱ ህዝቦች መካከል ሰላም እንዳይኖር ወያኔ በስውርም ሆነ በይፋ ሌት ተቀን ይሰራሉና።
    በ 27 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው ዞር ብለው ያላዪትን የትግራይ ህዝብ ዞረው ተገን በማድረግ ይኸው እንሆ ሃገር ምድሩን አተራምሰው አሁን ደግሞ በቃኝ በማለት ፊርማቸውን አስቀምጠዋል። ሲጀመር ወያኔና ወያኔ ቀመስ ድርጅቶች ከእውነት ጋር ተዛምዶ የመኖር ልምድም ፍላጎቱም የላቸውም። አንዴ በድንበር፤ ሌላ ጊዜ እኩልነት ገለ መሌ እያሉ ደም ሲያፈሱና የእነርሱም ሲፈስ እንዲኖር ነው የሚፈልጉት። ጥላቸው ልክ እንደ ጠባብ ብሄርተኞቹ ኦሮሞዎች ከኢትዪጵያ ጋር ነው። ኢትዮጵያዊነትን አምርረው ይጠላሉ። ለዚህም ነው ጌታቸው ረዳ ሲኦል ድረስ ወርደን ቢሆን ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን ያለው። ገና ከጅምሩ ትግራይን እገነጥላለሁ ብሎ የተነሳው ያ የወያኔ ፈረስ ከተሜ ሆኖ ሚኒሊክ ቤ/መንግስት ማደር ሲጀመር ነው የመገንጠል ጥያቄውን ያረገበው እንጂ ለዘመናት ለመገንጠል የሰሩና የሚሰሩ ጉዶች ናቸው። ትጥቅ ማስፈታቱ የቱ ቦታ ምን ሰአት እንደተጀመረ አላውቅም። ግን ሞትና ረሃብ የጠበሰው የትግራይ፤ የአማራና የአፋር ህዝብ የሰላሙን ጥሪ በደስታ እንደሚቀበል የታወቀ ነው። ግን በጥባጭ እያለ ማን ጥሩ ይጠጣል። ወያኔዎች ከምድሪቱ እስካልጠፉ ድረስ በምንም ሂሳብ ሰላም በእነዚህ ክልሎች ውስጥ አይኖርም። እነዚህ እብዶች እኮ በጉልበት የሰሜን እዝን አጥቅተው “መብረቃዊ ጥቃት” በማድረስ ሁሉን ተቆጣጥረናል ያሉን ጉዶች ናቸው። አሁን ታዲያ አንተም ጉንድሽ እኔም ጉንድሽ ሲሆን ነገሩ ትሩፋቱ የቱ ላይ ነው? በ 48 ዓመት ጊዜአቸው የዘሩት የጥላቻ ፓለቲካ ከደቂቅ እስከ ሊቅ አሳብዶ በሃገሯ በምድሯ ላይ አማርኛ ቋንቋ ውሃ በመጠየቋ እሷ ለውሃው 50% ጭማሬ ስትከፍል ነጮቹ ደግሞ በቅናሽ ገዝተውታል። እብደት ይሄ ነው። ጥላቻ እንዲህ ነው። ሌላም ነገር ደራሲዋ ትጠቅሳለችና መጽሃፉን እንድታነቡት እመክራለሁ። ሚዛናዊ ያለሆነ አለም ላይ ፍትህን መጠየቅ ራስን ለመከራና ለእንግልት አሳልፎ መስጠት ነው። ድሮ ድሮ ሰው ሰው እያለ በተገጠመ አንድ ግጥም ሃሳቤን ልዝጋ።
    ቦሩ ስላሴ ላይ ብርቱካን አፍርቶ
    የሩቅ ለቅሞት ሄደ የቅርቡ ተቀምጦ።
    መቼ ይሆን የምንማረውና የራስን የምናከብረው። ወገኔ ወንድሜ፤ እህቴ፤ እናቴ፤ አባቴ ብለን የምንተዛዘነው? ያ ቀን ይመጣ ይሆን ወይስ በክልል፤ በሃይማኖት፤ ወንዝ በማያሻግር የቋንቋ ሰንሰልት ታስረን አሳደን ስንሳደድ ዝንተ ዓለም እንኖር? በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule