• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአዲስ አበባ 325 የትህነግ አሸባሪዎች ከነመሣሪያቸው ተይዘዋል

July 19, 2021 09:24 pm by Editor Leave a Comment

የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በጥናት ላይ በመመስረት እና ከህዝብ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በከተማችን በስጋትነት በተለዩ የተለያዩ ንግድ ቤቶች እና ድርጅቶች ላይ ባደረገው ብርበራ እና ፍተሻ ልዩ ልዩ የጦር መሳሪዎችን፣ ሰነዶችን እና የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳትን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ።

መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር በህወሃት ጁንታ ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ ህግ የማስከበር ዘመቻው በድል ተጠናቆ የሀገር መከላከያ ሰራዊት መቀሌን ጨምሮ መላው ትግራይን መቆጣጠሩ ይታወቃል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ሐምሌ 11 ቀን 2013 ዓ/ም በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት በዚህ ሀገርን የማዳን እና ትግራይን የመታደግ ዘመቻ አብዛኞቹ የጁንታው አመራሮች ሲማረኩ፣ የተወሰኑት ደግሞ ተደምስሰዋል።

ወቅቱ የእርሻ በመሆኑ የትግራይ አርሶ አደሮች በእርሻ ስራቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ እና ለህዝብ ሰላም ሲባል መንግስት የተናጠል ተኩስ ማቆም እርምጃ መውሰዱን ኮሚሽነሩ አስታውሰው ነገር ግን ጁንታውና የጁንታው ደጋፊዎች የመንግስትን የተናጠል የተኩስ አቁም እርምጃ እንደ ፍርሃት በመቁጠር ልዩ ልዩ ሚዲያዎችንና ማህበራዊ ትስስር ገፆችን በመጠቀም የበሬ ወለደ አሉባልታ በማናፈስ ሀገርን የማተራመስ ሴራቸውን እንደ አዲስ ለማስቀጠል ላይ ታች ሲሉ መሰንበታቸውን ገልፀዋል።

በጁንታው የአገዛዝ ዘመን ልዩ ተጠቃሚ የነበሩ እና ለውጡ ስጋት ላይ የጣላቸው የጁንታው ናፋቂዎችና ደጋፊዎች ቀደም ባለው ጊዜ ህግ የማስከበር ዘመቻውን ለማደናቀፍ ብሎም ለውጡን ለመቀልበስ ከጁንታው ተልዕኮ ተቀብለው ቢንቀሳቀሱም በፀጥታ ኃይላችን ጥረት በህዝባችን ቅን ተባባሪነት ሴራቸውን ማክሸፍ ተችሏል ብለዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው።

በህግ ማስከበሩ ዘመቻ ወቅት በአዲስ አበባ ብቻ ከጁንታው ተላላኪዎች እጅ በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ልዩ ልዩ ወታደራዊ ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር መዋላቸው የሚታወቅ ነው።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በጥናት ላይ በመመስረት እና ከህዝብ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ ከሰኔ 19 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2013 ዓ/ም በሁሉም ክፍለ ከተሞች ባከናወነው ህግን የማስከበር ተግባር አሸባሪው ህወሃት በሀይል መቀሌን እንደተቆጣጠረ አስመስሎ ያናፈሰውን ሀሰተኛ መረጃ በማስተጋባት እንዲሁም በከተማችን ብጥብጥና ረብሻ ለማስነሳት ከጁንታው ተልእኮ ተቀብለው ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 325 ግለሰቦች በህግ አግባብ ተይዘው ምርመራ እየተጠራባቸው እንደሚገኝ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ገልፀዋል።

በተጨማሪም በስጋትነት በተለዩ ግሮሰሪዎች፣ ጭፈራ ቤቶች፣ ሆቴሎች እና ሌሎች ንግድ ቤቶች በድምሩ 793 ተቋማት ላይ ፖሊስ ባደረገው ብርበራ እና ፍተሻ 126 ልዩ ልዩ ሽጉጦች፣ 918 የሽጉጥ ጥይት እና 124 የሽጉጥ ካርታዎች፣ 3 ክላሽኢንኮቭ ጠመንጃ፣ 390 የክላሽ ጥይት ከ4 ካርታ ጋር፣ 1 ኤስ.ኬ.ኤስ እና 1 ኡዚ መሳሪያ በኤግዚቢትነት ተይዘዋል።

ከተጠርጣሪዎቹ እጅ በርካታ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የቀድሞ የደንብ ልብስ፣ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን፣ የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ የደንብ ልብስ፣ የፖሊስና የሀገር መከላከያ ማዕረጎች እንዲሁም ልዩ ልዩ መለዮዎች እንደተያዙም ኮሚሽነር ጌቱ አብራርተዋል። ከእነዚህ በተጨማሪ ለፖሊስ ምርመራ የሚረዱ መረጃዎች የተገኘባቸው ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ፍላሾች፣ ታብሌት ስልኮች፣ የባንክ የሂሳብ ደብተሮች፣ ሲም ካርድ፣ የፋክስ ማሽን እንዲሁም ጂ.ፒ.ኤስ እንደተያዙ ኮሚሽነር ጌቱ ጠቅሰዋል።

የጁንታው ቡድን አባላት ውይይት ሲያደርጉበት የነበረ ቃለ ጉባኤ እና የህወሃት መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም የጁንታው መልዕክት የተጫነባቸው ሞባይል ስልኮች መገኘታቸው የጁንታው ተላላኪዎች አደረጃጀት ፈጥረው እና ተልዕኮ ተቀብለው ሲንቀሰቀሱ እንደነበር በምርመራ መረጋገጡን ኮሚሽነሩ አብራርተዋል። ፖሊስ ባደረገው ክትትልና ምርመራ ከ175 ሺ በላይ ብር እና 11 ሺ የአሜሪካ ዶላር እንዲሁም የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች ከጁንታው ተላላኪዎችና ደጋፊዎች እጅ ተይዟል።

በከተማችን አዲስ አበባ መንግስት የወሰደውን የሰላም ዕርምጃ ከሽንፈት የቆጠሩ ተሸሽገውና አንገታቸውን ደፍተው የነበሩ የጁንታው ተላላኪዎች በአንዳንድ መዝናኛ እና ጭፈራ ቤቶች ሰንደቅ አላማችንን በሚያዋርድ መልኩ ያልተገባ ድርጊት እየፈፀሙ ሲጨፍሩ ተይዘው ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።

ምንም እንኳን የጁንታው አፈ-ቀላጤዎች በተለመደው የሐሰት ፕሮፖጋንዳ አሸንፈናል እያሉ መቃዠታቸው ለሁሉም ግልፅ ቢሆንም ጥቂት የማይባሉ ከእኛው ጋር የሚኖሩ፣ ሰላማቸው ተጠብቆላቸው የጥይት ድምፅ ሳይሰሙ በሠላም ውለው በሠላም እያደሩ እኛው መሐል ሆነው የሽብርተኛ ቡድኑ አጋር መሆናቸውን በግልፅ አሳይተዋል።

የከተማችን ሰላም ወዳድ ነዋሪ ለዘመናት በገነባው ጨዋነት እና አርቆ አስተዋይነት ግለሰቦቹ የጁንታው ተላላኪዎች መሆናቸውን በተግባራቸው ቢያረጋግጥም ለሚመለከታቸው የፍትህ አካላት ጥቆማ በመስጠት ህጋዊ የዜግነት ኃላፊነቱን ከመወጣት ውጪ እንደ እነሱ ስሜታዊነት አላሸነፈውም ፤አንዳችም ህገወጥ ተግባር አልፈፀመም። በዚህ አጋጣሚ ሠላም ወዳድ ለሆነው ለከተማችን ነዋሪ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው በራሳቸው እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በመጨረሻም መላው የከተማችን ነዋሪዎች በተደራጀ እና በነቃ ትብብር አካባቢያቸውን እንዲጠብቁ ፣ ከፖሊስ እና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር ያላቸውን የመረጃ ልውውጥ እንዲያጠናክሩ ፣ ወቅታዊ መረጃን በየዕለቱ ከትክክለኛው የመረጃ ምንጭ እንዲከታተሉ እና አጠራጣሪ ሁኔታ ሲያጋጥም ወዲያውኑ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ጥሪያቸውን አስተላፈዋል።

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf children soldiers

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule