• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?

April 19, 2018 11:52 pm by Editor 1 Comment

  • የዶ/ር አብይ መሾም “ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ” ይሆን? የዶ/ር መረራ ጥያቄ

ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ቃለምልልስ የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በአዲሱ ጠ/ሚ/ር ሹመትና የወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አካሄድ ከኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር አንጻር ትንታኔ ሰጥተዋል።

“ኢህአዴግ ለምን ተዘጋጅቷል?” የሚሉት መረራ ቀለል ያሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያስከትላሉ፤ “ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ ለሃቀኛ የፖለቲካ ውድድር (ኢህአዴግ) ተዘጋጅቷል ወይ?” በማለት ይጠይቃሉ። ራሳቸው ሲመልሱትም “ይህንን ካሁኑ ለመገመት ያስቸግራል” ይላሉ። የጠ/ሚ/ሩ ተስፋ የተሞላበትን ንግግሮች ሁሉ መልካም መሆናቸውን ቢገልጹም እርሳቸው እንደ ዜጋ እና ድርጅታቸውም እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የአብይ አህመድን ንግግሮችና የወደፊቱን ሁኔታ “ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ” በማድረግ እንደሚመለከቱት በመደጋገም ተናግረዋል።

የኦፌኮው ሊቀመንበር ይህንን ያሉበትን ምክንያትም ያብራራሉ፤ ኢህአዴግ ከታሪኩና ካለው ባህርዩ አንጻር ከለውጥ ጋር ትውውቅ የሌለው ድርጅት መሆኑን በእንደምታ ከገለጹ በኋላ ስለ ዶ/ር አብይ ንግግሮች ሲያስረዱ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የሚናገራቸው ወደ መሬት ወርደው በተግባር ላይ ይውላሉ የሚለውን ከኢህአዴግ ታሪክ አንጻር ለመናገር አስቸጋሪ ነው” በማለት ለምን ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ እንደሚያደርጉ ይናገራሉ።

ሆኖም ግን ዶ/ር መረራ ጨለምተኛ አይደሉም፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋቸው እንዳለ ሆኖ ይህንንም ተናግረዋል፤ “ኢህአዴግ ለሃቀኛ ጥልቅ ተሃድሶ ከተዘጋጀ ብሔራዊ ዕርቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይፈጠርበት ምንም ምክንያት የለም፤ተቃዋሚዎቹም ግማሽ መንገድ ሄደው የማይቀበሉበት ምንም ምክንያት የለም” በማለት የወደፊት ተስፋቸውን አስረድተዋል።

ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ቃል መገባቱ ተገቢ ቢሆንም ከዚያ በፊት ግን መፈጸም ያለባቸው ቀዳሚ ተግባራት እንዳሉ የፖለቲካ ምሁሩ መረራ ጉዲና ያስረዳሉ። ዶ/ር አብይ ወደሥልጣን መንበሩ ከመጣ በኋላ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች የሞቱና የታሰሩ መኖራቸውን በመጥቀስ እና ከዛሬ ዐሥር ዓመት ጀምሮ እስካሁን ታስረው የሚገኙ ስም በመዘርዘር “እነዚህን (እስር ቤት) አስቀምጠህ ሕዝብን የሚያማልል ንግግር እያደረግህ ምን ያህል ትቆያለህ?” በማለት ጠ/ሚ/ሩ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ሁለት ጉዳዮች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳትና የፖለቲካ እስረኞችን ሁሉ መፍታት እንደሆነ ተናግረዋል።

ዶ/ር መረራ “ጥርጣሬ” ያሉትንም አልደበቁም፤ “አሁንም ቢሆን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር (ከኢህአዴግ) የጋራ አመራር ርቆ ይሄዳል የሚል ግምት የለኝም፤ ይህ የጋራ አመራር የሚባለው ጠ/ሚ/ሩን እጅ እግር አሥሮ የሚያስቀምጥ ነው ወይስ ፋታ የሚሰጣቸው፤ እንደ አገር ጠቅላይ ሚኒስትር አገሪቱን እንዲመሩ፤ … ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ ስም የሚገባቸውን ቃልኪዳኖችን እንዲፈጽም፣ በተግባር እንዲተረጉም ዕድል ይሰጡታል?” በማለት አብይ አህመድን ጠርንፎ ስለያዘው የኢህአዴግ አሠራር በግልጽ አስረድተዋል።

በመጨረሻም የኦፌኮው ሊቀመንበር “ያልተመለሰ” ያሉትን ጥያቄ ምን እንደሆነ ተናግረዋል፤ “(ኢህአዴግ አብይ አህመድ የመረጠው) ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ ነው ይህንን ጠቅላይ ሚኒስትር ከኦሮሞ ያደረጉት ወይስ በሃቅ ለመለወጥ ነው?” ብለዋል። ሲቀጥሉም ይህ የብዙዎች አመለካከት እንደሆነና እርሳቸውም ይህንኑ በ“ተወሰነ ደረጃ” እንደሚጠረጥሩ በመናገር “(የጠቅላይ ሚ/ሩ) ፈተናው እዚያ ላይ ነው” ብለዋል።

ቃለምልልሱን በድምጽ ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/04/VOA_ዶር-መረራ-ጠሚኒስትር-ዶር-አብይ-በሀገሪቱ-አሉ-የሚሏቸውን-ችግሮች-እንዲፈቱ-ጠየቁ___እስክንድር-ፍሬው-April-18-2018.mp3

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

(ፎቶ፡ ዶ/ር መረራ ከእስር እንደተፈቱ በደጋፊዎቻቸው ታጅበው፤ ©ማኅበራዊ ድረገጽ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, merera, Middle Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    April 19, 2018 08:57 pm at 8:57 pm

    Great.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule