• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም” አንፈቅድም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

July 27, 2023 04:19 pm by Editor 2 Comments

የግማሽ ምዕተ ዓመት ገደማ ሴራ እና ተንኮል መጋለጫ፣ የሩብ ምዕተ ዓመት አምባገነናዊ አገዛዝ መሸኛ፣ የሦስት አስርት ዓመታት የጨለማ ጉዞ ምዕራፍ መቋጫ እና የአዲሱ ትውልድ የነጻነት አደራ ርክክብ ትናንት በቅርቡ የተስተዋለ ክስተት ነበር፡፡ እልፎች ማንነታችን ይከበር ብለው አደባባይ ድረስ ዘልቀው በመውጣት የከበረ መስዋዕትነት ሲከፍሉ ከተፈጥሯዊ ነጻነት ባሻገር የጠየቋቸው እና ለትግል የሚያበቁ አያሌ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡

ማኀበረሰባዊ ማንነትን የሚያስቀጥል ትግል ደግሞ በትውልድ ቅብብሎሽ መካከል የሚጸና የነጻነት መርከብ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ለማንነት መከበር በሚደረግ ትግል ውስጥ ውስኖች እንደ አብሪ ኮከብ ጎልተው ቢታዩም የትግሉ ባለቤት እና ሞተር ግን ሕዝብ መኾኑ አይካድም፡፡ የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት እና ራያ ሕዝብ የዘመናት የነጻነት ትግል መልህቅ በታሪክ አጋጣሚ በአዲሱ ትውልድ መዳፍ ውስጥ ገብቷል፡፡

የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በጀቱ የሕዝብ ቁጭት እና ብሶት ነው ያሉት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ናቸው፡፡ የወልቃይት ወረዳ በቅርቡ ያስገነባቸውን የተለያዩ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አጠናቆ አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነ-ሥርዓተ ላይ የተገኙት የዞኑ ምክትል አሥተዳዳሪ እና የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብን ለዘመናት ሞት፣ ስደት እና እንግልት ከዳረጉት የህወሐት ፖለቲካዊ ሸፍጦች መካከል አንዱ ፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት አለመኖር እንደነበር አንስተዋል፡፡

ለዘመናት በማንነቱ ምክንያት ፍትሐዊ ልማት ናፍቆት የኖረ ሕዝብ በጥረቱ የሠራውን የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በማየት ትናንት የበደሉን ሁሉ ሊሸልሙን እና ሊያመሰግኑን በተገባ ነበር ብለዋል፡፡

ወልቃይት ጠገዴ በርካታ የመልማት ጸጋዎች እና አቅሞች ያሉት አካባቢ ነው፡፡ ነገር ግን ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በህወሃት አምባገነናዊ የጭቆና አገዛዝ ውስጥ እንዲቆይ በመገደዱ ለከፋ ሰብዓዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና ማኀበራዊ ስብራቶች እንዲዳረግ አድርጎት እንደቆየ ኮሎኔል ደመቀ አንስተዋል፡፡ የወልቃይት ጠገዴ ሕዝብ በተለያዩ የትግል ስልቶች እና አማራጮች የተጫነበት የባዕድ ማንነት እንደማይገልጸው ተናግሯል፡፡ ነገር ግን የነበረው ሥርዓት ነባር ባለእርስቶችን አፈናቅሎ የእኔ ነው የሚለውን ማኀበረሰብ ማጽናት በመኾኑ የሕዝብን ጥያቄ በኃይል ለማፈን ብዙ እርቀት ተጉዞ ነበር፡፡

የወልቃት ወረዳ ማዕከል የኾነችው ወፍ አርግፍ ከተመሠረተች አያሌ ዓመታትን ብታስቆጥርም ይህ ነው የሚባል የመሠረተ ልማት ግንባታ የላትም፡፡ ኮሎኔል ደመቀ እንደሚሉት በከተማዋ መካከል አልፎ የሚሄደው የአስፓልት መንገድ የተሠራበት ዓላማ ግልጽ ቢኾንም ወፍ አርግፍን ሳይነካ እንዲያልፍ ለማድረግ የተሠራውን ሴራ ሕዝብ ያውቀዋል ብለዋል፡፡ በሕዝብ እምቢተኝነት መንገዱ በከተማዋ መካከል አልፎ እንዲሄድ ቢገደዱም፡፡ 

ኮሎኔል ደመቀ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብ የነበረውን መዋቅራዊ ሴራ በሚገባ ተረድቷል ነው ያሉት፡፡ “የማንንም ርስት አልፈን አልነካንም፤ ያስመለስነውም ለረጂም ጊዜ ታግለንና መስዋእትነት ከፍለን ማንነታችንን ነው” ብለዋል፡፡ የትግራይ ሕዝብ የወልቃይትን እውነት መመስከር እንዳለበትም ነው የተናገሩት፡፡

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብ እና አሥተዳደር አሁን በሙሉ አቅሙ ልማት ላይ ነው፡፡

“ከማንም ጋር ግጭት አንፈልግም በማንነታችን ላይ ግን ዳግም ለአፍታ እንኳን ተዘናግተን የተራዘመ መከራ እና ባርነት ለመቀበል ፍጹም የማንፈቅድ መኾኑን ሊታወቅ ይገባል” ብለዋል የሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኅላፊው፡፡

የትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር በሀገረ አሜሪካ ገብቶ የሚነዛውን የሃሰት ፕሮፖጋንዳ እየሰማን ነው ያሉት ኮሎኔል ደመቀ የትግራይ ሕዝብ በውሸት መመራት ይበቃኛል ማለት አለበት ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ የትግራይ መገናኛ ብዙኀኖች ሳይቀር የሚሰብኩትን እና የሚጎስሙትን የጦርነት ነጋሪት ሊገነዘበው እንደሚገባም ኮሎኔል ደመቀ ተናግረዋል፡፡

ህወሃት አካባቢውን የግጭት ቀጠና ለማድረግ የሚሠሩትን ዘርፈ ብዙ ሙከራ በሚገባ እናውቃለን ነው ያሉት ኮሎኔል ደመቀ። የተለየ ሃሳብ እና ፍላጎት ያለው ሁሉ ሃሳቡን አደባባይ አውጥቶ ይሞግት፤ ሃሳብ ያሸነፍል ወይም ይሸነፋል፡፡

ይሁን እንጅ ውስጥ ለውስጥ መሄድ እና የአካባቢውን ሕዝብ ዳግም የማያባራ ዋጋ ለማስከፈል የሚደረግ የትኛውም አይነት እንቅስቃሴ ተገቢነት የለውም ብለዋል፡፡ (አሚኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: demeke zewdu, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist, wolkayit

Reader Interactions

Comments

  1. Miherete Tibebe says

    August 1, 2023 08:55 am at 8:55 am

    WOW!!!!

    Reply
  2. Tesfa says

    August 3, 2023 02:25 pm at 2:25 pm

    እግዚአብሄር ለዚህች ዓለም ግድ የለውም – ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ። መልካም አባባል ነው። ዓለምን የሚሾፍሯት ጉልበተኞች ነው። በተለይ በሃበሻዋ ምድር ከትውልድ ትውልድ ሰዎች እንባ የሚያፈሱባት፤ ስቃይ የሚቀበሉባት፤ ሁሌም አካኪ ዘራፍ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚባልባት የግፍ መሬት ለመሆኗ ካለፈው ታሪክዋ ተነስቶ አሁን ጣራ ላይ የወጣውን ሰው በሰው ላይ የሚፈጽመውን ግፍ ማየት መረጃ ይሆናል። እልፍ ጦር መዛዥ፤ እልፍ ቃል እየደረደሩ ለሃገር ነው የሚሉ እቡዪች፤ ከዚያም አልፎ ለብሄሩ ነፍጥ አንስቶ ዝንተ ዓለም ሃተፍ ተፍ ያለው ሁሉ ተመልሶ የከፋ የድር አራዊት ሲሆን አይናችን አፍጠን አይተናል። እያየንም ነው።
    አሁን እንሆ በአማራ ክልል የሚሆነው ሁሉ ምንም ለአማራ ህዝብም ሆነ ለኢትዮጵያ የማይጠቅም መሆኑን ከአሁኑ መረዳት ይቻላል። አማራ አማራውን እየገደለና እያስገደለ ለአማራ ህዝብ ቆመናል ማለት ቧልት ነው። በዚህ ፍጅት ትርፍ ያላቸው ኦነግና ወያኔ እንዲሁም የሃገሪቱን ሰላም ጭራሽ የማይፈልጉ የውስጥና የውጭ ሃይሎች ብቻ ናቸው። ፋኖ ከተማን ተቆጣጠረ ይህን ምሽግ ሰበረ እያሉ ሰውን ለሞት ማመቻቸት ተገቢ አይደለም። ፌዴራል መንግስቱ ያለውን ሁሉ ሃይል ከተጠቀመ ተራራ ላይ መውጣት፤ ምሽግ ውስጥ መደበቅ፤ ወይም ጫካ ውስጥ መወሸቅ አያድንም። ፋኖ የፓለቲካ ጥያቄ ካለው ይህን ለመንግስትና ለዓለም ህዝብ ግልጽ አድርጎ ማስረዳት አለበት። ይህ ሲባል መንግስት በአማራ ህዝብ ላይ ተጽኖ አላደረግም። አማራ በዘርና በቋንቋው እየተሰቃዬ አይደለም ለማለት አይደለም። ኦነግ በአማራ ህዝብ ላይ የሰራውና የሚሰራው ዶኮሜንት የተደረገ ተግባር ስለሆነ ዓሊ ሊባል አይችልም። የብልጽግናው መንግስት ወደ ልቡ ተመልሶ በምክክርና ነገሮችን በማርገብ ፋንታ ልክ ከወያኔ ጋር 3 ጊዜ እንደተፋለመው አሁንም ህግ አስከብራለሁ በሚል ሽፋን ህዝብን ማመሳቀል ዛሬን ብቻ ማየት ብቻ ይሆናል። የተገፋ ህዝብ ሆ ብሎ ሲነሳ ምንም ምንም አያስቆመውም።
    የብልጽግናው መንግስት እልፍ ጊዜ በወልቃይትና በሌሎች የአማራ ቦታዎች ከመወሻከት ይልቅ እውነቱን ይዞ ቦታና ስፍራው ለአማራ ህዝብ ማስረከብ ነው። ከዚህ በዘለለ ወያኔን ለማስደስት የሚደረገው መገለባበጥ ሁሉ ህዝብን ለእልቂት የሚዳርግ ነው። አሁን በአማራ ክልል የሚደረገውም ወረራ አማራውን አዳክሞ ለወያኔ ለማስረከብ የታለመ እንደሆነ ማመን አያዳግትም። ውጊያው ለምን በአማራ ክልል ሆነ? የሚሞተውና የሚታሰረው ለምን አማሮች ብቻ ሆኑ? ፍርሃቱ ከየት የመነጨ ነው? ከላይ ኮ/ሉ እንዳሉት ከማንም ጋር ግጭት አይጠቅምም። ግን ወያኔ በወልቃይት ህዝብ ላይ ያደረሰውን ግፍ ያየ ዳግም ከወያኔ ሥር ከመሆን ተፋልሞ መሞትን ይመርጣል። ወያኔ በወልቃይት ህዝብ ላይ የፈጸመው በደል ጀኖሳይድ ነው። ግን ለጥቁር ደም ማን ገዶት? ለዚያውም ጥቁርን ጥቁር ሲገድለው እፎይታ እንጂ ማን ለምን ብሎ ይጠይቃልና! በማጠቃለያው ፋኖ ቋሚ መግለጫና አላማ ለህዝብና ለመንግስት ይፋ ሊያረግ ይገባል ዝም ብሎ በለውና በይው ለማንም አይጠቅምም። ሞት ይብቃ፤ ሰላም ለሃገራችን ይሁን!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule