• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“(ላለፉት 4 ዓመታት) ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ” ወ/ሮ መዓዛ

November 6, 2022 08:46 pm by Editor Leave a Comment

የመንግሥት ሥራ አስፈጻሚ አካል የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ ማክበር ካልቻለ ሥርዓት ተሰብሯል ማለት እንደሆነ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ተናገሩ። ላለፉት አራት ዓመታት ሪፖርት ሊያቀርቡ ባለመቻላቸው አፈጉባዔውን ወቅሰዋል።

ፕሬዚዳንቷ ይህን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ፣ እንዲሁም የሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ ክንውን ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በገመገመበት ወቅት ነው።

ምክር ቤቱ ባካሄደው የአንድ ቀን የፍርድ ቤቶች ግምገማ ከምክር ቤት አባላትና ከሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች፣ ፍርድ ቤት ከወሰነላቸው በኋላ ውሳኔ የማይከበርላቸውን አካላት በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

የሕግ ባለሙያው አቶ በፍቃዱ ድሪባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ድርጅት በመወከል የተገኙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሦስቱ የመንግሥት አካላት አንዱና ትልቁ ዜጎች የመጨረሻ የመብት ጥሰት ሲገጥማቸው መብታቸውን ሊያስከብሩበት የሚችሉበት ተቋም በመሆኑ፣ በማንኛውም መንገድ ይህ ተቋም የሚወስነው ውሳኔ አጠያያቂ መሆን እንደሌለበትና ቀይ መስመር መቀመጥ እንዳለበት ተናግረዋል።

በመሆኑም የአንድ ዳኛ ውሳኔ ለማስከበር እስከየትኛውም ርቀት ድረስ መሄድ እንዳለበት የገለጹት አቶ በፍቃዱ፣ ለአብነት በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት አንድ ዳኛ የወሰነውን ውሳኔ እንዲያስፈጽም ትዕዛዝ የተሰጠው ፖሊስ ጉዳዩን ባለማስፈጸሙ ምክንያት፣ ፖሊሱ ላይ ማዘዣ እንደወጣ፣ ፖሊሱ አልታዘዝ በማለቱ ደግሞ የፖሊሱ አለቃ ላይ ማዘዣ የወጣበትን ክስተት አውስተዋል።

በመሆኑም ዳኞች በዚህ ደረጃ ቆራጥ መሆን እንዳለባቸው በመጥቀስ አንድ ዜጋ ያለ አግባብ አንድ ሰዓትም ቢሆን መታሰር እንደሌለበት ተናግረዋል።

የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ እፀገነት መንግሥቱ በበኩላቸው፣ ፓርላማው የመስክ ምልከታ በሚያደርግበት ወቅት ያጋጠሙ በርካታ ቁልፍ የሆኑ ችግሮች ያሏቸውን በመጥቀስ፣ ለምሳሌ ያህል፣ “በውሳኔ መዘግየት ምክንያት እስር ላይ የሚቆዩ ሰዎች ማየት በጣም ውስጥን የሚነካ ነገር ነው፤” ብለዋል።

በዚህም ዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እየተጣሰ እንደሆነና እንዲህ እየሆነ ያለው በእስር ላይ ባሉ ዜጎች ችግር ሳይሆን፣ በተለያዩ ተቋማት ተቀናጅቶ ባለመሥራት የተነሳ መሆኑን ጠቁመዋል። ለምሳሌ ፖሊስ በወቅቱ ጉዳይ ባለማጣራቱ ምክንያትና በመሰል ሰበቦች የሚቀርቡ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ፍርድ ቤቶች በዚህ ውሳኔ ሳያገኙ እንዲቀሩ በሚደረጉ ሰዎች ላይ ምን ትላላችሁ ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።

የውሳኔ አፈጻጸምን በተመለከተ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቷ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ፣ ምላሽ ሲሰጡ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ሁልጊዜም ተፈጻሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። ለአብነት በፍርድ ቤቶች በዓመት 200 ሺሕ ጉዳዮች እንደሚታዩና ከዚህ ውስጥ ችግር ያጋጠመው ከአምስት ወይም ከስድስት እንደማይበልጥ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ያም ሆኖ ጉዳዩ ሁልጊዜ ጎላ ብሎ ሲጠየቅ እንደሚሰማ በመጥቀስ፣ “የፍርድ ቤት ውሳኔ ተሰጥቶ መፈጸም ያቃተን ካለ ግን፣ መዝገቡ ይምጣልን ክትትል እናደርጋለን፤” ብለዋል። “ከዚያ አልፎ አስፈጻሚው ይህንን ማክበር ካልቻለ፣ ሥርዓት ተሰብሯል ማለት እንደሆነ፣ ይህ ከፍተኛና ከፍርድ ቤትም ያለፈ ችግር በመሆኑ፣ እንዲህ ዓይነት ጉዳይ ያለው አካል ማስረጃ ይዞ ይምጣ እኛ ክትትል አድርገን እስከ መጨረሻው ድረስ እንሄዳለን፤” ብለዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ማጉላላት እንዳለ የጠቀሱት ፕሬዚዳንቷ፣ የፍርድ ቤት ውሳኔ አልተፈጸመም የሚል አካል ካለ ግን አሁንም ማስረጃ ይዞ ይምጣ ብለዋል።

“በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኃላፊነት ከተሰጠን አራት ዓመት ቢቆጠርም፣ የፍርድ ቤቶችን አፈጻጸም ሪፖርት ሙሉውን ለፓርላማው እንድናቀርብ ዕድል አላገኘንም፤” ሲሉ ወቀሳ አቅርበዋል።

“ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ፤” ሲሉ የተናገሩት ወ/ሮ መዓዛ፣ “ወቅቱን ጠብቀን ከሥር ከሥር መረጃ ባለማቅረባችን ምክንያት መቅረብ የነበረባቸው ጉዳዮች ይበዛሉ፤” ሲሉ አክለው ተናግረዋል። ሆኖም ሙሉ ፓርላማው ላይ ሪፖርት ለማቅረብ ዕድል ባይገኝም፣ በተለያዩ ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ልምዶችን በመውሰድ አሁናዊ የፍርድ ቤቶች ሪፖርት በሚል መረጃ እንደሚሰጡ አስረድተዋል።

የፍርድ ቤት ሪፎረም መሬት ላይ ያለው አተገባበር ዝቅተኛ ነው ተብሎ ከአባላቱ ለተነሱላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ፣ “ቁጭ ብዬ አንዳንድ ጊዜ ሪፖርት ሳነብ እንዲሁም ከሌሎች ጋር ስንነጋገር፣ እውነቱን ልንገራቸሁ፣ ራሴን ማመሥገን አይሁንና ይህ ሁሉ ሥራ እንዴት ተሠራ ብዬ እጠይቃለሁ፤” ብለዋል። አሁን በሥራ ላይ ያለው አመራር ትልቁ ጥንካሬ ከዚህ ቀደም ታስበው ያልተሠሩ ሥራዎችን ለመሥራት ማሽኑን በማንቀሳቀስ፣ ወደ 30 የሚደርሱ መመርያዎች ማዘጋጀት መቻሉ ቀላል አለመሆኑን፣ ነገር ግን የፍርድ ቤት ሥራ ሰፊ በመሆኑና ፍርድ ቤት ሲሶ መንግሥት በመሆኑ ሥራው ተጀመረ እንጂ አላለቀም ብለዋል።

ለረዥም ዓመታት በዕቅድ ላይ የነበረውን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዘመናዊ ሕንፃ ግንባታ፣ ፍርድ ቤቱ ምንም እንኳ መሬት ተቀብሎ ዲዛይን አውጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊዙን በማቋረጥ ካርታውን እንዳመከነው፣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃነ መስቀል ዋቅጋሪ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ የሕንፃ ግንባታ ጨረታ ለማውጣት ያልመከነ ካርታ ስለሚያስፈልግ፣ “ፓርላማው በጀት እንደመደበልን ሁሉ፣ ቦታውን አግኝተን ሕንፃውን መገንባት እንድንችል ዕገዛ ያድርግልን፤” በማለት ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal supreme court, meaza ashenafi, tagesse chafo

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule