• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች

April 2, 2018 03:03 pm by Editor Leave a Comment

በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል።

“በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ” ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ።

በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ እና የእምነት ሰው ናቸውና፣ ይህንን ለማድረግ እንጂ ለማለት ብቻ አልተናገሩትም።

ከየት ጫፍ ተነስተው የት ጫፍ ላይ እንደደረሱ ለተመለከቷቸው ሁሉ፤ ከአንደበታቸው የወጣው ይህ ቃል ምን ያህል በተግባር ሊመነዘር እንደሚችል ይገምታሉ።

ሃገሪቷን ሸብቦ የያዛት የዘረኝነትን በሽታ እናጥፋ ብለዋል። “ማንነታችን የተሳሰረ፣ የተጋመደ እና የተዋሃደ ነው” ይላሉ። ይህችን አባቶቻችን በደማቸው የቆዩዋት ኃያል ሃገር ወደ ቀድሞዋ ታላቅነትዋ እንመልሳት፤ በርካታ ዘመን ተሻጋሪ የሆነ ታሪክ አለን ብለው ሲናገሩ ለሚሰማ ሰው እውነትም ይህ ሰው ሊመራኝ ይገባል ማለቱ እንግዳ አይሆንም። ይህ በእኛ ዘመን አልተለመደማ!

ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ ስርዓት ለመገንባት የህዝብ ፍላጎት እና ይሁንታ ያለው መንግስት መመስረት እንደሚገባው በአጽንኦት ተናግረዋል። ተቀናቃኝ ያሉዋቸውን የተቃዋሚ ሃይሎችም ጥሪ አቅርበዋር። ለሃገሪቱ ባይተዋር ሳይሆኑ የለውጡ አካል እንዲሆኑ ጋብዘዋል።

የሰው ልጆች ነጻነት ከመንግስት የሚቸር ስጦታ ሳይሆን የሰው ልጅ በተፈጥሮ ያገኘው ጸጋ እንደሆነ መናገራቸው ስለ ፕሬስ ነጻነት መቆማቸን ይጠቁመናል።

ከዲያስፖራ ጋር ያለው የሻከረ ግንኙነት ጠፍቶ ዲያስፖራውም በሂደቱ እንዲሳተፍ ተማጽነዋል። ያለፈውን ምዕራፍ ዘግተን በአዲስ ምዕራፍ እንጓዝ ሲሉ ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ጠርተዋል። ጽንፈኛ ብሎ የሚሳደብ እንጂ፤ ይቅር እንባባል የሚል ልብ የሚነካ ጥሪ ከየትኛውም መሪ አልሰማንም። ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ ብሎ የተናገረ መሪ እስካሁንም አላየንም። ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ብሎስ የተናገረ የኢህአዴግ ሰው መች ተሰምቶ ይታወቃል።

ከኤርትራ መንግስት ጋር ስለሚኖረው እርቅ እና ሰላም እቅድም ጥቅሰዋል። ሁለቱ ሃገር ህዝቦች በደም የተሳሰረ መሆናቸው እና ለክልሉ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ለኤርትራ መንግስትም ጥሪ አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያ በርካታ የለውጥ እድል እንደነበራት እና በአመራር ድክመት ሳብያ እነዚህ እድሎችዋን ሳትጠቀም መቅረትዋን ብቻ አልነበረም የተናገሩት፤ እሳቸውን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ያመጣውን ይህንን እድልም ይጠቅሳሉ። የንግግራቸው ቁልፍ ይህ ይመስላል። ይህ እድል እንዳያመልጥ የሚል ይመስላል። ብሄራዊ መግባባትን ፈጥሮ ሁሉን ያቀፈ ፍትሃዊ ስርዓትን መመስረት።

የዶ/ር አብይ ንግግር፣ በመለስ ራዕይ ጀምሮ በመለስ ራዕይ ካበቃው ከኃይለማርያም ደሳለኝ አሰልቺ ንግግር ጋር የሰማይ እና የምድር አይነት ርቀት አለው።

ከኃይለማርያም የተረከቡት ይህ የስልጣን ሽግግር ከጊዜው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ሁኔታዎች ጋር እኩል የሚጓዝና በህዝብ ፍላጎት የሚገዛ፤ ህዝብን አለቃው አድርጎ የሚያገለግል ስርዓት እየገነባን መሆኑን አብስሮናል።

የዶ/ር አብይ ንግግር ፓርላማው ለመጥራት እንኳ ይቀፍፈው በነበረው ኢትዮጵያዊነት ጀምሮ በዚያው ነው የጨረሰው። “ኢትዮጵያ የሁላችን ቤት ናት። ልዩነት እርግማን ሳይሆን በረከት ነው” ከሚለው የመቀነስ ሳይሆን የድምር ፖለቲካ እሳቤ – ከሳጥን ውስጥ የወጣ አዲስ እሳቤ ነው።

በርግጥ ይህ የስልጣን ሽግግር ብዙ የተከፈለበት የህዝብ ትግል ውጤት መሆኑ ባይዘነጋም፣ መላው ሕዝብ በእኝህ መሪ ደስተኛ መሆኑ ከፈጣሪ የመጣ ተዓምር ነው ያሰኛል።

አለም በስጋት እና በጉጉት እየጠበቀው ያለው ይህ የለውጥ ሽግግር በተግባር ሲተረጎም ፈተናዎች ሊገጥሙት ይችላል። የሁሉም ድጋፍ ሲታከልበት የተሳካ ለውጥ እንደሚመጣ እርግጥ ነው። የቀድሞው ወዳጃቸው፣ ኸርማን ኮኸን በትዊተር ለዶክተር አብይ በላኩት መልዕክት “አይዞህ ስራህን በድፍረት ስራ፤ አለም አቀፉ ህብረተሰብ ካንተ ጋር ነው” ብለዋል።

የሹመት ንግግር በተናጋሪው መጻኢ ዘመን ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የኦባማ ንግግር በተግባር ባይተረጎምም ብዙዎችን ልብ ገዝቶ ነበር። ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬነዲ በቀዝቃዛው ጦርነት ሰሞን ምዕራብ በርሊን ተሰብስቦ ለነበረ ህዝብ Ich bin ein Berliner በርሊናዊ ነኝ፤ ሲሉ በመናገር የመላ ጀርመንን ልብ ሰልበው እንደነበርም ታሪክ ያወሳል። ይህን ያሉት ኮምኒዝምን ለመምታት እንጂ ለሕዝበኝነት አልነበረም።

የዶ/ር አብይ ንግግር የሕዝብን ልብ ለመግዛት የሚደረግ ቢሆንም ይህ ክፋት የለውም። የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል እንዲሉ … በቃሉ የሚኖር ሰው ከአነሳሱ ያስታውቃል። ስልጣን … የማንም ስልጣን ገደል ይግባ! ከሀገር በላይ አይደለም:: ከማናችንም ስልጣናችን፣ ክብራችን፣ ከሀገር በታች ነው!” ብለውን ነበር ኦቦ ለማ መገርሳ።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy, eprdf, Left Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule