• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት እስክንድርን ከአገር እንዳይወጣ በመከልከል ባላሰበው ማነቆ ውስጥ ገባ

April 19, 2018 08:41 pm by Editor 2 Comments

በኔዘርላንድ በሚደረግ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል 50ኛ ዓመት ክብረበዓል ላይ ለመገኘት ተጋብዞ የነበረው እስክንድር ነጋ ሐሙስ ሌሊት ለአርብ ጠዋት ቦሌ ላይ ከአገር እንዳወጣ ታግቷል። ጎልጉል ባገኘው መረጃ መሠረት ጉዳዩ ህወሓትን ትልቅ ቅርቃር ውስጥ ከቶታል።

ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተሉ የነበሩት የመብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ በፌስቡክ ገጻቸው እንደገለጹት ይህ ፈጽሞ መከሰት ያልነበረበት ጉዳይ መሆኑን በመጥቀስ ጠ/ሚ/ር አብይ በጉዳዩ ላይ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጡበት ጠይቀዋል።

ሌላው ለጉዳዩ ቅርበት ያለውና ክስተቱ እንደተፈጸመ አጭር ዘገባ ያሰራጨው ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ “ከሌሊቱ 8 ሰዓት ቦሌ ያሉ የደህንነት አካላት ፓስፖርቱን ቀምተው አትሄድም ብለውታል። የከለከሉበትን ምክንያቱን ግን አልገለጹም” ብሏል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ከቦሌ አካባቢ ባገኘው መረጃ መሠረት እስክንድርን እንዳይወጣ ፓስፖርቱንና የጉዞ ሰነዱን የነጠቀችው የትግራይ ተወላጅ የሆነች የኤርፖርቱ ደኅንነት ሠራተኛ መሆኗ ታውቋል። ሆኖም ክስተቱ እንደተፈጸመ እና እስክንድርም በአየር ማረፊያው እንዲታገድ ከተደረገ በኋላ በምዕራቡ ዓለም ለሚገኙና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው መረጃው እንዲደርስ ተደርጓል። የእስክንድርን መታገድ አስመልክቶ ማን ትዕዛዝ እንደሰጠ በወቅቱ የተደረገ ክትትል በቦታው የሚገኙት እርስበርሳቸው ሲወነጃጀሉና ራሳቸውን ከጥፋተኝነት ለማግለል ሲሞክሩ ተሰምተዋል።

እንደ ጎልጉል መረጃ ከሆነ ከእስክንድር ፓስፖርት መነጠቅ ጋር በተያያዘ በተከሰተው የህወሓት የአፈና ተግባር በምዕራቡ ዓለም የሚገኙ የህወሓት ድርጎ ሰፋሪዎች ዘንድ መረጃው ደርሶ ህወሓት በሚገባው ቋንቋ እንደሚነግሩት ለማወቅ ተችሏል። እየሻከረ የመጣው የህወሓትና የምዕራቡ ግንኙነት ላይም ትልቅ ነጥብ የሚጥል መሆኑን አብሮን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። “ይህንን በፍጹም ማድረግ አልነበረባቸውም” የሚል ተጠያቂ የሚያደርግ ንግግር እና “የግመሏን ወገብ የሚሰብረው የመጨረሻው ገለባ ነው” የሚለው የእንግሊዝኛ ብሒል አብሮ ተሰምቷል።

እስክንድር በኢትዮጵያ አቆጣጠር አርብ ሲሆን የሚፈታ መሆኑን በተቻለው ሁሉ ለአምነስቲ ፕሮግራም ለመድረስ የሚችልበት ሁኔታ ለመፍጠር እንደሚሞከር ለማወቅ ችለናል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍቃሪ ህወሓት የትግራይ ተወላጆች የተሞላ መሆኑንና እዚያም የሚገኙ ሠራተኞች እንደ መንግሥት ራሳቸውን በመቁጠር የፈለጉትን የሚያደርጉበት አሠራር መቆም ያለበት መሆኑን ዛሬ ከእስክንድር መታገት በኋላ በአጽንዖት በአየርመንገዱ አካባቢ የነበሩ ያሰሙት አቤቱታ ነው። ጠ/ሚ/ር አብይ ከሚያጸዱት መ/ቤት መካከል ቀዳሚው አየር መንገዱ እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል።

አርብ ወደ ጎንደር የሚጓዙት ዶ/ር አብይ አህመድ፤ እስክንድር ነጋ ወደ አምስተርዳም እንደሚበር ሳያረጋግጡ ጉዟቸውን ወደ ጎንደር ማቅናት የለባቸውም ሲሉ ከአዲስ አበባ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰው ለጎልጉል ተናግረዋል።

ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ ያቀናበaረው ዜና ከዚህ በታች ይነበባል፤

እስክንድር ነጋ -ፓስፖርቱን ነጥቀው ቦሌ ላይ አገቱት

የዲሞክራሲ ጥማት የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተመልክቻለሁ – እስክንድር ነጋ

ክንፉ አሰፋ — አምነስቲ ኢንተርናሽናል 50ኛ ዓመቱን ሲያከብር ለክብር እንግድነት በሆላንድ የጠራው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ሊወጣ ሲል በህወሃት ታግቷል።

ከሌሊቱ 8 ሰዓት ቦሌ ያሉ የደህንነት አካላት ፓስፖርቱን ቀምተው አትሄድም ብለውታል። የከለከሉበትን ምክንያቱን ግን አልገለጹም። እስክንድር ነጋ ሃሳቡን በነጻ በመግለጹ ምክንያት የመጨረሻውን ሳንደምረው ለ8 ጊዜ ታስሯል። እ. ኤ. አ. በ2013 በሽብርተኝነት ተከሶ 18 ዓመት እስራት ተፈርዶበት ነበር።

እስክንድር ነጋ የካቲት 14 ቀን 2018 ከሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ጋር ቢለቀቅም እንደገና ለ 9ኛ ጊዜ ታሰሮ ነበር።

እስክንድር ከዘጠኝ በላይ የክብር ሽልማቶች ያገኘ ኢትዮጵያዊ ጀግና ነው።
1. በ 2011 PEN America (NY)
2. በ 2012 Barbara Goldsmith Freedom to Write Award
3. በ 2014 World Association of Newspapers’ Golden Pen of Freedom Award
4. በ 2015 PEN Canada Freedom of Expression Award
5. በ 2017 International Press Institute World Press Freedom Hero
6. በ 2018 Oxfam Novib/PEN Award for Freedom of Expression (60 laureates)
7. ሂዩመን ራይት ዋች የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እና አምነስቲ የኢንተርናሽናል የክብር ተሸላሚ መሆኑ የሚታወስ ነው።

ዶ/ር አብይ አህመድ ለውጥ ሊያመጣ ቃል በገባ ሳምንታት ቢቆጠሩም የህወሃት አፈና እና ግድያ ግን ተባብሶ መቀጠሉን የአለም መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ይገኛሉ። ዛሬ በእስክንደር ነጋ ላይ የተፈጸመው የተለመደ የህወሃት በደል በዶ/ር አብይ ፈንጥቆ የነበረውን ተስፋ የሚያጨልም ነው። የህግ ሳይሆን የህወሃት የበላይነት እስካለ ድረስ በኢትዮጵያ ለውጥ አይታሰብም።

ሕወሃት አይታደስም። አይጠገንምም። ህወሃት ከምድሪቱ ላይ መጥፋት ነው ያለበት። ይህ ደግሞ በሕዝባዊ አመጹ እውን ይሆናል።

እስክንድር ነጋ በሆላንድ ሃገር ከተዘጋጀለት የአምነስቲ ዝግጅት በኋላ ልጁን እና ባለቤቱን ለማየት ወደ አሜሪካ ሊያመራ እንደነበር ይታወቃል።

የሆላንድ ንጉስ ዊለም አሌክሳንደር የሚገኙበት የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ከብረ-በዓል በእስክንድር ያለመገኘት የተነሳ መልካም የነበረ ድባቡ እንዲጠፋ መደረጉን የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ተወካይ ገልጸውልናል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

ተጨማሪ፤ ከአዲስ አበባ ባገኘነው መረጃ መሠረት እስክንድር ብዙም ሳይቆይ ተፈቷል። ፓስፖርቱና የጉዞ ሰነዱ ተመልሶለታል። በአምነስቲ ላይ የመገኘቱ ተስፋ አምልጧል። (April 20, 2018 @7:14PST)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: abiy, abiy ahmed, amnesty, eskinder, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    April 20, 2018 07:44 pm at 7:44 pm

    ያሠሩት በማን ትዛዝ እንደሆነ ተጣርቶ ከኃላፊነታቸው መነሳት አለባቸው።

    Reply
  2. የዋህ ነሽ says

    May 5, 2018 11:30 am at 11:30 am

    በማስምሰል እንኮእን በቅጣት መልክ አድራጊውን ቢያነሱ ያው የነሱ የሆነውን የትግሪ ጊንጥ ነው የሚተኩት።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule