• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል

July 15, 2021 01:33 pm by Editor Leave a Comment

በማይካድራ ንጹሃንን ጨፍጭፎ የሸሸው የአሸባሪው የህወሓት ወንጀለኛ ታጣቂ ቡድን በሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሴቶችን መድፈሩን በመከላከያ ሰራዊት የተማረኩት የህክምና ባለሙያና ወታደራዊ አመራር የሆኑት ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ማጋለጣቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል።

በሱዳን የስደተኛ ጣቢያ ውስጥ ከሚገኙ ከ170 በላይ የሚሆኑት የጁንታው አባላት ሴቶች ላልተፈለገ እርግዝናና ለአባላዘር በሽታዎች መጋለጣቸውንም ምረኮኛው ገልጸዋል።

ወንጀል ፈፅመው ወደ ሱዳን የሸሹ የትህነግ ታጣቂዎች በስደተኞቹ ላይ ወሲባዊ ጥቃት እንደሚፈፀሙና በዚህም ያልተፈለገ እርግዝናና የአባላዘር በሽታዎች መስፋፋታቸውን ሲታዘቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል።

ተክለወይኒ ታረቀ

ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ትውልዳቸውና ዕድገታቸው በሰሜን ምስራቅ ትግራይ ታህታይ አዲያቦ በባድመ አካባቢ ሲሆን ከሰራዊቱ በጡረታ ከተገለሉ በኋላ በግል የህክምና ስራ ሲሰሩ ቆይተው በ2011 ዓ/ም ጁንታው ባደረገላቸው ጥሪ የልዩ ሀይሉን መቀላቀላቸውን ተናግረዋል።

በልዩ ሀይሉም የ6ኛ ሬጅመንት ሀኪም በኋላም የሬጅመንቱ ምክትል አዛዥ በመሆን በአዲጎሹና በአብድራፊ ቀጥሎም ወደ ደደቢት በመሄድ በአቃቤ ሰሀት ፣ በአድዋ ፣ በተንቤንና በህንፃፅ የጥፋት ተልዕኮ ሲፈፅሙ መቆየታቸውን ገልፀው፤  በውጊያው እንደማያሸንፉ ሲያውቁ የተወሰኑ ታጣቂዎችን ይዘው ወደ ሱዳን ቢሸሹም በቡድኑ አመራሮች አስገዳጅነት ሌላ ተልዕኮ በመስጠት ወደ ሀገር ቤት መላካቸውን ተናግረዋል።

በስደተኛ ጣቢያዎቹ ያለው ህይወት በጣም አስቸጋሪ መሆኑን የሚናገሩት ምርኮኛው ፣ ተገድባ በተባለው ካምፕ በአይን ተላላፊ በሽታ ብዙ ስደተኞች መጠቃታቸውንና በሱዳን በሚገኙት አራቱም የስደተኛ ጣቢያዎች ተቅማጥና ሌሎች ተላላፊ በሽታዎች በብዛት እንደሚታዩም ተናግረዋል።

ሻምበል ተክለወይኒ ከሱዳን በመነሳት ከጁንታው ተልዕኮ ተቀብለው ከሶስት መቶ በላይ ታጣቂዎችን በመምራት ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ በመከላከያ ሰራዊቱ መማረካቸው ይታወሳል ሲል የመከላከያ ሰራዊት በማህበራዊ ገጹ ላይ አስታውቋል።

በሰሜን ምዕራብ ዞን ላዕላይ አዳቦ ወረዳ ዓዲ ዳዕሮ ከተማ 15 ሺህ ነዋሪዎች ሰልፍ በመውጣት ከ10 በላይ ባለትዳር ሴቶችን በመድፈር የተከሰሰን ፖሊስ በመቃወም ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።   

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በትግራይ ክልል ሴቶችን የመድፈር ወንጀል በመበራከቱ ወጣት ሴቶች ጥቁር ልብስ በመልበስ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

በተመሳሳይም ይህ የሴት መድፈር ወንጀልን በመቃወም የአረና ፓርቲ አመራሩ አብረሃ ደስታ በማህበራዊ ገጹ ላይ ድርጊቱን በማውገዝ መልዕክት ማስተላለፉም አይዘነጋም ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule