በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የቃብትያ ሁመራ ወረዳና የዞኑ “የተከዜ ዘብ” በባለፉት ሳምንታት ሲሰለጥኑ የቆዩትን ሰልጣኞች በዛሬ ቀን በዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ፣ የወልቃይት ጠገዴ አማራ የማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ጀግናው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት ተመርቀዋል። ወልቃይት ጠገዴ የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት መጠበቂያ መሠረት ናት። ከጥንት እስከ ዛሬ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስከበር አያሌ መስዋዕትነት ተከፍሏል። በተከፈለው መስዋዕትነትም የሀገር ሉዓላዊነት ከነክብሩ ኖሯል። ኢትዮጵያውያን ለነፃነታቸው እና ለሉዓላዊነታቸው በአንድነት እና በኅብረት እየተነሱ ጠላታቸውን ድል ሲመቱ ኖረዋል። ድል ማድረግ የኢትዮጵያውያን የሥነ-ልቦና እና የባህሪ … [Read more...] about የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ
demeke zewdu
“ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ
የግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ ሴራ እና ተንኮል መጋለጫ፣ የሩብ ምዕተ ዓመት አምባገነናዊ አገዛዝ መሸኛ፣ የሦስት አስርት ዓመታት የጨለማ ጉዞ ምዕራፍ መቋጫ እና የአዲሱ ትውልድ የነጻነት አደራ ርክክብ ትናንት በቅርቡ የተስተዋለ ክስተት ነበር፡፡ እልፎች ማንነታችን ይከበር ብለው አደባባይ ድረስ ዘልቀው በመውጣት የከበረ መስዋዕትነት ሲከፍሉ ከተፈጥሯዊ ነጻነት ባሻገር የጠየቋቸው እና ለትግል የሚያበቁ አያሌ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡ ማኀበረሰባዊ ማንነትን የሚያስቀጥል ትግል ደግሞ በትውልድ ቅብብሎሽ መካከል የሚጸና የነጻነት መርከብ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ለማንነት መከበር በሚደረግ ትግል ውስጥ ውስኖች እንደ አብሪ ኮከብ ጎልተው ቢታዩም የትግሉ ባለቤት እና ሞተር ግን ሕዝብ መኾኑ አይካድም፡፡ የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ ሕዝብ የዘመናት የነጻነት ትግል መልህቅ በታሪክ አጋጣሚ በአዲሱ … [Read more...] about “ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ
የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ነው
"እናንተ የመለስናችሁ ለእረፍት እንጂ ጥያቂያችን መቋጫ አግኝቶ ትግል ስላበቃ አይደለም ። የወልቃይት-ጠገዴ ነፍጥ ገና ይጠብቃል እንጂ አይወርድም። እኔ በዚህ እድሜዬ ጋቢ ለብሼ ከዘራ ይዤ ቤተክርስቲያን ሲሄድ ነበር የሚያምርብኝ። ነገር ግን አሁንም በዚህ እድሜዬ ጠበንጃ ተሸክሜ የምታዩኝ የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ስለሆነ ነው። ጥያቄው እልባት ሲያገኝ እናንተም በሙሉ ልብ ወደ ልማታችሁ እኔም ገዘራ ይዤ ጋቢ ለብሸ የምሄድ ይሆናል"ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱየወ/ጠ/ሰ/ሁ/ዞን ም/አስተዳዳሪና ሰላምና ደህንነት ሃላፊ "የወልቃይት-ጠገዴ ህዝብ ሲኖርም በምክንያት ሲሞትም በምክንያት ነው። አሁን እየተዳደርን ያለነው በምንፈልገው የቤጌምድር አማራ ማንነት ነው። በዚህም እንቀጥላለን። በህግ ጥያቄ ያለው ካለ በህግ ይጠይቀን።በህዝብ ፍላጎት መሰረት እስከሆነ ድረስ አስተዳደራችንም ድሮም … [Read more...] about የወልቃይት-ጠገዴ ትግል መቋጫው ገና ነው



