• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?

April 19, 2018 11:52 pm by Editor 1 Comment

  • የዶ/ር አብይ መሾም “ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ” ይሆን? የዶ/ር መረራ ጥያቄ

ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ቃለምልልስ የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በአዲሱ ጠ/ሚ/ር ሹመትና የወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አካሄድ ከኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር አንጻር ትንታኔ ሰጥተዋል።

“ኢህአዴግ ለምን ተዘጋጅቷል?” የሚሉት መረራ ቀለል ያሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያስከትላሉ፤ “ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ ለሃቀኛ የፖለቲካ ውድድር (ኢህአዴግ) ተዘጋጅቷል ወይ?” በማለት ይጠይቃሉ። ራሳቸው ሲመልሱትም “ይህንን ካሁኑ ለመገመት ያስቸግራል” ይላሉ። የጠ/ሚ/ሩ ተስፋ የተሞላበትን ንግግሮች ሁሉ መልካም መሆናቸውን ቢገልጹም እርሳቸው እንደ ዜጋ እና ድርጅታቸውም እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የአብይ አህመድን ንግግሮችና የወደፊቱን ሁኔታ “ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ” በማድረግ እንደሚመለከቱት በመደጋገም ተናግረዋል።

የኦፌኮው ሊቀመንበር ይህንን ያሉበትን ምክንያትም ያብራራሉ፤ ኢህአዴግ ከታሪኩና ካለው ባህርዩ አንጻር ከለውጥ ጋር ትውውቅ የሌለው ድርጅት መሆኑን በእንደምታ ከገለጹ በኋላ ስለ ዶ/ር አብይ ንግግሮች ሲያስረዱ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የሚናገራቸው ወደ መሬት ወርደው በተግባር ላይ ይውላሉ የሚለውን ከኢህአዴግ ታሪክ አንጻር ለመናገር አስቸጋሪ ነው” በማለት ለምን ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ እንደሚያደርጉ ይናገራሉ።

ሆኖም ግን ዶ/ር መረራ ጨለምተኛ አይደሉም፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋቸው እንዳለ ሆኖ ይህንንም ተናግረዋል፤ “ኢህአዴግ ለሃቀኛ ጥልቅ ተሃድሶ ከተዘጋጀ ብሔራዊ ዕርቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይፈጠርበት ምንም ምክንያት የለም፤ተቃዋሚዎቹም ግማሽ መንገድ ሄደው የማይቀበሉበት ምንም ምክንያት የለም” በማለት የወደፊት ተስፋቸውን አስረድተዋል።

ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ቃል መገባቱ ተገቢ ቢሆንም ከዚያ በፊት ግን መፈጸም ያለባቸው ቀዳሚ ተግባራት እንዳሉ የፖለቲካ ምሁሩ መረራ ጉዲና ያስረዳሉ። ዶ/ር አብይ ወደሥልጣን መንበሩ ከመጣ በኋላ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች የሞቱና የታሰሩ መኖራቸውን በመጥቀስ እና ከዛሬ ዐሥር ዓመት ጀምሮ እስካሁን ታስረው የሚገኙ ስም በመዘርዘር “እነዚህን (እስር ቤት) አስቀምጠህ ሕዝብን የሚያማልል ንግግር እያደረግህ ምን ያህል ትቆያለህ?” በማለት ጠ/ሚ/ሩ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ሁለት ጉዳዮች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳትና የፖለቲካ እስረኞችን ሁሉ መፍታት እንደሆነ ተናግረዋል።

ዶ/ር መረራ “ጥርጣሬ” ያሉትንም አልደበቁም፤ “አሁንም ቢሆን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር (ከኢህአዴግ) የጋራ አመራር ርቆ ይሄዳል የሚል ግምት የለኝም፤ ይህ የጋራ አመራር የሚባለው ጠ/ሚ/ሩን እጅ እግር አሥሮ የሚያስቀምጥ ነው ወይስ ፋታ የሚሰጣቸው፤ እንደ አገር ጠቅላይ ሚኒስትር አገሪቱን እንዲመሩ፤ … ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ ስም የሚገባቸውን ቃልኪዳኖችን እንዲፈጽም፣ በተግባር እንዲተረጉም ዕድል ይሰጡታል?” በማለት አብይ አህመድን ጠርንፎ ስለያዘው የኢህአዴግ አሠራር በግልጽ አስረድተዋል።

በመጨረሻም የኦፌኮው ሊቀመንበር “ያልተመለሰ” ያሉትን ጥያቄ ምን እንደሆነ ተናግረዋል፤ “(ኢህአዴግ አብይ አህመድ የመረጠው) ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ ነው ይህንን ጠቅላይ ሚኒስትር ከኦሮሞ ያደረጉት ወይስ በሃቅ ለመለወጥ ነው?” ብለዋል። ሲቀጥሉም ይህ የብዙዎች አመለካከት እንደሆነና እርሳቸውም ይህንኑ በ“ተወሰነ ደረጃ” እንደሚጠረጥሩ በመናገር “(የጠቅላይ ሚ/ሩ) ፈተናው እዚያ ላይ ነው” ብለዋል።

ቃለምልልሱን በድምጽ ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/04/VOA_ዶር-መረራ-ጠሚኒስትር-ዶር-አብይ-በሀገሪቱ-አሉ-የሚሏቸውን-ችግሮች-እንዲፈቱ-ጠየቁ___እስክንድር-ፍሬው-April-18-2018.mp3

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

(ፎቶ፡ ዶ/ር መረራ ከእስር እንደተፈቱ በደጋፊዎቻቸው ታጅበው፤ ©ማኅበራዊ ድረገጽ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, merera, Middle Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    April 19, 2018 08:57 pm at 8:57 pm

    Great.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule