• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?

April 19, 2018 11:52 pm by Editor 1 Comment

  • የዶ/ር አብይ መሾም “ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ” ይሆን? የዶ/ር መረራ ጥያቄ

ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ቃለምልልስ የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በአዲሱ ጠ/ሚ/ር ሹመትና የወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አካሄድ ከኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር አንጻር ትንታኔ ሰጥተዋል።

“ኢህአዴግ ለምን ተዘጋጅቷል?” የሚሉት መረራ ቀለል ያሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያስከትላሉ፤ “ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ ለሃቀኛ የፖለቲካ ውድድር (ኢህአዴግ) ተዘጋጅቷል ወይ?” በማለት ይጠይቃሉ። ራሳቸው ሲመልሱትም “ይህንን ካሁኑ ለመገመት ያስቸግራል” ይላሉ። የጠ/ሚ/ሩ ተስፋ የተሞላበትን ንግግሮች ሁሉ መልካም መሆናቸውን ቢገልጹም እርሳቸው እንደ ዜጋ እና ድርጅታቸውም እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የአብይ አህመድን ንግግሮችና የወደፊቱን ሁኔታ “ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ” በማድረግ እንደሚመለከቱት በመደጋገም ተናግረዋል።

የኦፌኮው ሊቀመንበር ይህንን ያሉበትን ምክንያትም ያብራራሉ፤ ኢህአዴግ ከታሪኩና ካለው ባህርዩ አንጻር ከለውጥ ጋር ትውውቅ የሌለው ድርጅት መሆኑን በእንደምታ ከገለጹ በኋላ ስለ ዶ/ር አብይ ንግግሮች ሲያስረዱ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የሚናገራቸው ወደ መሬት ወርደው በተግባር ላይ ይውላሉ የሚለውን ከኢህአዴግ ታሪክ አንጻር ለመናገር አስቸጋሪ ነው” በማለት ለምን ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ እንደሚያደርጉ ይናገራሉ።

ሆኖም ግን ዶ/ር መረራ ጨለምተኛ አይደሉም፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋቸው እንዳለ ሆኖ ይህንንም ተናግረዋል፤ “ኢህአዴግ ለሃቀኛ ጥልቅ ተሃድሶ ከተዘጋጀ ብሔራዊ ዕርቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይፈጠርበት ምንም ምክንያት የለም፤ተቃዋሚዎቹም ግማሽ መንገድ ሄደው የማይቀበሉበት ምንም ምክንያት የለም” በማለት የወደፊት ተስፋቸውን አስረድተዋል።

ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ቃል መገባቱ ተገቢ ቢሆንም ከዚያ በፊት ግን መፈጸም ያለባቸው ቀዳሚ ተግባራት እንዳሉ የፖለቲካ ምሁሩ መረራ ጉዲና ያስረዳሉ። ዶ/ር አብይ ወደሥልጣን መንበሩ ከመጣ በኋላ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች የሞቱና የታሰሩ መኖራቸውን በመጥቀስ እና ከዛሬ ዐሥር ዓመት ጀምሮ እስካሁን ታስረው የሚገኙ ስም በመዘርዘር “እነዚህን (እስር ቤት) አስቀምጠህ ሕዝብን የሚያማልል ንግግር እያደረግህ ምን ያህል ትቆያለህ?” በማለት ጠ/ሚ/ሩ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ሁለት ጉዳዮች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳትና የፖለቲካ እስረኞችን ሁሉ መፍታት እንደሆነ ተናግረዋል።

ዶ/ር መረራ “ጥርጣሬ” ያሉትንም አልደበቁም፤ “አሁንም ቢሆን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር (ከኢህአዴግ) የጋራ አመራር ርቆ ይሄዳል የሚል ግምት የለኝም፤ ይህ የጋራ አመራር የሚባለው ጠ/ሚ/ሩን እጅ እግር አሥሮ የሚያስቀምጥ ነው ወይስ ፋታ የሚሰጣቸው፤ እንደ አገር ጠቅላይ ሚኒስትር አገሪቱን እንዲመሩ፤ … ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ ስም የሚገባቸውን ቃልኪዳኖችን እንዲፈጽም፣ በተግባር እንዲተረጉም ዕድል ይሰጡታል?” በማለት አብይ አህመድን ጠርንፎ ስለያዘው የኢህአዴግ አሠራር በግልጽ አስረድተዋል።

በመጨረሻም የኦፌኮው ሊቀመንበር “ያልተመለሰ” ያሉትን ጥያቄ ምን እንደሆነ ተናግረዋል፤ “(ኢህአዴግ አብይ አህመድ የመረጠው) ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ ነው ይህንን ጠቅላይ ሚኒስትር ከኦሮሞ ያደረጉት ወይስ በሃቅ ለመለወጥ ነው?” ብለዋል። ሲቀጥሉም ይህ የብዙዎች አመለካከት እንደሆነና እርሳቸውም ይህንኑ በ“ተወሰነ ደረጃ” እንደሚጠረጥሩ በመናገር “(የጠቅላይ ሚ/ሩ) ፈተናው እዚያ ላይ ነው” ብለዋል።

ቃለምልልሱን በድምጽ ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/04/VOA_ዶር-መረራ-ጠሚኒስትር-ዶር-አብይ-በሀገሪቱ-አሉ-የሚሏቸውን-ችግሮች-እንዲፈቱ-ጠየቁ___እስክንድር-ፍሬው-April-18-2018.mp3

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

(ፎቶ፡ ዶ/ር መረራ ከእስር እንደተፈቱ በደጋፊዎቻቸው ታጅበው፤ ©ማኅበራዊ ድረገጽ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, merera, Middle Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    April 19, 2018 08:57 pm at 8:57 pm

    Great.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule