• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠ/ሚ/ር አብይ “የወልቃይት ኮሚቴ አባላቱን ከወንበር ተነስቶ ይቅርታ ጠይቋል”

April 20, 2018 11:13 am by Editor 5 Comments

  • “እኛ ትግሬ አንጠላም፣ እነሱ ግን አሁም ያሳድዱናል። ለምን ያሳድዱናል?” የወልቃይት አማራ ማንነት ኮሚቴ

በመቀሌ ንግግር ከፍተኛ አቧራ ያስነሳውን የወልቃይትን ጉዳይ ጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ከኮሚቴው አባላት ጋር በመነጋገር መቁዋጫ አድርጎለታል።

በቅድሚያ ጎንደር ላይ ባደረገው ንግር ይህንን ብሎ ነበር፤

“የወልቃይትን ጉዳይ በተመለከተ በህግ አግባብ ሊፈታ እንደሚችል ህዝቡ ማመን አለበት። ህገ መንግስቱ ይህን ጉዳይ ሊፈታ ይችላል። በቀጣይም ከወልቃይት ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አደርጋለሁ ብለዋል፤ጠቅላይ ሚኒስትሩ። በመወያየት ያሉ ጥያቄዎች መመለስ እንችላለን። ዋናው ነገር በዚህ ሂደት ውስጥ ሀይል የተቀላቀለበት እና ወደ ቁርሾ በሚያስገባ መንገድ መሆን እንደሌለበት ህዝቡ ሊያውቅ ይገባል”።

(ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎንደር ሲገቡ ፎቶ ከኢንተርኔት የተገኘ)

ከማህበራዊ ድረገጽ በተገኘ መረጃ ደገሞ ከወልቃይት ኮሚቴ አባላት ጋር ሲነጋገር ይህንን ማለቱ ተዘግቧል፤ “የጎንደር ሕዝብ አኩርፎብሃል አትሂድ ተብዬ ነበር። ቢበዛ ቆንጥጦ ቢያስተምረኝ ነው ብየ መጥቻለሁ”።

ጌታችው ሽፈራው ደግሞ ከተሰብሳቢዎቹ የተገኘ መረጃ ያለውን በዚህ መልኩ አቀናብሮታል፤

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኮሚቴ አባላቱን ከወንበር ተነስቶ ይቅርታ ጠይቋል

ዶ/ር አብይ አቶ አታላይ ዛፌን፣ጌታቸው አደመን፣ ተሻገር ወ/ሚካኤልና ወረታው አዛናውን ጠርቶ አናግሯል። የኮሚቴ አባላቱን ከወንበር ተነስቶ ይቅርታ ጠይቋል።

በውይይቱ ወቅት አቶ አታላይ ዛፌ “ወንድ ልጅ ራሱን ይዞ ያለቀሰበት ጊዜ ቢኖር እርስዎ መቀሌ ላይ በወልቃይት ጉዳይ ከተናገሩ በኋላ ነው። ወልቃይት ብዙ ስቃይ ይፈፀማል። በአማርኛችን እንኳ መዝፈን አንችልም። አስከሬን በወጉ መቅበር አንችልም። አሁንም በወልቃይት ጉዳይ እስር ቤት የሚገኙ አሉ። በወልቃይት ጉዳይ 9 ወጣቶች በቅርቡ ተከሰዋል። እኛ ትግሬ አንጠላም፣ እነሱ ግን አሁም ያሳድዱናል። ለምን ያሳድዱናል? የወልቃይትን ጥያቄ ያነሳው ዲያስፖራ አይደለም። ዳያስፖራም ቢሆን ከባህር አሳ፣ ከኮንቴነር ሞት ተርፎ የተሰደደ ወገናችን ነው፣ ሲሞት አስከሬኑ ታሽጎ የሚላክልን ወገናችን ነው። ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱልም እንፈልጋለን። ነገር ግን እኛ በዳያስፖራ አንመራም” ሲል ለዶ/ር አብይ ቅሬታውን አቅርቧል።

ዶ/ር አብይም ወደፊት ከኮሚቴዎቹ ጋር እንደሚወያይ፣ መቀሌ የመለሰው ጥያቄ ከማንነት ጋር በቀጥታ የተገናኘ ሳይሆን አንድ ሰው “ዳያስፖራ እያፋጀን ነው” ብሎ ለጠየቀው ጥያቄ እንደሆነ ገልፆላቸዋል። “የወልቃይት ጉዳይ በእኔ በአንድ ሰው፣ በስብብሰባ አዳራሽ የሚፈታ አይደለም” እንዳለም ታውቋል።

(መረጃዎቹ ከተስሳቢዎቹ የተገኙ ናቸው)

ህወሓት/ኢህአዴግ “ፓርላማ” ባለው ስብስብ በሶማሊያ የሞቱት ወገኖቻችን ስንት እንደሆኑ እንዲነገር ለሞተው መለስ ዜናዊ ጥያቄ ሲቀርብለት ፓርላማው የመጠየቅ መብት እንደሌለውና ማንም እንደማያገባው በእብሪት መናገሩ የሚረሳ አይደለም። ከዚህም ሌላ በምርጫ 1997 ለሞቱት ሰዎች ይቅርታ ትጠይቃለህ ወይ በማለት የቢቢሲ ሃርድ ቶክ ጋዜጠኛ ስቲፈን ሳኩር ሲጠይቀው እብሪተኛው መለስ ሰው ስለሞተ አዝናለሁ፤ ተጣርቶ እስኪታወቅ ግን ይቅርታ አልጠይቅም ማለቱ የሚዘነጋ አይደለም።

ጎልጉል፥ የድረገጽ ጋዜጣ

(መግቢያ ፎቶ፤ ሪፖርተር)

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, Full Width Top, gondar, Middle Column, wolkayit

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    April 21, 2018 03:39 am at 3:39 am

    ወልቃይት ምን ጊዜም ቢሆን የትግራይ ክልል ህዝብ ነው!! ብዙ ማስረጃ ኣለኝ!!

    Reply
    • aradaw says

      April 24, 2018 01:39 am at 1:39 am

      Let us hear and see.

      Reply
  2. Joe Mama says

    April 21, 2018 08:26 am at 8:26 am

    Dr. Abeye You got the power with the help of the Ethiopian people take charge!!!!

    Reply
  3. Joe Mama says

    April 21, 2018 08:44 am at 8:44 am

    Dr abeye You are between a rock and a hard place. We understand your position try to do your best
    or explain to the Ethiopian people if mafia hooligans in your way and resign with honor
    don’t be like you know who

    Reply
  4. Ezira says

    April 21, 2018 10:58 pm at 10:58 pm

    ጎበዝ!አንርሳ
    ጉጭማው የትግሬ ወያኔ አለቃ መለስ ዜናዊ እኮ ስልጣኑን ከጨበጠ ጀምሮ እስኪደፋ ድረስ አንድም ጊዜ ፊቱ ተፈትቶ አይታችሁት ታውቃላችሁ ? በጭራሽ። ምክኒያቱም የትግሬው ወያኔ ነፃ አውጭ ግንባር እንደ ግንባር ፡ ጉጭማው ለገሰ ዜናዊ ደግሞ እንደ ግል የነጮቹ ባሪያ ሆኖ ሊያገለግል የተሸጠ መሸጦ ስለነበር ነርቭስ ነበር – አግሬሲብም ነበር። ምክንያቱም ሲጀመር የተገዛ ባሪያ ስለነበር ለገዙት አለቆቹ ግሩም ባሪያ መሆኑን ለማሳየት ሲተጋ ……የኢትዮፕያ ህዝብ ደግሞ የቆመበትን ምንጣፍ ከታች እየሳበ ይገዘግዘው ነበር። በዚህ ምክንያት የበታችነቱን ለመደበቅ ዳቦ በቀደደው አፉ “ወራዳ እደገመዋለሁ ወራዳ”፡ እያለ ውስጣዊ ጭንቀቱን በስድብ ያንፀባርቅ ነበር። የሚሳደብበት አፉም ስለሚደረቅ በየደቂቃው ዉሃ ይጠጣ ነበር። በመጨረሻም ተቀጣሪ ባሪያ ማንነቱና የተቀመጠበት የምንሊክ ወንበር ተቃርኖ ነቀርሳ ሆኖ ወደ መቃብር ከተተው። Thanks God

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule