• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም

July 20, 2021 09:41 pm by Editor Leave a Comment

ከቶንሲልና ተያያዥ ህመሞች ጋር በተያያዘ የሚመጡ በተለይም ቦርቀው ባልጠገቡ ህጻናት ላይ የሚያጋጥሙ የልብ ህመሞችን በማከም ይታወቃሉ።

መሳቅ፤ መጫወትም ሆነ መቦረቅ አቅቷቸው ነጋቸው የጨለመባቸውን በርካታ ህጻናት ለመታደግ በመቻላቸውም ስማቸው በብዙዎች ይጠቀሳል፤ ኢትዮጵያው ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም ዶ/ር ፈቀደ አግዋር።

ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና ህክምና ታሪክ አዲስ ምዕራፍን ከፍተዋል የሚባልላቸው ዶ/ር ፈቀደ በግላቸው 326 ገደማ ቀዶ ጥገናዎችን ማድረጋቸውን ከአል ዐይን አማርኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።

በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ለመገመት ሊያዳግት በሚችል ደረጃ በርካቶችን ረድተናል የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ እነዚህን የብዙዎችን ህይወት የታደጉ ቀዶ ጥገናዎች በ4 ዓመታት ውስጥ ነው ያደረጉት።

ከ326ቱ ውስጥ 290 ገደማዎቹ ቀዶ ጥገናዎች ሙሉ በሙሉ የልብና የሳንባን ስራ በማቆም የተሰሩ ናቸው። “27 አካባቢ ብቻ ናቸው ልብም ሳንባም ሳይቆም የሰራኋቸው” ሲሉም ነው የሚያስቀምጡት።

ዶ/ር ፈቀደ እና የስራ ባልደረቦቻቸው በኢትዮጵያ እምብዛም ያልተለመደውን የህክምና ግልጋሎት ነው በመስጠት ላይ ያሉት። በዚህም ብዙዎች በሃገራቸው በቤተሰባቸው መካከል ሆነው በሚያግባባቸው ቋንቋ እየተነጋገሩ ርቀው ሄደው ሳይንገላቱ ህክምናውን ለማግኘት ችለዋል።

ይህ መሆኑ በአገልግሎቱ በቶሎ አለመገኘት ምክንያት ሊጠፋ የሚችለውን ህይወት ከመታደግ፤ እንግልትና ድካምን ከማስቀረትም በላይ እንደ ሃገር ሊታጣ የሚችለውን የምንዛሬ ገንዘብ ያድናል።

በራስ ሰው፣ አቅም እና ሃብት ታክሞ መዳኑም ቀላል አይደለም። ወደ ውጭ ሃገር የሄደው ታማሚ ሁሉ ድኖ ስለመመለሱም ዋስትና የለም።

“እኔ ህንድ በምማርበት ጊዜ ወገኖቻችን የሚያሳልፉትን ይህን መከራ አይቻለሁ” የሚሉት ዶ/ር ፈቀደም “በሃገርህ መሬት በሃገርህ እውቀት ስትሰራ ይሄን ሁሉ ችግር ነው የምታስወግደው” ሲሉ ይናገራሉ።

ዶ/ር ፈቀደ “ዋናው ቁም ነገር የምትሰጠው ግልጋሎት ልብን ቀደህ ስትጠግን የምታስገኘው ውጤት ከዓለም ጋር ተቀራራቢ ነወይ? የሚለው ነው” ይላሉ፤ ሰዎች ወደ ውጭ ሄደው ከሚያገኙት ህክምና ያነሰ ውጤት የሚገኝ ከሆነ ወደ ውጭ ሄደው መታከማቸው ተገቢነት እንዳለው በመጠቆም።

ውጤቴም፤ በፍጹም ከሌላው ዓለም የማይተናነስና ቆንጆ ውጤት ያለው ስራ ሰርተናልም ነው እውቁ ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም የሚሉት። ይሄን ማንኛውም ሰው ስራዎቻቸውን በሚመለከት በዓለም አቀፍ መጽሄቶች (ጆርናልስ) ላይ ጭምር ከጻፏቸው ጽሁፎች አይቶ ለመረዳት እንደሚችል በመግለጽ።

በአዲስ አበባ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ፈቀደ የሶስት ልጆች አባት ናቸው። በዚሁ በአዲስ አበባ፣ በጎንደር ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲሁም በህንድ ሃገር ቤንግሎር ተምረዋል።

ዋና ስራዬ ቀዶ በመጠገን የሰዎችን ህይወት መቀየር ነው የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ የሰራሁት ብዙ ነው ብዬ አላምንምና አሁንም ቀዶ ጥገናዎችን ማድረግ እፈልጋለሁ ሲሉ ይናገራሉ። (አል ዐይን አማርኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: fekade agwar, gifted hands, heart surgeon

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule