ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት ከህወሃት ጋር ድብቅ ግንኙነት በመፍጠር በአሶሳ ከተማ ጥፋት ለመፈጸም በዝግጅት ላይ እንደሆኑ የተጠረጠሩ 20 ግለሰቦች ዛሬ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱላዚዝ መሐመድ ተናገሩ። ኮሚሽነሩ ለኢዜአ እንዳሉት፤ግለሰቦቹ በአሶሳ ከተማ ኢንቨስትመንትን ሽፋን በማድረግ ጥፋት ለመፈጸም ከህወሃት ድብቅ ትልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው። ከዚህ ቀደም በክልሉ መተከል ዞን የተፈጸመውን ጥቃት ያስታወሱት ኮሚሽነሩ ግለሰቦቹ ይህንን ጥፋት ዳግም ማስቀጠል ዋነኛ ግባቸው … [Read more...] about በአሶሳ ከተማ ከአሸባሪው ህወሃት ጋር በመሆን በድብቅ ጥቃት ሊፈጽሙ የነበሩ 20 ግለሰቦች ተያዙ
Middle Column
ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህወሃት መሪውን የያዘው መሆኑ ታወቀ
“ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) መኖሩን የሚያሳዩ መረጃዎች በፖሊስ ተደርሶባቸዋል” ሲሉ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ ገለጹ። ጀኔራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ የደረሰውን ጥቃት በተመለከተ ከትላንት በስቲያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ “በህወሃት ስልጠና ተሰጥቷቸው በኦሮሚያ ክልል ሽብር እንዲፈጽሙ ከተላኩት መካከል የተያዙ ሰዎች እንዳሉ አረጋግጠናል” ብለዋል። ድምጸ ወያኔ ቲቪ እና ኦኤንኤን ቲቪ ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩ ዘገባዎች በመስራት ላይ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የኦነግ ሸኔ ታጣቂ ሃይል ባለፉት ሁለት ዓመታት በክልሉ በተለያዩ ቦታዎች የመንግስት ሰራተኞችን፣ አመራሮችን፣ ነጋዴወችን ጨምሮ በንጹ ዜጎች ላይ ግድያ ሲፈጽም መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁንም … [Read more...] about ከኦነግ ሸኔ ጀርባ ህወሃት መሪውን የያዘው መሆኑ ታወቀ
ቀዩ መስመር ታልፏል
የሥራ አስፈጻሚው ከፍተኛው አካላት የሆኑት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅና ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ህወሃት ቀዩን መስመር ማለፉን አስታውቀዋል። ፕሬዚዳንት ሳህለ-ወርቅ ዘውዴ በምዕራብ ወለጋ ዞን በንጹሀን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በማስመልከት ያስተላለፉት መልዕክት። “የሰማሁት አሰቃቂ ግድያ ልቤን በእጅጉ ሰብሮታል። ንጹሀን ዜጎች በሌሎች እብደት ውድ ሕይወታቸውን የሚከፍሉበት ንብረታቸው የሚወድምበት መሄጃ አጥተው የሚንከራተቱበት ምንም ምክንያት የለም። የዛሬ ዓመት በ30/10/2019 የጻፍኩትን ትዊት ልድገመው። “ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል። ለቅሶ፣ ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው። “ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል … [Read more...] about ቀዩ መስመር ታልፏል
መከላከያ ፈጣን ምላሽ የሚሰጡ ሁለት ዕዞች አቋቋመ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት የሚሰጡኝን ግዳጆች በፍጥነት ማከናወን ያስችሉኛል ያላቸውን ተጨማሪ ሁለት ዕዞች ማደራጀቱን ትላንት አስታውቋል። አዲሶቹ ዕዞች በዚህ ዓመት ወደ ስራ ይገባሉ ተብሏል። ዕዞቹ በውስጥም በውጭም የሚቃጡ ጥቃቶችና ችግሮችን ፈጥነው ለመከላከል እንዲችሉ ታስቦ የተደራጁ እንደሆኑ ተገልጿል። ማዕከላዊና ሰሜን ምዕራብ አዲስ የተደራጁት ዕዞች ሲሆኑ የቀደሙት ምዕራብ፣ ሰሜን፣ ደቡብ እና ምስራቅ ዕዞች መኖራቸው ይታወቃል። ዕዞቹ አዲስ አበባና ባሕር ዳር ላይ እንደሚደራጁ ሁለቱ ጄኔራሎች በመግለጫቸው አስታውቀዋል። (ኢዜአ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about መከላከያ ፈጣን ምላሽ የሚሰጡ ሁለት ዕዞች አቋቋመ
የመተከል ዞን ሕዝብ ሊደራጅና ሊታጠቅ ይገባዋል – አቶ ደመቀ መኮንን
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በዛሬው (ሰኞ) ዕለት የተፈፀመውን አሳዛኝ ድርጊት መነሻ በማድረግ በመተከል ዞን ከሚመራው ኮማንድ ፖስት አመራር አካላት ጋር በዞኑ ወቅታዊ ሁኔታ ዙሪያ መክረዋል። ህይወታቸውን ላጡ ዜጎች ቤተሰቦች እና ወዳጆች መፅናናትን ተመኝተዋል። በዞን የተለየዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት ኮማንድ ፖስት ተደራጅቶ የራሱን ዕቅድ አዘጋጅቶ ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ሰፊ ርብርብ እየተደረገ ቢሆንም፤ አሁንም የዜጎች ህይወት በአሳዛኝ ሁኔታ መጥፋት መቀጠሉ ሪፖርት ቀርቧል። በዚህ አካባቢም ሆነ በሌሎች ሠላምና ፀጥታን በአስተማማኝ ሁኔታ ለመፍጠር የሴረኞችን ገመድ መበጣጠስ፣ ጠንካራ የህግ የበላይነት ማስከበር ህብረተሰቡ ራሱን የመከላከል አቅም እንዲኖረው ማድረግ ወሳኝ ተግባር መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል። ምክትል ጠቅላይ … [Read more...] about የመተከል ዞን ሕዝብ ሊደራጅና ሊታጠቅ ይገባዋል – አቶ ደመቀ መኮንን
ኢዜማ በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ክስ መሠረተ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሰሰ። ፓርቲው ክሱን የመሰረተው የከተማው አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በሰጠው ትዕዛዝ፤ የፓናል ውይይት እንዳያደርግ መከልከሉን በመቃወም ነው። በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ፍትሐ ብሔር ችሎት ባለፈው አርብ መስከረም 30፤ 2013 የተከፈተው የክስ መዝገብ፤ በፓርቲው ላይ የደረሰው “የሁከት ተግባር እንዲታገድ” የሚጠይቅ ነው። ኢዜማ ይህን ክስ ለማቅረብ የተገደደው ሕገ መንግስታዊ የሆነው “የመሰብሰብ መብት” በተከሳሽ መስሪያ ቤት በተሰጠ ትዕዛዝ በመገደቡ መሆኑን ገልጿል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽህፈት ቤት ለክስ ያበቃውን ትዕዛዝ ለፓርቲው የጻፈው ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 25፤ 2013 ነበር። … [Read more...] about ኢዜማ በአዲስ አበባ አስተዳደር ላይ ክስ መሠረተ
የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ተወሰነ
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ማክሰኞ ባካሄደው መደበኛ ጉባዔ የፌደራል መንግሥት ከትግራይ ክልል መስተዳድር ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ውሳኔ አሳለፈ። ይህ ውሳኔ ሊተላለፍ የቻለው ባለፈው ነሃሴ 30 2012 ዓ.ም የፌዴሬሽን ምክር ቤት አድርጎት በነበረው አስቸኳይ ጉባዔ በትግራይ ክልል የሚካሄደው ምርጫ እንዳልተደረገ፣ እንዳልተፈጸመ እና እንደማይጸና ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ነው። ውሳኔውን የሚከታተል የህገ መንግስት ጉዳዮች እና የማንነት ጉዳዮች አጣሪ ቋሚ ኮሚቴ ጉዳዩን ሲከታተል ቆይቶ ውሳኔው ባለመፈጸሙ ባዛሬው ዕለት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ነው ይህንን ወሳኔ ሊያሳልፍ ያቻለው። ምክር ቤቱ በትግራይ ክልል መንግስት ላይ ሶስት ውሳኔዎችን ማሳለፉን ገልጿል። የመጀመሪያው የትግራይ ክልል ያካሄደውን ኢ-ህገ መንስታዊ ምርጫ ተከትሎ ከተመሰረቱ የትግራይ ክልል … [Read more...] about የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳያደርግ ተወሰነ
ፕሮፍ ተሸኙ!
የጂኦግራፊ ሊቅ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና ደራሲ መስፍን ወልደ ማርያም (ፕሮፌሰር) (1922-2013) “አንድ ትውልድ ይወለዳል፣ በጊዜው እንደጊዜው ያድጋል፣ ያልፋል፣ በሌላ ትውልድ ይተካል። አዲሱም ትውልድ የተረከበውን ቅርስ ይዞ ይነሳና በራሱ ጥረት አዳዲስ ሥራዎችን ሠርቶ ይጨምርበትና ያድጋል፣ አዲስ ነገርን ትቶ ያልፋል። የቀደመው ትውልድ ተፈጥሮና ኑሮው ከሚያስገድደው በላይ ለሚቀጥለው ትውልድ መስዋዕት መሆን አይችልም፣ አይጠበቅበትምም። በምፅዋትና በሞግዚት አስተዳደር የሚኖር ትውልድ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፈው ዕዳ ብቻ ነው፣ ዕዳን በውርስ ተሸክሞ የሚፈጠር ትውልድ ያለምርኩዝ መንቀሳቀስ አይችልም፣ ምርኩዝ ሊሆኑት የሚችሉት እነዚያው የዕዳው ባለቤቶች ናቸው። ስለዚህም ከዕዳና ከምፅዋት አዙሪት አይወጣም።” ይህን ጠሊቅ ዕይታ የትውልድ ቅብብሎሽ አንፃራዊ ገጽታና ትችት … [Read more...] about ፕሮፍ ተሸኙ!
መቀሌ ተሸርቦ አዲስ አበባና ደብረዘይት ሊተገበር የነበረው ሽብር ከሸፈ
የሽብር ጥቃት ለመፈጸም በህቡዕ ሲሰራ የቆየ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ። የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት በላከው መግለጫ÷ በቢሾፍቱና በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ከሚከበረው የኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሽብር ጥቃቶች ለመፈጸም፣ አመጽ ለማቀጣጠል፣ ግጭትና ትርምስ ለመፍጠር ከጥቂት የህወሓት የጥፋት ቡድኖች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ተልዕኮ ተቀብሎ በህቡዕ ሲያስተባብርና ሲመራ የነበረ የኦነግ ሸኔ ቡድን ከእነ ግብረአበሮቹ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ማድረጉን አስታውቋል። አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ለመገናኛ ብዙሃን ባሰራጨው መረጃ እንደገለጸው÷ ከኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ፣ በቢሾፍቱና በሌሎቹም የአገሪቱ አካባቢዎች በጦር መሳሪያ የተደገፈ … [Read more...] about መቀሌ ተሸርቦ አዲስ አበባና ደብረዘይት ሊተገበር የነበረው ሽብር ከሸፈ
ቪኦኤና ጀርመን ድምጽ – የክልሎችን ኅልውና እንደ ህወሓት እየጣሱ ነው
በተለይ ካለፉት ሦስት ወራት ወዲህ የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ብሎ የሚጠራውን መቀሌ የመሸገውን የወንበዴዎች ስብስብ (ትህነግን) እያገለገሉ ስለመሆኑ ከሚያቀርቡት ያልተመጣጠነ መረጃ መረዳት አያዳግትም። ለዚህም ይመስላል የተጠቀሱት ሚዲያዎች በተለይም የጀርመን ድምጽ ተቃውሞ እየቀረበበት ይገኛል። የጎልጉል የአዲስ አበባ መረጃ አቀባይ እንዳለው “አለቃና ተቆጣጣሪ ያለ አይመስልም” ሲል በተጠቀሱት ሚዲያዎች ከሚሰሩ ዜና አቅራቢዎች ጋር ቅርብ መሆኑንን የጠቀሰ አስተያየት ሰጪ እንደነገረው ይገልጻል። የአንድ ጋዜጣ ኤዲተር እንደነበር ገልጾ አስተያየት የሰጠው ባለሙያ “ሚዲያዎቹ አንዳንድ ጊዜ የሚያቀርቧቸው፣ በተለይም ከክልል ሪፖርተሮቻቸው የሚተላለፉት መረጃዎች ያስደነግጡኛል። ሁሉም እንዳሻቸው ሪፖርት የሚያቀርቡና የኤዲተሮች ሚና የሚታይባቸው … [Read more...] about ቪኦኤና ጀርመን ድምጽ – የክልሎችን ኅልውና እንደ ህወሓት እየጣሱ ነው