• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች

April 2, 2018 03:03 pm by Editor Leave a Comment

በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል።

“በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ” ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ።

በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ እና የእምነት ሰው ናቸውና፣ ይህንን ለማድረግ እንጂ ለማለት ብቻ አልተናገሩትም።

ከየት ጫፍ ተነስተው የት ጫፍ ላይ እንደደረሱ ለተመለከቷቸው ሁሉ፤ ከአንደበታቸው የወጣው ይህ ቃል ምን ያህል በተግባር ሊመነዘር እንደሚችል ይገምታሉ።

ሃገሪቷን ሸብቦ የያዛት የዘረኝነትን በሽታ እናጥፋ ብለዋል። “ማንነታችን የተሳሰረ፣ የተጋመደ እና የተዋሃደ ነው” ይላሉ። ይህችን አባቶቻችን በደማቸው የቆዩዋት ኃያል ሃገር ወደ ቀድሞዋ ታላቅነትዋ እንመልሳት፤ በርካታ ዘመን ተሻጋሪ የሆነ ታሪክ አለን ብለው ሲናገሩ ለሚሰማ ሰው እውነትም ይህ ሰው ሊመራኝ ይገባል ማለቱ እንግዳ አይሆንም። ይህ በእኛ ዘመን አልተለመደማ!

ዘላቂ እና ሁሉን አቀፍ ስርዓት ለመገንባት የህዝብ ፍላጎት እና ይሁንታ ያለው መንግስት መመስረት እንደሚገባው በአጽንኦት ተናግረዋል። ተቀናቃኝ ያሉዋቸውን የተቃዋሚ ሃይሎችም ጥሪ አቅርበዋር። ለሃገሪቱ ባይተዋር ሳይሆኑ የለውጡ አካል እንዲሆኑ ጋብዘዋል።

የሰው ልጆች ነጻነት ከመንግስት የሚቸር ስጦታ ሳይሆን የሰው ልጅ በተፈጥሮ ያገኘው ጸጋ እንደሆነ መናገራቸው ስለ ፕሬስ ነጻነት መቆማቸን ይጠቁመናል።

ከዲያስፖራ ጋር ያለው የሻከረ ግንኙነት ጠፍቶ ዲያስፖራውም በሂደቱ እንዲሳተፍ ተማጽነዋል። ያለፈውን ምዕራፍ ዘግተን በአዲስ ምዕራፍ እንጓዝ ሲሉ ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ጠርተዋል። ጽንፈኛ ብሎ የሚሳደብ እንጂ፤ ይቅር እንባባል የሚል ልብ የሚነካ ጥሪ ከየትኛውም መሪ አልሰማንም። ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ ብሎ የተናገረ መሪ እስካሁንም አላየንም። ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች ብሎስ የተናገረ የኢህአዴግ ሰው መች ተሰምቶ ይታወቃል።

ከኤርትራ መንግስት ጋር ስለሚኖረው እርቅ እና ሰላም እቅድም ጥቅሰዋል። ሁለቱ ሃገር ህዝቦች በደም የተሳሰረ መሆናቸው እና ለክልሉ እድገት ወሳኝ በመሆኑ ለኤርትራ መንግስትም ጥሪ አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያ በርካታ የለውጥ እድል እንደነበራት እና በአመራር ድክመት ሳብያ እነዚህ እድሎችዋን ሳትጠቀም መቅረትዋን ብቻ አልነበረም የተናገሩት፤ እሳቸውን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ያመጣውን ይህንን እድልም ይጠቅሳሉ። የንግግራቸው ቁልፍ ይህ ይመስላል። ይህ እድል እንዳያመልጥ የሚል ይመስላል። ብሄራዊ መግባባትን ፈጥሮ ሁሉን ያቀፈ ፍትሃዊ ስርዓትን መመስረት።

የዶ/ር አብይ ንግግር፣ በመለስ ራዕይ ጀምሮ በመለስ ራዕይ ካበቃው ከኃይለማርያም ደሳለኝ አሰልቺ ንግግር ጋር የሰማይ እና የምድር አይነት ርቀት አለው።

ከኃይለማርያም የተረከቡት ይህ የስልጣን ሽግግር ከጊዜው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ሁኔታዎች ጋር እኩል የሚጓዝና በህዝብ ፍላጎት የሚገዛ፤ ህዝብን አለቃው አድርጎ የሚያገለግል ስርዓት እየገነባን መሆኑን አብስሮናል።

የዶ/ር አብይ ንግግር ፓርላማው ለመጥራት እንኳ ይቀፍፈው በነበረው ኢትዮጵያዊነት ጀምሮ በዚያው ነው የጨረሰው። “ኢትዮጵያ የሁላችን ቤት ናት። ልዩነት እርግማን ሳይሆን በረከት ነው” ከሚለው የመቀነስ ሳይሆን የድምር ፖለቲካ እሳቤ – ከሳጥን ውስጥ የወጣ አዲስ እሳቤ ነው።

በርግጥ ይህ የስልጣን ሽግግር ብዙ የተከፈለበት የህዝብ ትግል ውጤት መሆኑ ባይዘነጋም፣ መላው ሕዝብ በእኝህ መሪ ደስተኛ መሆኑ ከፈጣሪ የመጣ ተዓምር ነው ያሰኛል።

አለም በስጋት እና በጉጉት እየጠበቀው ያለው ይህ የለውጥ ሽግግር በተግባር ሲተረጎም ፈተናዎች ሊገጥሙት ይችላል። የሁሉም ድጋፍ ሲታከልበት የተሳካ ለውጥ እንደሚመጣ እርግጥ ነው። የቀድሞው ወዳጃቸው፣ ኸርማን ኮኸን በትዊተር ለዶክተር አብይ በላኩት መልዕክት “አይዞህ ስራህን በድፍረት ስራ፤ አለም አቀፉ ህብረተሰብ ካንተ ጋር ነው” ብለዋል።

የሹመት ንግግር በተናጋሪው መጻኢ ዘመን ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የኦባማ ንግግር በተግባር ባይተረጎምም ብዙዎችን ልብ ገዝቶ ነበር። ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬነዲ በቀዝቃዛው ጦርነት ሰሞን ምዕራብ በርሊን ተሰብስቦ ለነበረ ህዝብ Ich bin ein Berliner በርሊናዊ ነኝ፤ ሲሉ በመናገር የመላ ጀርመንን ልብ ሰልበው እንደነበርም ታሪክ ያወሳል። ይህን ያሉት ኮምኒዝምን ለመምታት እንጂ ለሕዝበኝነት አልነበረም።

የዶ/ር አብይ ንግግር የሕዝብን ልብ ለመግዛት የሚደረግ ቢሆንም ይህ ክፋት የለውም። የማያጠግብ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል እንዲሉ … በቃሉ የሚኖር ሰው ከአነሳሱ ያስታውቃል። ስልጣን … የማንም ስልጣን ገደል ይግባ! ከሀገር በላይ አይደለም:: ከማናችንም ስልጣናችን፣ ክብራችን፣ ከሀገር በታች ነው!” ብለውን ነበር ኦቦ ለማ መገርሳ።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy, eprdf, Left Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule