• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል

July 15, 2021 01:33 pm by Editor Leave a Comment

በማይካድራ ንጹሃንን ጨፍጭፎ የሸሸው የአሸባሪው የህወሓት ወንጀለኛ ታጣቂ ቡድን በሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሴቶችን መድፈሩን በመከላከያ ሰራዊት የተማረኩት የህክምና ባለሙያና ወታደራዊ አመራር የሆኑት ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ማጋለጣቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

በሱዳን የስደተኛ ጣቢያ ውስጥ ከሚገኙ ከ170 በላይ የሚሆኑት የጁንታው አባላት ሴቶች ላልተፈለገ እርግዝናና ለአባላዘር በሽታዎች መጋለጣቸውንም ምረኮኛው ገልጸዋል።

ወንጀል ፈፅመው ወደ ሱዳን የሸሹ የትህነግ ታጣቂዎች በስደተኞቹ ላይ ወሲባዊ ጥቃት እንደሚፈፀሙና በዚህም ያልተፈለገ እርግዝናና የአባላዘር በሽታዎች መስፋፋታቸውን ሲታዘቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል።

ተክለወይኒ ታረቀ

ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ትውልዳቸውና ዕድገታቸው በሰሜን ምስራቅ ትግራይ ታህታይ አዲያቦ በባድመ አካባቢ ሲሆን ከሰራዊቱ በጡረታ ከተገለሉ በኋላ በግል የህክምና ስራ ሲሰሩ ቆይተው በ2011 ዓ/ም ጁንታው ባደረገላቸው ጥሪ የልዩ ሀይሉን መቀላቀላቸውን ተናግረዋል።

በልዩ ሀይሉም የ6ኛ ሬጅመንት ሀኪም በኋላም የሬጅመንቱ ምክትል አዛዥ በመሆን በአዲጎሹና በአብድራፊ ቀጥሎም ወደ ደደቢት በመሄድ በአቃቤ ሰሀት ፣ በአድዋ ፣ በተንቤንና በህንፃፅ የጥፋት ተልዕኮ ሲፈፅሙ መቆየታቸውን ገልፀው፤  በውጊያው እንደማያሸንፉ ሲያውቁ የተወሰኑ ታጣቂዎችን ይዘው ወደ ሱዳን ቢሸሹም በቡድኑ አመራሮች አስገዳጅነት ሌላ ተልዕኮ በመስጠት ወደ ሀገር ቤት መላካቸውን ተናግረዋል።

በስደተኛ ጣቢያዎቹ ያለው ህይወት በጣም አስቸጋሪ መሆኑን የሚናገሩት ምርኮኛው ፣ ተገድባ በተባለው ካምፕ በአይን ተላላፊ በሽታ ብዙ ስደተኞች መጠቃታቸውንና በሱዳን በሚገኙት አራቱም የስደተኛ ጣቢያዎች ተቅማጥና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች በብዛት እንደሚታዩም ተናግረዋል።

ሻምበል ተክለወይኒ ከሱዳን በመነሳት ከጁንታው ተልዕኮ ተቀብለው ከሶስት መቶ በላይ ታጣቂዎችን በመምራት ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ በመከላከያ ሰራዊቱ መማረካቸው ይታወሳል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ገጹ ላይ አስታውቋል።

በሰሜን ምዕራብ ዞን ላዕላይ አዳቦ ወረዳ ዓዲ ዳዕሮ ከተማ 15 ሺህ ነዋሪዎች ሰልፍ በመውጣት ከ10 በላይ ባለትዳር ሴቶችን በመድፈር የተከሰሰን ፖሊስ በመቃወም ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።   

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በትግራይ ክልል ሴቶችን የመድፈር ወንጀል በመበራከቱ ወጣት ሴቶች ጥቁር ልብስ በመልበስ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይም ይህ የሴት መድፈር ወንጀልን በመቃወም የአረና ፓርቲ አመራሩ አብረሃ ደስታ በማህበራዊ ገጹ ላይ ድርጊቱን በማውገዝ መልዕክት ማስተላለፉም አይዘነጋም ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule