• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም

July 20, 2021 09:41 pm by Editor Leave a Comment

ከቶንሲልና ተያያዥ ህመሞች ጋር በተያያዘ የሚመጡ በተለይም ቦርቀው ባልጠገቡ ህጻናት ላይ የሚያጋጥሙ የልብ ህመሞችን በማከም ይታወቃሉ።

መሳቅ፤ መጫወትም ሆነ መቦረቅ አቅቷቸው ነጋቸው የጨለመባቸውን በርካታ ህጻናት ለመታደግ በመቻላቸውም ስማቸው በብዙዎች ይጠቀሳል፤ ኢትዮጵያው ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም ዶ/ር ፈቀደ አግዋር።

ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና ህክምና ታሪክ አዲስ ምዕራፍን ከፍተዋል የሚባልላቸው ዶ/ር ፈቀደ በግላቸው 326 ገደማ ቀዶ ጥገናዎችን ማድረጋቸውን ከአል ዐይን አማርኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።

በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ለመገመት ሊያዳግት በሚችል ደረጃ በርካቶችን ረድተናል የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ እነዚህን የብዙዎችን ህይወት የታደጉ ቀዶ ጥገናዎች በ4 ዓመታት ውስጥ ነው ያደረጉት።

ከ326ቱ ውስጥ 290 ገደማዎቹ ቀዶ ጥገናዎች ሙሉ በሙሉ የልብና የሳንባን ስራ በማቆም የተሰሩ ናቸው። “27 አካባቢ ብቻ ናቸው ልብም ሳንባም ሳይቆም የሰራኋቸው” ሲሉም ነው የሚያስቀምጡት።

ዶ/ር ፈቀደ እና የስራ ባልደረቦቻቸው በኢትዮጵያ እምብዛም ያልተለመደውን የህክምና ግልጋሎት ነው በመስጠት ላይ ያሉት። በዚህም ብዙዎች በሃገራቸው በቤተሰባቸው መካከል ሆነው በሚያግባባቸው ቋንቋ እየተነጋገሩ ርቀው ሄደው ሳይንገላቱ ህክምናውን ለማግኘት ችለዋል።

ይህ መሆኑ በአገልግሎቱ በቶሎ አለመገኘት ምክንያት ሊጠፋ የሚችለውን ህይወት ከመታደግ፤ እንግልትና ድካምን ከማስቀረትም በላይ እንደ ሃገር ሊታጣ የሚችለውን የምንዛሬ ገንዘብ ያድናል።

በራስ ሰው፣ አቅም እና ሃብት ታክሞ መዳኑም ቀላል አይደለም። ወደ ውጭ ሃገር የሄደው ታማሚ ሁሉ ድኖ ስለመመለሱም ዋስትና የለም።

“እኔ ህንድ በምማርበት ጊዜ ወገኖቻችን የሚያሳልፉትን ይህን መከራ አይቻለሁ” የሚሉት ዶ/ር ፈቀደም “በሃገርህ መሬት በሃገርህ እውቀት ስትሰራ ይሄን ሁሉ ችግር ነው የምታስወግደው” ሲሉ ይናገራሉ።

ዶ/ር ፈቀደ “ዋናው ቁም ነገር የምትሰጠው ግልጋሎት ልብን ቀደህ ስትጠግን የምታስገኘው ውጤት ከዓለም ጋር ተቀራራቢ ነወይ? የሚለው ነው” ይላሉ፤ ሰዎች ወደ ውጭ ሄደው ከሚያገኙት ህክምና ያነሰ ውጤት የሚገኝ ከሆነ ወደ ውጭ ሄደው መታከማቸው ተገቢነት እንዳለው በመጠቆም።

ውጤቴም፤ በፍጹም ከሌላው ዓለም የማይተናነስና ቆንጆ ውጤት ያለው ስራ ሰርተናልም ነው እውቁ ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም የሚሉት። ይሄን ማንኛውም ሰው ስራዎቻቸውን በሚመለከት በዓለም አቀፍ መጽሄቶች (ጆርናልስ) ላይ ጭምር ከጻፏቸው ጽሁፎች አይቶ ለመረዳት እንደሚችል በመግለጽ።

በአዲስ አበባ ተወልደው ያደጉት ዶ/ር ፈቀደ የሶስት ልጆች አባት ናቸው። በዚሁ በአዲስ አበባ፣ በጎንደር ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንዲሁም በህንድ ሃገር ቤንግሎር ተምረዋል።

ዋና ስራዬ ቀዶ በመጠገን የሰዎችን ህይወት መቀየር ነው የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ የሰራሁት ብዙ ነው ብዬ አላምንምና አሁንም ቀዶ ጥገናዎችን ማድረግ እፈልጋለሁ ሲሉ ይናገራሉ። (አል ዐይን አማርኛ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Social Tagged With: fekade agwar, gifted hands, heart surgeon

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule