• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“(ላለፉት 4 ዓመታት) ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ” ወ/ሮ መዓዛ

November 6, 2022 08:46 pm by Editor Leave a Comment

የመንግሥት ሥራ አስፈጻሚ አካል የፍርድ ቤቶችን ውሳኔ ማክበር ካልቻለ ሥርዓት ተሰብሯል ማለት እንደሆነ፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ ተናገሩ። ላለፉት አራት ዓመታት ሪፖርት ሊያቀርቡ ባለመቻላቸው አፈጉባዔውን ወቅሰዋል።

ፕሬዚዳንቷ ይህን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ፣ እንዲሁም የሸሪዓ ፍርድ ቤቶችን፣ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ ክንውን ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. በገመገመበት ወቅት ነው።

ምክር ቤቱ ባካሄደው የአንድ ቀን የፍርድ ቤቶች ግምገማ ከምክር ቤት አባላትና ከሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች፣ ፍርድ ቤት ከወሰነላቸው በኋላ ውሳኔ የማይከበርላቸውን አካላት በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

የሕግ ባለሙያው አቶ በፍቃዱ ድሪባ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ድርጅት በመወከል የተገኙ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሦስቱ የመንግሥት አካላት አንዱና ትልቁ ዜጎች የመጨረሻ የመብት ጥሰት ሲገጥማቸው መብታቸውን ሊያስከብሩበት የሚችሉበት ተቋም በመሆኑ፣ በማንኛውም መንገድ ይህ ተቋም የሚወስነው ውሳኔ አጠያያቂ መሆን እንደሌለበትና ቀይ መስመር መቀመጥ እንዳለበት ተናግረዋል።

በመሆኑም የአንድ ዳኛ ውሳኔ ለማስከበር እስከየትኛውም ርቀት ድረስ መሄድ እንዳለበት የገለጹት አቶ በፍቃዱ፣ ለአብነት በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት አንድ ዳኛ የወሰነውን ውሳኔ እንዲያስፈጽም ትዕዛዝ የተሰጠው ፖሊስ ጉዳዩን ባለማስፈጸሙ ምክንያት፣ ፖሊሱ ላይ ማዘዣ እንደወጣ፣ ፖሊሱ አልታዘዝ በማለቱ ደግሞ የፖሊሱ አለቃ ላይ ማዘዣ የወጣበትን ክስተት አውስተዋል።

በመሆኑም ዳኞች በዚህ ደረጃ ቆራጥ መሆን እንዳለባቸው በመጥቀስ አንድ ዜጋ ያለ አግባብ አንድ ሰዓትም ቢሆን መታሰር እንደሌለበት ተናግረዋል።

የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ወ/ሮ እፀገነት መንግሥቱ በበኩላቸው፣ ፓርላማው የመስክ ምልከታ በሚያደርግበት ወቅት ያጋጠሙ በርካታ ቁልፍ የሆኑ ችግሮች ያሏቸውን በመጥቀስ፣ ለምሳሌ ያህል፣ “በውሳኔ መዘግየት ምክንያት እስር ላይ የሚቆዩ ሰዎች ማየት በጣም ውስጥን የሚነካ ነገር ነው፤” ብለዋል።

በዚህም ዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው እየተጣሰ እንደሆነና እንዲህ እየሆነ ያለው በእስር ላይ ባሉ ዜጎች ችግር ሳይሆን፣ በተለያዩ ተቋማት ተቀናጅቶ ባለመሥራት የተነሳ መሆኑን ጠቁመዋል። ለምሳሌ ፖሊስ በወቅቱ ጉዳይ ባለማጣራቱ ምክንያትና በመሰል ሰበቦች የሚቀርቡ መሆናቸውን በመግለጽ፣ ፍርድ ቤቶች በዚህ ውሳኔ ሳያገኙ እንዲቀሩ በሚደረጉ ሰዎች ላይ ምን ትላላችሁ ሲሉ ጥያቄ አቅርበዋል።

የውሳኔ አፈጻጸምን በተመለከተ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንቷ ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ፣ ምላሽ ሲሰጡ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ሁልጊዜም ተፈጻሚ እንደሚሆኑ ገልጸዋል። ለአብነት በፍርድ ቤቶች በዓመት 200 ሺሕ ጉዳዮች እንደሚታዩና ከዚህ ውስጥ ችግር ያጋጠመው ከአምስት ወይም ከስድስት እንደማይበልጥ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ያም ሆኖ ጉዳዩ ሁልጊዜ ጎላ ብሎ ሲጠየቅ እንደሚሰማ በመጥቀስ፣ “የፍርድ ቤት ውሳኔ ተሰጥቶ መፈጸም ያቃተን ካለ ግን፣ መዝገቡ ይምጣልን ክትትል እናደርጋለን፤” ብለዋል። “ከዚያ አልፎ አስፈጻሚው ይህንን ማክበር ካልቻለ፣ ሥርዓት ተሰብሯል ማለት እንደሆነ፣ ይህ ከፍተኛና ከፍርድ ቤትም ያለፈ ችግር በመሆኑ፣ እንዲህ ዓይነት ጉዳይ ያለው አካል ማስረጃ ይዞ ይምጣ እኛ ክትትል አድርገን እስከ መጨረሻው ድረስ እንሄዳለን፤” ብለዋል። በተለያዩ ምክንያቶች ማጉላላት እንዳለ የጠቀሱት ፕሬዚዳንቷ፣ የፍርድ ቤት ውሳኔ አልተፈጸመም የሚል አካል ካለ ግን አሁንም ማስረጃ ይዞ ይምጣ ብለዋል።

“በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኃላፊነት ከተሰጠን አራት ዓመት ቢቆጠርም፣ የፍርድ ቤቶችን አፈጻጸም ሪፖርት ሙሉውን ለፓርላማው እንድናቀርብ ዕድል አላገኘንም፤” ሲሉ ወቀሳ አቅርበዋል።

“ሪፖርት ባለማቅረባችን ክቡር አፈ ጉባዔውን በግል እወቅሳቸዋለሁ፤” ሲሉ የተናገሩት ወ/ሮ መዓዛ፣ “ወቅቱን ጠብቀን ከሥር ከሥር መረጃ ባለማቅረባችን ምክንያት መቅረብ የነበረባቸው ጉዳዮች ይበዛሉ፤” ሲሉ አክለው ተናግረዋል። ሆኖም ሙሉ ፓርላማው ላይ ሪፖርት ለማቅረብ ዕድል ባይገኝም፣ በተለያዩ ምክንያቶች ዓለም አቀፍ ልምዶችን በመውሰድ አሁናዊ የፍርድ ቤቶች ሪፖርት በሚል መረጃ እንደሚሰጡ አስረድተዋል።

የፍርድ ቤት ሪፎረም መሬት ላይ ያለው አተገባበር ዝቅተኛ ነው ተብሎ ከአባላቱ ለተነሱላቸው ጥያቄ መልስ ሲሰጡ፣ “ቁጭ ብዬ አንዳንድ ጊዜ ሪፖርት ሳነብ እንዲሁም ከሌሎች ጋር ስንነጋገር፣ እውነቱን ልንገራቸሁ፣ ራሴን ማመሥገን አይሁንና ይህ ሁሉ ሥራ እንዴት ተሠራ ብዬ እጠይቃለሁ፤” ብለዋል። አሁን በሥራ ላይ ያለው አመራር ትልቁ ጥንካሬ ከዚህ ቀደም ታስበው ያልተሠሩ ሥራዎችን ለመሥራት ማሽኑን በማንቀሳቀስ፣ ወደ 30 የሚደርሱ መመርያዎች ማዘጋጀት መቻሉ ቀላል አለመሆኑን፣ ነገር ግን የፍርድ ቤት ሥራ ሰፊ በመሆኑና ፍርድ ቤት ሲሶ መንግሥት በመሆኑ ሥራው ተጀመረ እንጂ አላለቀም ብለዋል።

ለረዥም ዓመታት በዕቅድ ላይ የነበረውን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዘመናዊ ሕንፃ ግንባታ፣ ፍርድ ቤቱ ምንም እንኳ መሬት ተቀብሎ ዲዛይን አውጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊዙን በማቋረጥ ካርታውን እንዳመከነው፣ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃነ መስቀል ዋቅጋሪ ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ የሕንፃ ግንባታ ጨረታ ለማውጣት ያልመከነ ካርታ ስለሚያስፈልግ፣ “ፓርላማው በጀት እንደመደበልን ሁሉ፣ ቦታውን አግኝተን ሕንፃውን መገንባት እንድንችል ዕገዛ ያድርግልን፤” በማለት ፕሬዚዳንቱ ጠይቀዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal supreme court, meaza ashenafi, tagesse chafo

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule