• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስምምነቱን በማይቀበሉ ወይም ዕንቅፋት በሚፈጥሩ ላይ አሜሪካ ዕርምጃ ትወስዳለች

November 4, 2022 04:55 pm by Editor 1 Comment

በተጀመረ በአስረኛው ቀን ይፋ የሆነውን የሰላሙን ስምምነት ማክበር ለአሜሪካ ቀዳሚ አጀንዳ እንደሆነ በተለያዩ ኃላፊነት ላይ ያሉ ባለሥልጣኖች ቢናገሩም፣ ስምምነቱ ከመፈረሙ ከቀናት በፊት የስምምነቱን ውጤት በተመለከተ አሜሪካ አስቀድማ ውጤት አመላካች የሆነ ማስጠንቀቂያዋ ከወትሮው የከረረ ነበር። ይኸው ማስጠንቀቂያ ዛሬ የተገላቢጦሽ የሚሠራ መሆኑ ደግሞ ዜናውን ትኩስ አድርጎታል። 

ለትህነግ ያላትን ወገንተኝነት ያለ ኃፍረት በዓለምአቀፍ መድረኮች ስታስተጋባና አጀንዳ እየተከለች ኢትዮጵያ ላይ ጫናዋን ስታበረታ የነበረችው አሜሪካ፣ የሰላሙ ንግግር ከመጀመሩ ቀናት በፊት ውጤቱን አስመልክታ ያወጣቸውን መግለጫ ወይም አቋም ቁጣ ቀላቅለው ያስታወቁት በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ ነበሩ።

ከትህነግ ጋር ቤተሰባዊ ግንኙነት እንዳላቸው በሥፋት በፎቶ ማስረጃዎች የሚቀርብባቸው ሊንዳ ቶማስ-ግሪንፊልድ የአገራቸውን አቋም ይፋ ያደረጉት የሰላሙ ንግግር ሰኞ ሊጀመር አርብ ኦክቶበር ፳፩ ቀን የጸጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ላይ ለመወሰን ስብሰባ ጠርቶ በነበረበት ወቅት ነው። ስብሰባው ያለአንዳች ውጤት መበተኑ የሚታወስ ነው።

ስብሰባው ትህነግ፣ ደጋፊዎቹ፣ አንጋሾቹ ምዕራባውያን፣ ወዘተ በተስፋ የጠበቁትና የኢትዮጵያን እጅ የሚጠመዝዝ ውሳኔ ይተላለፍበታል የተባለ የመጨረሻው ተስፋቸው ነበር። ስብሰባው እንደተጠበቀው ሳይሆን ያለ አንዳች ውሳኔ በመጠናቀቁ ሐዘን ውስጥ የገቡትን ወዳጆቻቸውን የሚያጽጽና መልዕክት ይዘው የወጡት አምባሳደር ሊንዳ በወቅቱም እንዲህ ነበር ያሉት፤

“አጭር ነገር ልናገር ነው የወጣሁት፤ የሰላሙን ንግግር በተመለከተ ከአፍሪካ ኅብረት መግለጫና ማብራሪያ ተሰጥቶናል፤ የጸጥታው ምክር ቤት ስለ ጉዳዩ አንድ ወጥ መግለጫ ለማውጣት ስምምነት ላይ አለመድረሱ አሳዛኝ ነው፤ ስለዚህ ነው እኔ አሁን እዚህ ብቅ ብዬ መናገሬ አስፈላጊ የሆነው” ካሉ በኋላ ኢትዮጵያን የሚወቅስ እና ጥፋተኛ የሚያደርግ ፣ ነገር ግን በዲፕሎማሲያዊ ቃላት የታጀበ ዲስኩር አሰሙ። “ተኩስ አቁም ከተደረገ በኋላ” አሉ ሊንዳ፤ ሲቀጥሉም “የወደፊቱን ጉዳይ ቀስ ብለው ሁለቱ ወገኖች ሊነጋገሩ ይችላሉ፤ መጠነ ሰፊ የፖለቲካ ንግግር፣ የሰላምና መረጋጋት፣ ያልተገደበ የሰብዓዊ ዕርዳታና የተቋረጡ አገልግሎቶችን የመመለስ ጉዳይ በቀጣይ የሚከናወን ይሆናል” በማለት የሚፈለገውን ዘረዘሩ። ይሁን እንጂ ስለ ትህነግ ትጥቅ መፍታትም ሆነ ኢትዮጵያ ሉዓላዊትና የግዛት አንድነቷ የተጠበቀ አገር ስለመሆኗ ወይም ለአንድ አገር ይህንን ማስከበር ወሳኝ መሆኑን ሳይጠቅሱ አለፉ።

አምባሳደሯ ሲቋጩ “የአፍሪካ ኅብረትን ለመደገፍ አሜሪካ ሙሉ በሙሉና በትጋት በማንኛውም የዲፕሎማሲያዊ ተግባራት መስክ በከፍተኛ ደረጃ እንደምትደግፍ ለመናገር እፈልጋለሁ። ሆኖም የዚህ ግጭት ውሳኔ ውጤት ለማጨናገፍ በሚፈልጉ ወይም ስምምነቱ ላይ ዕንቅፋት በሚፈጥሩ ወገኖች አሜሪካ ዕርምጃ የምትወስድ ሲሆን፣ ሰብዓዊ መብቶችን የጣሱ ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ በማድረግ በኩል ያለንን ቁርጠኝነት ለመናገር እወዳለሁ” ሲሉ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂ የተቀላቀለበት ዛቻቸውን አሰሙ።

እንደ እውነቱ ከሆነ በፕሪቶሪያው ስምምነት ደስተኛ ያልሆነውም ሆነ ህጻናትን ለጦርነት ከማሰለፍ ጀምሮ እጅግ ዘግናኝ የሰብዓዊ መብቶችን ሲጥስ የኖረው አካል ማን እንደሆነ ሊንዳ፣ አገራቸው፣ የተሰበሰቡበት ድርጅት፣ ዓለምና መላው ህብረተሰቧ የሚያውቁት ቢሆንም ማስፈራሪያው በጅምላ ነበር።

ምንም እንኳን የዲፕሎማቷ ንግግር ኢትዮጵያን ለመደገፍ ታስቦ የተነገረ ባይሆንም በመንግሥት ባለሥልጣንነት ለተናገሩት አሜሪካ ቃሏን እንደምትጠብቅና በርግጥም ይህንን የሰላም ስምምነት ለማክሸፍ በሚሞክሩ በአገሯ ከሚገኙ የትህነግ አክቲቪስትና ሌሎች ተከፋዮች ጀምሮ በቅርቡ እርምጃ መውሰድ እንድትጀምር ግፊት ሊደረግ እንደሚገባ እየተጠቆመ ነው።

ለዚህም ተግባራዊነት ይረዳ ዘንድ የስምምነቱን አውድ በማሳየት ላይ ሌት ተቀን የተዛባና ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጫርስ መረጃ የሚረጩ ክፍሎች እነማን እንደሆኑ፣ የሚሰጡት መረጃ ደግሞ በማስረጃ እየተሰበሰበ እንደሆነ ይህም የፕሪቶሪያው ስምምነት አንዱ አካል እንደሆነ ጎልጉል ከዲፕሎማቲክ ምንጮቹ ለመረዳት ችሏል። ጉዳዩን በአፍሪካ ኅብረት በኩል አስፈላጊ ለሆኑ ወገኖች እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል።  

ከስምምነቱ በኋላ በርካታ አገሮች አድናቆታቸውን ቢሰጡም በዋናነት ግን አሜሪካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ሰላሙን ለማጽናትና የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑንን ይፋ ማድረጋቸውን እንደሚደግፉና ማናቸውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን አመልክታለች።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    November 4, 2022 07:33 pm at 7:33 pm

    አንድ የውጭ ሃገር የቀድሞ የስለላ መረብ ባለሙያ ስለ ስምምነቱ ሲናገር እንዲህ ብሏል። ” የጦርነቱ መቆም የሚጠቅመው ሁሉን ነው። በዚህ ጦርነት ላይ አፈንጋጮች ቢኖሩ እብዶችና ከሩቅ ድንጋይ የሚያቀብሉ ብቻ ይሆናሉ”። አክሎ ሲናገርም ወያኔ በሶስት ጊዜ ወረራው ያለ ቅጥ ሰራዊቱን በማጣቱና የአሜሪካም የተቀዛቀዘ ድጋፍ በጠረጴዛ ዙሪያ ለሰላም እንዲቀመጥ አድርጎታል በማለት ነገሩን ይዘጋል። ጄ/ጻድቃን “ጦርነቱ አልቋል አሁን ከማን ጋር ነው ስለ ሰላም የምንነጋገረው” ባለበት አንደበቱ ስለ ሰላም ቁጭ እንዲል ያደረገው የጦር ሜዳ ላይ ሽንፈቱ ነው። እንግዲህ ወያኔ ተሸነፈ፤ የኢትዮጵያ ጥምር ሃሎች አሸነፉ አሸሸ ገዳየው የሚያሰኝ ነገር የለውም። ሲጀመር ነገሩ ሁሉ በእብደት ላይ የተመሰረተ ነበርና። አይን ያለው፤ ጀሮው የሚሰማ የሆነው ሁሉ ከአማኑኤል ሆስፒታል ያመለጠ በሽተኛ የማያስበውና የማያደርገው ጉዳይ እንደሆነ መገመት ይችላል። የወያኔው እብደት ግን የእብደት ቁንጮ ነውና ለዚህ በቃን። ግን ትዕቢት ውድቀትን የምትቀድመው ለዚህ ነው። አሁን የወያኔ ደጋፊዎች ሃዘን ላይ ተቀምጠዋል። መልካም ነው እነርሱ ያልቅሱ። ሃበሳውን የቆጠረው የትግራይ ህዝብ እፎይ ይበል። 48 ዓመት ሙሉ በአንድ ጨካኝ ድርጅት ሥር 1 ለ 5 በተባለ የአልባኒያ የፓለቲካ ስልት ተጠፍሮ አንዴ ሃገር ልትሆን ነው ሲባል፤ ሌላ ጊዜ ኤርትራ ልትውጥህ ነው ሲሉት፤ ሲሊላቸው አማራ ሊያርድህ ሊዘርፍህ መጣብህ እያሉ ሲያታልሉት ይኸው እንሆ አውሬዎቹ ወያኔዎች ብቻ ሆነው ተገኙ። በአፋር፤ በአማራ ክልሎች የፈጸሙት ወንጀል ሰማይ ጠቀስ ነው። ሥራቸው ዲያብሎሳዊ ነውና።
    የተፈረመውን የሰላም ሰነድ ወደ ተግባር ለመለወጥ እንቅፋቶች ይኖራሉ። ይህ ደግሞ የሚጠበቅ ነው። ግን ያም ተግደረደረ ይህ መሞከሩ አይቀሬ ነው። አሜሪካ ገና ወያኔ የሰሜን ጦርን የዛሬ 2 ዓመት በፊት ሳያጠቃ ማስቆም ትችል ነበር። ግን በሴራው ነበሩበት። ለዚያ ነው ደጋግመው እንዲሞክሩ የገፏቸውና ይህ ሁሉ ህዝብ ከሁለቱም ወገን ያለቀው። ወያኔዎች ወደ ሽዋ ሲጠጉ ኤምባሲያቸውን ሁሉ እስከ መዝጋት የቀረቡት። የአሜሪካ ሴራ ብዙ ነው። ግን ስለ ዲሞክራሲ እየለፈለፉ በስመ ዲሞክራሲ ሃገርን ማፍረስ ሙሉ ሥራቸው ነው። ያኔ ወያኔ በሚኒሊክ ቤ/መንግስት እያለ ይሰራ የነበረውን ግፍ ሁሉ አፍንጫቸው ጥግ ሆነው እየተመለከቱ ምንም ትንፍሽ ያላሉት የሚጋልቡት ፈረስ አልጋለብም በሚል መሪ ሲተካ እንዲህ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ እስከ ጭንቅላታቸው መግባታቸው የሴራቸውን ክፋት ያሳያል። ያም ሆነ ይህ በሁለቱም ወገኖች ጉራ፤ ማስፈራራት፤ አሸነፍን ተሸነፍን መባባሉ ነገር ያባብሳል እንጂ ለማንም አይጠቅምም። ያለፈው የእብደት ጥፋት አሁን በሰላም ይተካ። ህዝባችን ያለችውን ቆሎ እንኳን ቆርጥሞ የጠበንጃ ድምጽ ሳይሰማ ይኑር። አሁንም ፍልሚያን እንደ መፍትሄ የሚመለከቱ ወገኖች ህመምተኞች ናቸው። ምድሪቱ በተውሶ መሳሪያ መታረሷ ይብቃ? አየሩን አንበክለው። አራዊቶችንና አዕዋፍን ሁሉ አንመርዝ። ማበዳችን በዚህ ይዘጋ። ኤርትራውያን በትግራይ ህዝብ ላይ ጭራሽ ጥላቻ የላቸውም። ያው ወያኔ እንደ ጭራቅ ማስፈራሪያ አድርጓቸው እንጂ። የኤርትራው መሪ እድሜው ከመሸ በህዋላ ሰላምን የሚፈልግና ነገሮችን የሚመዝን እየሆነ መጥቷል። ማን ያውቃል በኤርትራም በሰላም ዲሞክራሲያዊ ለውጥና ምርጫ ሊመጣ ይችላል። በአፈሙዝና በጦርነት የሚደረጉ ተግዳሮቶች ሁሉ አፍራሾች ናቸውና ከዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ራሳችን በማራቅ ለምሥራቅ አፍሪቃ ሰላምና ብልጽግና በህብረት እንስራ። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule