በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ ተስፋን-በጥንቃቄ (cautious optimism) ካነገቡት ሰዎች አንዱ ነኝ። የተስፋዬ መሠረቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥልጣን የመጡበት መንገድ፣ የገቧቸው ቃልኪዳኖች እና አሁን የታየው መረጋጋት ናቸው። አሁን የታየው መረጋጋት ስል የቄሮዎች የአደባባይ ተቃውሞ መቆሙን ማለቴ አይደለም። ተቃዋሚዎችን እያሳደዱ መከታተል፣ ማዋከብ እና ማሰር ርቀን ሳንሔድ አምና ከነበረው አንፃር እንኳ ልዩነቱ የትየለሌ ነው። ለዚህ የራሴን ስሜት እና ተሞክሮ ነው በምሳሌነት የማቀርበው። በፊትም አሁንም ሐሳቤን በነጻነት እገልጻለሁ። ነገር ግን አምና እና ካቻምና ከያንዳንዱ ጽሑፎቼ/ንግግሮቼ ቀጥሎ እስር ይመጣል እያልኩ እየሰጋሁ ነበር የማደርገው። አሁን ምን ያክል ይዘልቃል የሚለው ቢያሰጋኝም እታሰራለሁ እያልኩ በየደቂቃው አልባትትም። በፊት ሲያስሩ፣ ሲያዋክቡ እና ሲከስሱ ከነበሩት … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትሩን ከራሳቸው ማዳን!
abiy
ኤች አር 128 ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የኛ ሚና
በቅርቡ አሜሪካ የሚኖሩት ወገኖቻችን በተባበረ ጥረታቸው ለብዙ ጊዜ ሲዋጉለት የነበረውንና የኢትዮጵያን መንግሥት ቢያንስ ቢያንስ ወደ ተከላካይነት ሊያወርደው ይችላል ተብሎ የታመነበት የአሜሪካ ኮንግረስ ውሳኔ በአደባባይ ለመላው ዓለም ሲታወጅ የተሰማን ደስታ ወሰን አልነበረውም። እኛ የአንጋፋው ትውልድ፣ ከሩቅ ሆነን ሲመቸን ብቻ “በርቱ” እያልን “ድጋፍ” ስንሰጣቸው የነበርነውን ይህን ያህል ያስደስተን፣ በቦታው ሆነው ሌት ተቀን ሳይታክቱ ከስቴት ወደ ስቴት እየተደዋወሉ በተወካዮቻቸው የኮንግረስ አባላት ዘንድ በመደወልና በመጻፍ ተጽዕኖ እያሳደሩ በመጨረሻ ላይ የለፉለት ግቡን ሲመታ ምንኛ እንደተደሰቱ ገምቼ እኔም በጣም ተደሰትኩላቸው። ብዙዎቹ እንደነገሩኝ ከሆነ፣ ያን ቀን በጥዋት ተነስተው ወደ ካፒቶል በማምራት፣ አሰልቺውን የጸጥታ ምርመራ በትዕግሥት አልፈው ወደ ኮንግሬስ ተወካዮቻቸው ቢሮ … [Read more...] about ኤች አር 128 ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የኛ ሚና
የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”
ዶር. ዓቢይና አቶ ለማ መገርሳ በኢትዮጵያ መድረክ ላይ መታየት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ የተአምር አገር መሆንዋን አስታወስሁና እግዚአብሔር ፊቱን ወደኢትዮጵያ መመለሱን ተረዳሁ፤ ከዚያም በላይ ያለፈው ጠቅላይ ሚኒስትር እናቱን በመውቀስና በመመጻደቅ ጀመረ፤ አዲሱ ደግሞ እናቱን በማወደስ መጀመሩ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ ያለውን እምነት በአደባባይ ደጋግሞ በመግለጹ አከበርሁት፤ አከብረዋለሁ። ከዚህ በፊት ሦስት ጊዜ በፌስቡክ የጻፍሁትን ልድገመው፤ አንድ፤ በ1965 በወሎ ችጋር ዘመን በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች እርዳታ ለማድረግ በምንሯሯጥበት ጊዜ አንዳንድ የኢሕአፓ አባሎች ለተራቡት እርዳታ መሰብሰብ አብዮቱ እንዳይመጣ ማድረግ ነው እያሉ ይቃወሙን ነበር፤ ነፍሱን ይማረውና አብርሃም ደሞዝና እኔ ተቆጥተንና አስፈራርተን አደብ እንዲገዙ አድርገናቸው ነበር፤ ዛሬ ደግሞ … [Read more...] about የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”
ጠ/ሚ/ር አብይ “የወልቃይት ኮሚቴ አባላቱን ከወንበር ተነስቶ ይቅርታ ጠይቋል”
“እኛ ትግሬ አንጠላም፣ እነሱ ግን አሁም ያሳድዱናል። ለምን ያሳድዱናል?” የወልቃይት አማራ ማንነት ኮሚቴ በመቀሌ ንግግር ከፍተኛ አቧራ ያስነሳውን የወልቃይትን ጉዳይ ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ከኮሚቴው አባላት ጋር በመነጋገር መቁዋጫ አድርጎለታል። በቅድሚያ ጎንደር ላይ ባደረገው ንግር ይህንን ብሎ ነበር፤ "የወልቃይትን ጉዳይ በተመለከተ በህግ አግባብ ሊፈታ እንደሚችል ህዝቡ ማመን አለበት። ህገ መንግስቱ ይህን ጉዳይ ሊፈታ ይችላል። በቀጣይም ከወልቃይት ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አደርጋለሁ ብለዋል፤ጠቅላይ ሚኒስትሩ። በመወያየት ያሉ ጥያቄዎች መመለስ እንችላለን። ዋናው ነገር በዚህ ሂደት ውስጥ ሀይል የተቀላቀለበት እና ወደ ቁርሾ በሚያስገባ መንገድ መሆን እንደሌለበት ህዝቡ ሊያውቅ ይገባል”። ከማህበራዊ ድረገጽ በተገኘ መረጃ ደገሞ ከወልቃይት ኮሚቴ አባላት ጋር … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር አብይ “የወልቃይት ኮሚቴ አባላቱን ከወንበር ተነስቶ ይቅርታ ጠይቋል”
አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?
የዶ/ር አብይ መሾም “ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ” ይሆን? የዶ/ር መረራ ጥያቄ ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ቃለምልልስ የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በአዲሱ ጠ/ሚ/ር ሹመትና የወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አካሄድ ከኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር አንጻር ትንታኔ ሰጥተዋል። “ኢህአዴግ ለምን ተዘጋጅቷል?” የሚሉት መረራ ቀለል ያሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያስከትላሉ፤ “ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ ለሃቀኛ የፖለቲካ ውድድር (ኢህአዴግ) ተዘጋጅቷል ወይ?” በማለት ይጠይቃሉ። ራሳቸው ሲመልሱትም “ይህንን ካሁኑ ለመገመት ያስቸግራል” ይላሉ። የጠ/ሚ/ሩ ተስፋ የተሞላበትን ንግግሮች ሁሉ መልካም መሆናቸውን ቢገልጹም እርሳቸው እንደ ዜጋ እና ድርጅታቸውም እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የአብይ አህመድን ንግግሮችና የወደፊቱን ሁኔታ “ጥንቃቄ የተሞላበት … [Read more...] about አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?
ህወሓት እስክንድርን ከአገር እንዳይወጣ በመከልከል ባላሰበው ማነቆ ውስጥ ገባ
በኔዘርላንድ በሚደረግ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል 50ኛ ዓመት ክብረበዓል ላይ ለመገኘት ተጋብዞ የነበረው እስክንድር ነጋ ሐሙስ ሌሊት ለአርብ ጠዋት ቦሌ ላይ ከአገር እንዳወጣ ታግቷል። ጎልጉል ባገኘው መረጃ መሠረት ጉዳዩ ህወሓትን ትልቅ ቅርቃር ውስጥ ከቶታል። ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተሉ የነበሩት የመብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት ይህ ፈጽሞ መከሰት ያልነበረበት ጉዳይ መሆኑን በመጥቀስ ጠ/ሚ/ር አብይ በጉዳዩ ላይ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጡበት ጠይቀዋል። ሌላው ለጉዳዩ ቅርበት ያለውና ክስተቱ እንደተፈጸመ አጭር ዘገባ ያሰራጨው ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ “ከሌሊቱ 8 ሰዓት ቦሌ ያሉ የደህንነት አካላት ፓስፖርቱን ቀምተው አትሄድም ብለውታል። የከለከሉበትን ምክንያቱን ግን አልገለጹም” ብሏል። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከቦሌ አካባቢ ባገኘው መረጃ መሠረት እስክንድርን … [Read more...] about ህወሓት እስክንድርን ከአገር እንዳይወጣ በመከልከል ባላሰበው ማነቆ ውስጥ ገባ
“መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” ጠ/ሚ/ር ዓብይ አህመድ
"መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው፤" እየተባለ ጆሮዋችን ሲደነቁርባት በነበረ አገር አዲሱ ጠቅላይ ሚ/ር ዓብይ አህመድ “መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” በማለት ለኢትዮጵያ የሚመጥን ንግግር ኣድርገዋል። ይህንን አስመልክቶ ሪፖርተር ያጠናቀረው ዘገባ አንዲህ ይነበባል። "ኢትዮጵያውያን ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ደግሞ ኢትዮጵያ ነን" ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በፓርላማ ሲሰየሙ ባደረጉት ንግግር፣ በሕዝብ ዘንድ ትኩረትን ከሳቡት ጉዳዮች መካከል የቤተሰብ ጉዳይ አንዱ ነው። የሰባት ዓመት ልጅ እያሉ ሩቅ፣ ጥልቅና ረቂቅ ራዕይ በውስጣቸው የተከሉትን፣ ያሳደጓቸውንና ለፍሬ ያበቋቸውን ወላጅ እናት ለማመሥገን እንዲፈቀድላቸው ሲጠይቁ ብዙዎች ልባቸው ተነክቷል። እናታቸው … [Read more...] about “መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” ጠ/ሚ/ር ዓብይ አህመድ
“(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
ማክሰኞ መጋቢት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. ምሽት እኩለ ሌሊት እየተቃረበ እያለ የተሰማው ሰበር ዜና በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ያነጋገረ ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከኢሕአዴግ ሊቀመንበርነታቸውና ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው ለመልቀቅ መወሰናቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ፣ ተተኪያቸው ማን ይሆን የሚለው በመላ አገሪቱ ዋነኛ መነጋገሪያ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በተለይ ማክሰኞ መጋቢት 11 ቀን 2010 ዓ.ም. ተተኪውን የግንባሩን ሊቀመንበር ለመምረጥ ስብሰባ የተቀመጠው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ለአንድ ሳምንት በመቆየቱ፣ በርካቶች በመላ ምቶችና በሴራ ንድፈ ሐሳቦች እንዲጨናነቁ አድርጓቸዋል፡፡ የአገሪቱ ፖለቲካ ለትንተና እስከሚያስቸግር ድረስ የተለያዩ መረጃዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች በመሰማታቸው፣ የተተኪው ማንነት ብዙዎችን ቢያሳስብ አይገርምም … [Read more...] about “(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል። “በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ። በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ … [Read more...] about ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
እርግጥ እንደ መለስ ዜናዊ ባለ ሙሉ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል? ከልክ በላይ ለጥጠው፤ እንደ ልብ አንጠልጥል ፊልም ያቆዩትን ፍትግያ ትናንት በዜና ሲሰብሩት ደስታቸውን ይገልጹ የነበሩት ዜጎች ጥቂት አልነበሩም። ወትሮውን በስብሻለው ከሚለን ስራዓት አዲስ ነገር የሚጠብቅ ተስፈኛ ቢደሰት ብዙም አይደንቅም። የጠቅላይ ሚንስትር እንጂ የስራዓት ለውጥ መች ተመለከትን? ዶ/ር አብይ አህመድ በዚህ ቀውጢ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ መመረጡ ግን ከክብሩና ከስልጣኑ ይልቅ ፈተናው ያመዝናል። ለሶስት ቀናት ተብሎ የተጀመረው ግብግብ ይሉት ክርክር በተነገረለት ቀን መቋጨት ያለመቻሉ በራሱ የሚነግረን ነገር ነበር። አወዛጋቢው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ፣ ፓርላማ ላይ በጸደቀበት ወቅት ዶ/ር አብይ በስፍራው ባለመገኘታቸው የህወሃት ሰዎች ክፉኛ እንደተበሳጩ አይተናል። ይህንን ቅሬታ በብሎገሮቻቸውም … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች