• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጥቅምት 24 “የክህደት ቀን” ተብሎ በግንቦት 20 መቃብር ላይ ይተከልልን!

November 4, 2022 01:58 am by Editor Leave a Comment

በራሳቸው ሕዝብ ላይ ሲደርስ ሰማይ የሚደፋባቸውና ዓለም ሁሉ አብሯቸው እንዲያለቅስ የሚፈልጉት ምዕራባውያን በሌሎች ላይ ለሚደርሰው ሰቆቃ ቅንጣት ታህል ግድ አይላቸውም። አንድ ማሳያ እንጥቀስ፤

የዛሬ 80 ዓመት አካባቢ ጃፓን የአሜሪካንን ድንበር ጥሳ ከሐዋይ ደሴቶች አንደኛዋ ላይ የሚገኘውን ወታደራዊውን የፐርል ወደብ ገና በጠዋቱ በድንገት አጠቃች፤ በወደቡ ላይ የነበሩት 8 መርከቦች ጉዳት ደረሰባቸው፤ አራቱ ሰጠሙ፤ በአጠቃላይ ወደ 20 የሚደርሱ መርከቦችና ጀልባዎች ከጥቅም ውጪ ሆኑ፤ ከ300 በላይ የሚሆኑ አውሮፕላኖች፣ ጀቶችና ሔሊኮፕተሮች ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባቸው፤ ከሁሉ በላይ ከ2,400 በላይ የሚሆኑ ባሕረኞች፣ ወታደሮችና ሰላማዊ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ፤ ከ1,000 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆሰሉ።

በቀጣዩ ቀን ዲሴምበር 8፣ 1941 የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት ሁለቱንም ምክር ቤት ሰብስበው ለአሜሪካ ሕዝብ ንግግር አደረጉ። “የጃፓን ንጉሣዊ የባሕርና የአየር ኃይል ሆን ብሎና በድንገት በአሜሪካ ላይ ያደረሰበት የትላንቱ ዲሴምበር 7፤ 1941 ጥቃት በታሪክ በክፋት ሲታወስ የሚኖር ቀን ይሆናል” በማለት ለሕዝባቸው ተናገሩ። ሲቀጥሉም፤ “ይህንን ሆን ብሎና በዕቅድ የደረሰብንን ጥቃት የቱንም ያህል ጊዜ ይውሰድ የአሜሪካ ሕዝብ ባለው ኃያል ጽድቅ በማሸነፍ ፍጹም ድል እንደሚጎናጸፍ ምንም ጥርጥር የለም” ካሉ በኋላ አሜሪካ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ውስጥ መግባቷን ይፋ አደረጉ፤ በቀጣይም ከ4 ዓመታት በኋላ አሜሪካ ሒሮሺማ እና ናጋሳኪ የሚባሉ የጃፓን ከተሞችን በአቶሚክ ቦምብ አወደመች። በመጨረሻም አሜሪካና አጋሮቿ ጦርነቱን በበላይነት አሸንፈው ክብራቸውን አስጠበቁ።

በምዕራባውያን ትከሻ ተንጠላጥለውና በጉልበተኛ ሤራቸው ተደግፈው ወደ ሥልጣን በመምጣት ኢትዮጵያን በግፍ ሲገዙ የነበሩት ትህነጎች በወታደራዊ ብቃታቸውና ጀግንነታቸው ድል እንዳደረጉ ራሳቸውን አሳምነው እንወክለዋለን የሚሉትን ሕዝብ ይህንኑ የውሸት ድል እያጠጡ በስካር አኖሩት። “ተራራ አንቀጥቃጭ”፣ “በድንጋይ ኮሎኔል ማራኪ”፣ ወዘተ በሚል ባዶ ፕሮፓጋንዳ ራሳቸውን ክበው የማይሸነፉ፣ የማይገረሰሱ፣ የማይንኮታኮቱ አድርገው ሕዝብን ለማሳመን ብዙ ጣሩ።

ይህንን ሲጠጣና ሲያጠጣ የኖረው ደጋፊና የጥቅማቸው ተካፋይ ሁሉ የትግራይን ሕዝብ በጦርነት ለመማገድ ከሩቅ ሆኖ “ጦርነት ባሕላዊ ጨዋታችን ነው”፣ “ጦርነትን እንፈጥራለን”፣ “እኛ ከእስራኤል በላይ ነን”፣ ወዘተ በማለት ውድቀቱን በሚያፋጥን ዕብሪት ተወጠረ።

የዚህ ሁሉ ጥርቅም ዕብሪትና ከኢትዮጵያ ተዘርፎ ሲከማች የነበረ በርካታ ገንዘብ፣ የቡድንና የግል የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሽ፣ ወዘተ ባንድ በኩል፤ በሌላ ደግሞ የምዕራባዊያን አለሁላችሁ ባይነት ተደምሮ የዛሬ ሁለት ዓመት ትህነግ የሰሜን ዕዝን ጥቅምት 24 ቀን በድንገት አጠቃ። ሲያበላው፣ ሲያርስለት፣ አንበጣ ሲከላከልለት፣ ከደሞዙ ቆጥቦ ትምህርት ቤትና መንገድ ሲያሰራለት የነበረውን ወታደር በግፍ ጨፈጨፈ፣ በተቀናጀና በተጠና ሰዓት በሰሜን ዕዝ ሥር በሚገኙ ክፍሎች ሁሉ የሚገኘውን ወታደር በቁጥጥሩ ሥር በማዋል የእጅ ሥጡ ጥያቄ አቀረበ።

ኢትዮጵያ በዕቅድ፣ በግልጽና በማያሻማ መልኩ የተከፈተባትን ጥቃት ለመመከት ጦርነት ውስጥ መግባት ግድ ሆነባት። በሁሉም የምድር ኃይል የበላይነት የነበረውንና በወታደር ብዛት በትንሹ አምስት የትህነግ ታጣቂ ለአንድ የኢትዮጵያ ወታደር በሆነበት ጦርነት እውነትን፣ ልበሙሉነትንና ኢትዮጵያዊነትን የተጎናጸፉት ልጆቻችን ትህነግን በ15 ቀናት አስተነፈሱት። የትህነግ ዓይነት ትዕቢት ግን ቶሎ አይተነፍስምና አንጋሾቹን ምዕራባውያንን ተማምኖ ደግሞ ደጋግሞ ጥቃት ሰነዘረብን፤ ደግሞ ደጋግሞ አሳፋሪ ወታደራዊ ሽንፈት ተቀበለ። ትላንት ጥቅምት 23 ቀን ደግሞ በፕሪቶሪያ ፖለቲካዊ ሽንፈትን በመቀበል ትጥቅ እፈታለሁ አለ።

ትህነግ በአገራችን ላይ ያደረሰው መጠነ ሰፊና ሁሉን ዓቀፍ ውድመት በአንድ ትውልድ ተዘክሮ፣ በጥቂት መጽሐፍት ተጽፎ፣ በጥቂት ስብሰባ ተወያይቶ የሚያበቃ አይደለም። ላለፉት 80 ዓመታት የናዚ ወንጀል ተወርቶ እንዳላለቀ የትህነግም እንዲሁ የሚያልቅ አይደለም።  

ጀርመኖች ናዚ ያደረሰባቸውን ደግመው ደጋግመው ያስቡታል፣ ይጽፉበታል፣ ይተውኑታል፣ በታሪክ ይማሩታል፣ በየዓመቱ ያከብሩታል፤ ወዘተ። ከዚያ አልፎ የዓለም ሕዝብ እንዲማርበት ልዩ ልዩ ማሳያዎችን ያቀርባሉ። በርሊን ከተማ ውስጥ የናዚን ግፍ የሚያስታውሱ ነገሮች በየቦታው አሉ። አንዳንዶቹ በምን ዓይነት ዝርዝር እና ጥንቃቄ ተሰንደው እንደተቀመጡ መመልከቱ እጅግ ያስደምማል።  

ጥቅምት 24 የትህነግ የግፍ ቁንጮ የታየባት ቀን ናት። ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብሎ በመሰየም የትግራይን ሕዝብ ሽፋን በማድረግ፤ “የምታገለው ለአንተ ነጻነት ነው” በማለት፤ መልሶ እታገልለታለሁ ያለውን ሕዝብ ያስጨፈጨፈው፣ ያስራበው፣ የግፈ ሰለባ ያስደረገው፣ … ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ቡድን የኢትዮጵያን የሥልጣን መንበር ከተቆናጠጠ በኋላ የትግራይ ሰዎችን በሌላው ኢትዮጵያዊ ለማስጠላትና “ስም ለማሰጠት” እንዲሁም ለማጠልሸት 50 ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል።

“እነዚህ” በኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ የዛሬ 30 ዓመት አነጋገር “የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ሕዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ …” የኢትዮጵያን ሃብት እየዘረፉ በትግራይ ኢንቨስት በማድረግ፣ የትግራይ ተወላጆችን የተለያዩ ስልቶችን – ከግድያ እስከ ማስገደድ – እየተጠቀሙ የወንጀላቸው ተባባሪ እንዲሆኑ በማድረግ፤ ትግራዮችን ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በማስጠላት ጉዳዩን ከራሳቸው በማውረድ በሕዝብ መካከል የሚደረግ በማስመሰል እኩይ ተግባራቸውን ሲወጡ ቆይተዋል። ለሆዳቸው ያደሩን በፕ/ር መስፍን አነጋገር “አእምሯቸው የሻገተባቸው” ይህንን ማታለያና ማባበያ እየወሰዱ ከሌላው የኢትዮጵያ ወገናቸው ጋር ሆድና ጀርባ በመሆን “ነጻ አውጣኝ” ብለው በስምምነት ያልሰየሙት ቡድን ባዶ ተስፋ እየሰጠ የውንብድና ተግባር ሲፈጽምባቸው የተግባሩ ተባባሪዎች ሆነዋል።

  • የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)
  • የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል ሁለት)
  • የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመንግሥት ውሸት፣ የሃይማኖት ተቋማት ውድቀት፣ … (ክፍል ሦስት)
  • የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች — የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ!
  • የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!

ትህነግ በተለይ ከትግራይ ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ ላለፉት 50 ዓመታት የበተነው መርዝ እንዲህ በቀላሉ የሚረሳና የሚተው አይደለም። ደግሞ እንዳይመጣ ደግሞ ደጋግሞ መታወስና መነገር አለበት። የጉዳቱ መጠን እንዴት አገር አልባ ሊያደርገን እንደነበር አሁን ላለነውም ወደፊት ለሚመጣውም ትውልድ ያለማቋረጥ ሊነገር፣ ሊታወስ፣ ሊዘከር ይገባል።

ስለዚህ ትህነግ ባላሸነፈው ጦርነት ለ27 ዓመታት ደርግን ድል ያደረግሁበት ቀን እያለ የሚያከብረው ግንቦት 20 ተራ የሥራ ቀን መሆን አለበት። መቀየር ያለበት ሕግ በፓርላማው መቀየር አለበት። በምትኩ የጥቅምት 24 ቀን በክብር እና በታላቅ ጥሞና በመላው አገራችን መከበር አለባት።

ድል የተቀዳጀነው ለግማሽ ምዕተ ዓመት በመሣሪያ፣ በሃብት፣ በቁስ፣ በፕሮፓጋናዳ ራሱን ካገዘፈ፣ መርዛማ ሥሩን በመላ አገሪቱና በውጭ ካሉ ጠላቶች ጋር አብሮ በዘረጋ ታሪካዊ ነቀርሳ ላይ ነውና ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ጥንቃቄ ብቻ ሳይሆን ብልጠትም ግድ ነው። ባለማስተዋል መርዙ እንዲያገረሽ ምቹ ሁኔታ ልንፈጥር እንደምንችል መረዳት ያስፈልጋል። ስለዚህ ጥቅምት 24 ታስቦ የሚውል ሳይን ተከብሮ የሚውል ቀን መሆን ያለበት።

ትህነግ ቢወላልቅም ጭራሽ ዓመድ እስኪሆን ጊዜና ጥበብ ስለሚያስፈልግ ከተራ የብሽሽቅ፣ “ድሉ የኔ ነው” ከሚል ያበጠ ስሜት መላቀቅና የፈራረሰው ትህነግን ብቻ በመለየት ከትግራይ ሕዝብም ጋር የቀደመውን መርዝ ያላጎደፈው ግንኙነት ለመመሥረት መሥራት ከዜጎች ሁሉ ይጠበቃል። ትህነግ ያከማቸውን ብረት ለማስረከብ የተገደደው ልክ የዛሬ ዓመት በክህደት በታረደው ኩራታችን የመከላከያ ሠራዊትና ጥምር ኃይሎች ደምና መስዋዕትነት በመሆኑ፣ አስተዋይነትን ማጣት ማለት በዚህ ውድ የሕይወት ዋጋ እንደመጫወት ይቆጠራልና ድሉን በብልሃትና በማስተዋል እናጽናው። ከዚህ አኳያ ድሉን ለማኮሰስና በሳንቲም ለቀማ ላይ በመሰማራት ያልተፈጠሩ ወሬዎችን በማኅበራዊ ሚዲያ በማሰራጨት የተሰማሩትን፤ ሕዝብን የሚያሸብር የሤራ ትንተና የሚሰጡን ሁሉ መንግሥት በሕግ እኛም እንደ ዜጋ በንቃት ልናስተናግዳቸው ይገባል።  

ጥቅምት 24ን አንረሳም ስንል በጥቂት ደቂቃዎች የእጅ በደረት ሥርዓት ብቻ የሚታለፍ መሆን የለበትም። ግንቦት 20ን ተክቶ ጥቅምት 24 በይፋ በመላው ኢትዮጵያና በዳያስፖራው ዘንድ የሚከበር በዓል መሆን አለበት። ጥቅምት 23 ትህነግ ያሸብረን የነበረበትን ትጥቅ እፈታለሁ ብሎ ዕብሪቱ የተነፈሰበት ትልቅ የድል ቀን ነው። የካቲት 23 የምዕራባውያንን ዕብሪት ያስተነፈስንበት የዓድዋ ድል በዓላችን ቀን ነው። ጥቅምት 24 ደግሞ አገራችን እንድትፈርስ ከተደገሰላት የክፋት ድግሥ ዓድዋን እያሰብን ድል ያደረግንበትና መቼም የማንረሳው ቀን የዘመናችን ዓድዋ ነው። ሥራ የማይሠራበት ቀን ሆኖ ይከበር ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Middle Column Tagged With: ethiopian terrorists, ginbot 20, operation dismantle tplf, tikimt 24, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule