ይህ ድምፅ የምዕራባውያኑ የመጨረሻው ድምፅ ነው። ወስነዋል። የመጨረሻውን ጫና ጀምረዋል። ጫናው እየጨመረ ይሄዳል። ለምን በአዲስ መልክ ጫናውን ጀመሩ ብንል ተስፋ አድርገውት የነበረው የተመድ የፀጥታው ም/ቤት እነሱ እንደሚፈልጉት ባለመወሰኑ ይመስላል። በክፍል 3 የመጨረሻ ካርዶችን እንይ:-1ኛ) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን ዶክተር አብይ ጋር ደውሎ ነበር። በትግራይ ረሃብ ሊከሰት ስለሚችል ያሳስበኛል። በሃገሪቱ ያለው የብሄር ውጥረቶችም ያሳስበኛል። የኤርትራ ጦር ይውጣ። ሁሉም አካላት ጦርነት አቁመው ወደ ድርድር መምጣት አለባቸው። ወዘተ የሚል ውይይት አድርጓል። የዚህ ስልክ አላማ በአጭሩ ከሞተው ጁንታ ጋር "ድርድር እና እርቅ" አድርግ የሚል ነው። ካልሆነ ግን (የብሄር ውጥረቶች ያልኩህ ሌላ መልክ እንዲይዙ እናደርጋለን። እርስበርስ ትፋጃላችሁ። ከዚያም አልቻልክም ተብለህ … [Read more...] about ምዕራባውያን – “ለድርድር እናስገድዳለን ካልሆነ ወደ ዶ/ር ዐቢይ እንዞራለን”
Archives for April 2021
በአስመጪ ዳዊት የማነ ሀሰተኛ ሰነድ ወደ ሀገር ዉስጥ ሊገባ የነበረ ገጀራ ተያዘ
ከፌደራል ፖሊስ ፈቃድ እንደተሰጠው በማስመሰል በተጭበረበረ ሰነድ ርክክብ ተፈጽሞ ባለቤት የተባለው ሰው ከተረከበ በኋላ በተደረገ ክትትል 186 ሺህ 240 ገጀራ በቁጥጥር ስር ዋለ። በጅምላ ጭፍጨፋ በተካሄደባቸው አገራት በተገኘ ልምድ ገጀራ ክልከላ የጣለበት የእጅ የጥፋት መሳሪያ ነው። ገጀራው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በማህበራዊ ሚዲያዎች ህጋዊ ፈቃድ እንዳለው እየተገለጸ የሚሰራጨው ደብዳቤ ሃሰት መሆኑም ተመልክቷል። ከ15 ቀን በፊት በአስመጪ ዳዊት የማነ ስም ብዛቱ 186,240 የእጅ ገጀራ በአራት ባለ 20 ጫማ ኮንቴይነሮች ከቻይና ተጭኖ ሞጆ ጉምሩክ ይደርሳል። እቃው በዲክላራሲዮን ቁጥር 4-1919/21 ተመዝግቦ ወደ ሀገር ዉስጥ እንዲገባ ከፌዴራል ፖሊስ የተፈቀደለት በማስመሰል እና ሐሰተኛ ሰነድ የተዘጋጀለት ነው። ይኸው ሃሰተኛ ሰነድ ለገቢ ዕቃ አወጣጥ የሰነድ መርማሪው … [Read more...] about በአስመጪ ዳዊት የማነ ሀሰተኛ ሰነድ ወደ ሀገር ዉስጥ ሊገባ የነበረ ገጀራ ተያዘ
ኢትዮጵያ “failed state” አይደለችም – የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት
የም/ቤቱ አባላት ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ የፖለቲካ ነፃነት እና የግዛት አንድነት ያላቸውን ጠንካራ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ የትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በክልሉ ላለው ቀውስ እልባት ለመስጠት የኢትዮጵያ መንግስት እያከናወነ ያለውን ተግባር አድንቋል፡፡ መግለጫው እንደሚለው፣ የፀጥታው ም/ቤት አባላት የኢትዮጵያ መንግሥት ሰብዓዊ ዕርዳታን ለማቅረብ እና ሰብዓዊ ተደራሽነትን ከፍ ለማድረግ እያደረገ ላለው ጥረት እውቅና ሰጥተዋል፡፡ ይሁንና የም/ቤቱ አባላት የሰብዓዊ ችግሮች አሁንም መኖራቸውን እንደሚገነዘቡ እና በክልሉ ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ እንደሚያሳስባቸውም ነው መግለጫው ያመለከተው፡፡ ከምግብ ዋስትና ጋር በተያያዘም የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ መጨመር እንዳለበት እና ያልተገደበ የሰብዓዊ … [Read more...] about ኢትዮጵያ “failed state” አይደለችም – የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት
“የጁንታው አባላት ከአገር ውጭ ለመውጣት ያደረጉት ጥረት ከሽፏል” – ሌ/ጄነራል ባጫ
የአገር መከላከያ ሰራዊት "ርዝራዥ" ሲል የሚጠራውን ሃይል መደምሰሱን አስታወቀ። ሃይሉ የተደመሰሰው ድንበር አቋርጦ ወደ ሱዳን ለመሸሽ በሞከረበት ወቅት እንደሆነ ታውቋል። ከተገደሉት በፍተሻ "የኦሮሞ ማንነት መታወቂያ ተሰርቶላቸው ነበር" ተብሏል። የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት የግንባታ ስራዎች ዋና አስተባባሪ ሌ/ጄነራል ባጫ ደበሌ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለፁት፤ እነዚህ የጁንታው አባላት ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ የሌላ ክልል መታወቂያ በመያዝ ከሀገር ሊሸሹ ሲሉ ሰራዊቱ በደረገው ከፍተኛ ጥረት ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡ የዚህ ድርጊት ዋነኛ አላማ እነዚህን አባላት ወደ ሱዳን በማሸሽ ከዚያ ሆኖ ሀገር ውስጥ ያሉትን ተጣቂ ሀይሎች በሽምቅ ውጊያ በማሰማራት ሀገር ለመበጥበጥ የታቀደ እንደነበር ሌ/ጄነራል ባጫ በመግለጫቸው ተናግረዋል፡፡ እርምጃ በተወሰደባቸው … [Read more...] about “የጁንታው አባላት ከአገር ውጭ ለመውጣት ያደረጉት ጥረት ከሽፏል” – ሌ/ጄነራል ባጫ
የዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ አደረገ
የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ለሚተገበሩት ሶስት ፕሮጀክትች የሚውል የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማድረግ ዛሬ ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና ዓለም ባንክ ግሩፕ ምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ሚ/ር ዲዮን ነው የተፈራረሙት። የገንዘብ ድጋፉ በኢትዮጵያ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎትን አሰጣጥንና ተደራሽነትን ለማሳደግ እንዲሁም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚውል ነው ተብሏል። የመጀመሪያው የ200 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች የሚውል ነው። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ክፉኛ የተጎዱ እንተርፕራይይች አዋጭ በሆነ መንግድ እንዲቀጥሉና በንግድ ውስጥ እንዲቆዩ ለማድረግ … [Read more...] about የዓለም ባንክ የ907 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ አደረገ
ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ማዘጋጀት ትፈልጋለች፡- አቶ ደመቀ መኮንን
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከሩሲያ-አፍሪካ የትብብር ጉባኤ ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦሌግ ኦዜሮቭ ጋር በጽ/ቤታቸው በተወያዩበት ወቅት ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ማዘጋጀት እንደምትፈልግ ተናግረዋል። በቀጣይ ዓመት በአፍሪካ ሊካሄድ ስለታሰበው ሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤን ኢትዮጵያ ለማዘጋጀት ዝግጁ መሆኗን ነው አቶ ደመቀ መኮንን የገለፁት። አምባሳደር ኦሌግ ኦዜሮቭ ስለ ጽ/ቤታቸው ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም የአፍሪካና ሩሲያ ኩባንያዎች በጋራ እንዲሰሩ የሚያስችል የኢኮኖሚ ትብብር ማህበር መቋቋሙን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። አያይዘውም የጉባኤው ዝግጅት አካል የሆነ ውይይት በመጪው ክረምት ከአፍሪካ ህብረትና ከአፍሪካ አገራት ጋር ምክክር እንደሚደረግም ገልጸዋል። ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላትን … [Read more...] about ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ ማዘጋጀት ትፈልጋለች፡- አቶ ደመቀ መኮንን
የአብን “ፀሐይ” ጎንደር ላይ ጠለቀች
ሤራ አክሻፊው ጎንደር ዛሬም ታሪክ ሠራ የኦህዴድ ጽንፈኞችና “አክራሪ” የሚባለው አብን በአንድነት የጠመቁት ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጭ ሴራ ዛሬ ጎንደር ላይ ተገለበጠ። ጎንደር የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማርሽ ቀያሪነቱን አሳየ። ሰልፉ ክልሉን ለማናወጥና ሕዝብ እንዲጋጭ ሌት ተቀን ለሚሰሩ ፖለቲካዊ ሞት እንደሆነ ተመልክቷል። ሰሞኑንን በደረሰው ዘገናኝ ዕልቂትና የንብረት ውድመት ማግስት የሽግግር መንግስት የጠየቁ አሉ። አብን መንግሥት እንደሌለ ሲያውጅና ክተት ሲጠራ “የሞሳድ ሥራ አስፈጻሚ” የሚባሉት፣ ቀደም ብለው አገራቸውን ከድተው የሸሹትና በውድ የኢትዮጵያ ጄኔራሎች የተመራውን መፈንቅለ መንግሥት እንዳከሸፉ የሚታወቁት ሻለቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ፤ አበበ በለው በሚመራው የአዲስ ድምጽ ሬዲዮ በኩል የሽግግር መንግሥት ለማቋቋም የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ይፋ አድርገዋል። አያይዘውም … [Read more...] about የአብን “ፀሐይ” ጎንደር ላይ ጠለቀች
ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ፈተና ውስጥ ነን። ይሁን እንጂ እንደ ሀገር እና እንደ ህዝብ ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም። “ኢትዮጵያን የመበታተኛው ሰአት አሁን ነው” - ግብጽና ሱዳን። ክፍል አንድ - መነሻ ሀገራችን የአፍሪካ የውሃ ማማ “the water tower of Africa” ይሏታል። ብዙ ሀይቆች አሏት፤ ብዙ ወንዞች አሏት። ምድር የተሸከመችው ትልቁ ወንዝ አባይ አላት። ብዙዎቹ የውሀ ሀብታምነታችንን ሲነግሩን እኛም ስንዘፍንለት፣ ለልጆቻችን በየተረቱና በየጂኦግራፊ ትምህርቱ ስናስተምረው ቆይተናል፤ ኖረናል። “አባይ አባይ፣ የሀገር ሀብት የሀገር ሰላይ” “አባይ ጉደል ብለው፣ አለኝ በትህሳስ፤ የማን ልብ ይችላል፣ እስከዚያው ድረስ።” ስለተፈጥሮ ሀብታችን ስንዘምርና ስንተርት አድገን፣ ሀገራችንን የድርቅና ረሃብ ምሳሌ ሆና መዝገበ ቃላት ውስጥ … [Read more...] about ተፈትነን እንጂ ወድቀን አናውቅም
ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ
የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ጋዜጠኛ ፍፁም ብርሃኔ እና የአይጋ ፎረም ዋና አዘጋጅና የኢትዮጵያ ተወካይ ጋዜጠኛ ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር መዋላቸዉ ተነግሯል፡፡ ልዩ ዘመቻዎች ሃይል 2ኛ ኮማንዶ ብርጌድ 3ኛ ኮማንዶ ሻለቃ በትግራይ ክልል ህግ በማስከበር ዘመቻ አመርቂ ግዳጅ መፈፀማቸው ተገልጿል፡፡ በዚህም የትግራይ ሚዲያ ሃውስ ጋዜጠኛ ፍፁም ብርሃኔ እና የአይጋ ፎረም ዋና አዘጋጅና የኢትዮጵያ ተወካይ ጋዜጠኛ ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ የ3ኛ ሻለቃ ዋና አዛዥ ሻለቃ ደረጄ ዴቢሳ እንደገለፁት ፣ በትግራይ በተደረገው ህግን በማስከበር ዘመቻ ጠላት የሚመካባቸውን ምሽጎች በሶሮቃ፣ በዳንሻ፣ በባካር፤ በመሶበር፤ በጨርጨርና በአይደፈር ተራሮች ላይ የተገነቡ ምሽጎችን በመስበር የጠላትን ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን መቆጣጠር ተችሏል ብለዋል፡፡ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር … [Read more...] about ፍፁም ብርሃኔና ታምራት የማነ በቁጥጥር ሥር ዋሉ
“ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
ስድስተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከቀደምቶቹ አምስት ምርጫዎች ለየት ያለና ሕዝቡ በምርጫ ሒደት እምነት እንዲያገኝ የሚያስችለው እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ እንዲሁም መንግሥት በተደጋጋሚ ሲያስተጋቡ ቆይተዋል፡፡ ይኼ ምርጫ በመንግሥት ትኩረት እንደተሰጠው ከሚያሳዩ ጉዳዮች አንዱ የተመደበለት በጀት መጠን ሲሆን፣ በአገሪቱ የምርጫ ታሪክ ከፍተኛ የሆነው 2.5 ቢሊዮን ብር ለምርጫ ዝግጅት በፓርላማ ፀድቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሳቢያ ምርጫው በአንድ ዓመት እንዲራዘም ከተደረገ በኋላ፣ ቦርዱ ለፓርላማ የ1.1 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ ይኼ ከመንግሥት የቀረበለት በጀት ሲሆን፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሽግግር የምርጫ ድጋፍ አማካይነት ደግሞ፣ በዓይነት የሚደረግ 1.8 ቢሊዮን ብር ገደማ … [Read more...] about “ለአንድ ፓርቲ የማደላ ከሆነ ሄጄ እዚያው ፓርቲ እገባለሁ” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ