• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አብይ አህመድ፤ ለክፉ ቀን የታሰበ የኦሮሞ ወጣቶች ብሶት ማስታገሻ?

April 19, 2018 11:52 pm by Editor 1 Comment

  • የዶ/ር አብይ መሾም “ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ” ይሆን? የዶ/ር መረራ ጥያቄ

ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ቃለምልልስ የሰጡት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በአዲሱ ጠ/ሚ/ር ሹመትና የወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አካሄድ ከኢህአዴግ ድርጅታዊ አሠራር አንጻር ትንታኔ ሰጥተዋል።

“ኢህአዴግ ለምን ተዘጋጅቷል?” የሚሉት መረራ ቀለል ያሉ መሠረታዊ ጥያቄዎችን ያስከትላሉ፤ “ለነጻና ፍትሃዊ ምርጫ፤ ለሃቀኛ የፖለቲካ ውድድር (ኢህአዴግ) ተዘጋጅቷል ወይ?” በማለት ይጠይቃሉ። ራሳቸው ሲመልሱትም “ይህንን ካሁኑ ለመገመት ያስቸግራል” ይላሉ። የጠ/ሚ/ሩ ተስፋ የተሞላበትን ንግግሮች ሁሉ መልካም መሆናቸውን ቢገልጹም እርሳቸው እንደ ዜጋ እና ድርጅታቸውም እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የአብይ አህመድን ንግግሮችና የወደፊቱን ሁኔታ “ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ” በማድረግ እንደሚመለከቱት በመደጋገም ተናግረዋል።

የኦፌኮው ሊቀመንበር ይህንን ያሉበትን ምክንያትም ያብራራሉ፤ ኢህአዴግ ከታሪኩና ካለው ባህርዩ አንጻር ከለውጥ ጋር ትውውቅ የሌለው ድርጅት መሆኑን በእንደምታ ከገለጹ በኋላ ስለ ዶ/ር አብይ ንግግሮች ሲያስረዱ፤ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ  የሚናገራቸው ወደ መሬት ወርደው በተግባር ላይ ይውላሉ የሚለውን ከኢህአዴግ ታሪክ አንጻር ለመናገር አስቸጋሪ ነው” በማለት ለምን ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋ እንደሚያደርጉ ይናገራሉ።

ሆኖም ግን ዶ/ር መረራ ጨለምተኛ አይደሉም፤ ጥንቃቄ የተሞላበት ተስፋቸው እንዳለ ሆኖ ይህንንም ተናግረዋል፤ “ኢህአዴግ ለሃቀኛ ጥልቅ ተሃድሶ ከተዘጋጀ ብሔራዊ ዕርቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይፈጠርበት ምንም ምክንያት የለም፤ተቃዋሚዎቹም ግማሽ መንገድ ሄደው የማይቀበሉበት ምንም ምክንያት የለም” በማለት የወደፊት ተስፋቸውን አስረድተዋል።

ከሁለት ዓመት በኋላ የሚካሄደው ምርጫ ነጻና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ቃል መገባቱ ተገቢ ቢሆንም ከዚያ በፊት ግን መፈጸም ያለባቸው ቀዳሚ ተግባራት እንዳሉ የፖለቲካ ምሁሩ መረራ ጉዲና ያስረዳሉ። ዶ/ር አብይ ወደሥልጣን መንበሩ ከመጣ በኋላ በተለያዩ የኦሮሚያ ከተሞች የሞቱና የታሰሩ መኖራቸውን በመጥቀስ እና ከዛሬ ዐሥር ዓመት ጀምሮ እስካሁን ታስረው የሚገኙ ስም በመዘርዘር “እነዚህን (እስር ቤት) አስቀምጠህ ሕዝብን የሚያማልል ንግግር እያደረግህ ምን ያህል ትቆያለህ?” በማለት ጠ/ሚ/ሩ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡት ሁለት ጉዳዮች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ማንሳትና የፖለቲካ እስረኞችን ሁሉ መፍታት እንደሆነ ተናግረዋል።

ዶ/ር መረራ “ጥርጣሬ” ያሉትንም አልደበቁም፤ “አሁንም ቢሆን አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር (ከኢህአዴግ) የጋራ አመራር ርቆ ይሄዳል የሚል ግምት የለኝም፤ ይህ የጋራ አመራር የሚባለው ጠ/ሚ/ሩን እጅ እግር አሥሮ የሚያስቀምጥ ነው ወይስ ፋታ የሚሰጣቸው፤ እንደ አገር ጠቅላይ ሚኒስትር አገሪቱን እንዲመሩ፤ … ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኢህአዴግ ስም የሚገባቸውን ቃልኪዳኖችን እንዲፈጽም፣ በተግባር እንዲተረጉም ዕድል ይሰጡታል?” በማለት አብይ አህመድን ጠርንፎ ስለያዘው የኢህአዴግ አሠራር በግልጽ አስረድተዋል።

በመጨረሻም የኦፌኮው ሊቀመንበር “ያልተመለሰ” ያሉትን ጥያቄ ምን እንደሆነ ተናግረዋል፤ “(ኢህአዴግ አብይ አህመድ የመረጠው) ይህንን ክፉ ቀን የኦሮሞ ወጣቶችን አስታግሶ ለማለፍ ነው ይህንን ጠቅላይ ሚኒስትር ከኦሮሞ ያደረጉት ወይስ በሃቅ ለመለወጥ ነው?” ብለዋል። ሲቀጥሉም ይህ የብዙዎች አመለካከት እንደሆነና እርሳቸውም ይህንኑ በ“ተወሰነ ደረጃ” እንደሚጠረጥሩ በመናገር “(የጠቅላይ ሚ/ሩ) ፈተናው እዚያ ላይ ነው” ብለዋል።

ቃለምልልሱን በድምጽ ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ።

https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/04/VOA_ዶር-መረራ-ጠሚኒስትር-ዶር-አብይ-በሀገሪቱ-አሉ-የሚሏቸውን-ችግሮች-እንዲፈቱ-ጠየቁ___እስክንድር-ፍሬው-April-18-2018.mp3

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

(ፎቶ፡ ዶ/ር መረራ ከእስር እንደተፈቱ በደጋፊዎቻቸው ታጅበው፤ ©ማኅበራዊ ድረገጽ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, eprdf, Ethiopia, Full Width Top, merera, Middle Column, prime minister, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    April 19, 2018 08:57 pm at 8:57 pm

    Great.

    Reply

Leave a Reply to Tadesse Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule