ባለፈው ሳምንት "ከሃዲው ዳዊት ወልደጊዮርጊስን" አስመልክቶ "ዳዊት ወልደጊዮርጊስ – የጸረ ኢትዮጵያዊነት መገለጫ" በሚል እርዕስ ዜና ማቅረባችን ይታወሳል። በዜናው ግንባር የተጠቀሰው ሳይጀመር በከሸፈው "የሽግግር መንግሥት" ማመልከቻ ጉዳይ ነበር። ያተምነውን ዜና ተከትሎ አቶ ለማ መገርሳ "ተውኝ። ልኑርበት" ሲሉ ስለጉዳዩ ምንም እንደማያውቁ በይፋ መናገራቸው፣ ፕሮፌሰር ተዘራ ዳዊት የሤራው ስብስብ አገር ለመርዳት መስሏቸው ከገቡ በኋላ ሲያዩት ሃያ ሰባት ዓመታት ኢትዮጵያን ሲዘርፍና ሲያደማ የኖረውን ትህነግን ወደ ስልጣን ለመመለስ እንደሆነ ሲረዱ ራሳቸውን ማግለላቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ ራሱ አስተባባሪውም "የለሁበትም" ሲል ዳግም ክህደቱን አሳይቷል። በዚህ ዜና ላይ ዳዊት ከሃዲና ዘራፊ መሆኑን ለማሳየት ከረሃብ ሰለባዎች ጉሮሮ መንትፎ አገር ስለመክዳቱ መግለጻችን ከተራ … [Read more...] about የ”ከሃዲው” ዳዊት የሌብነት መረጃ
Archives for July 2021
ዳዊት ወልደጊዮርጊስ – የጸረ ኢትዮጵያዊነት መገለጫ
ዳዊት ወልደጊዮርጊስ እሱን የመሰሉትን ከየዓይነቱ ሰብስቦ በጀመረው ዘመቻ የሽግግር መንግሥት ሰነድ ነድፎ የሞተውን ትህነግን አዝሎ እየሮጠ እንደሆነ አስቀድሞ የተገለጸ ቢሆንም ዛሬ ላይ ግን እሱና ራሱን በሚከረፉ ቃላት አደባባይ መላው ኢትዮጵያ ህዝብ ፊት ካዋረደው ታምራት ላይኔ የሚደግፏቸው ሚዲያዎች አማካይነት ይህንኑ የሽግግር መንግሥት አዋጅ ልክ ነገ እንደሚተገበር አድርጎ እያሳወጃቸው ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ተሞክረው ከከሸፉ በርካታ መልካም አጋጣሚዎች ጀርባ ስሙ የሚነሳው ሰላዩ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ደጋፊ ለማሰባሰብ ሲል እሱና ታምራት ላይኔ፣ እንዲሁም በመረጃ ቲቪ ባለቤቶች ስፖንሰር አድራጊነት የአሜሪካ መንግሥት ዕውቅና እንዳለው አድርጎ የሚዲያ ማስታወቂያ ያሰራበት ዕቅድ ሰነድ ለአሜሪካ መንግሥት ከመድረሱ በፊት ሙሉ ዶሴው መንግሥት እጅ መግባቱን የጎልጉል ተባባሪ ዘጋቢያችን … [Read more...] about ዳዊት ወልደጊዮርጊስ – የጸረ ኢትዮጵያዊነት መገለጫ
የኢሰመኮና የሪፖርተሩ ጎዶሎ ሪፖርት ብዙ ይነግረናል – አለ ገና!!
ራሱን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ) ብሎ በመጥራት ለበርካታ ዓመታት አገራችንን ሲያሸብር የኖረው እና በዓለምአቀፉ የአሸባሪዎች ቋት በአሸባሪነት የተዘመገበው፤ በቅርቡም በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት በአሸባሪነት የተመዘገበውን ትህነግ “አሸባሪ” ብሎ ለመጥራት ሲጨንቃቸው የሚታዩ የአገር ውስጥና የውጪ (እንደ ቢቢሲ፣ ቪኦኤ እና ጀርመን ድምፅ) ሚዲያ ተቋማት መኖራቸው በግልጽ እየታየ የመጣ ክስተት ሆኗል። በቅርቡ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባወጣው መግለጫ “ሕወሓትን የክልል መንግስት ማለት እና በክልል ደረጃ የመከላከያ ኃይል የሚል ስያሜ መጠቀም የተወካዮች ምክር ቤት ስልጣንን አለማከበር ነው” ካለ በኋላ “እነዚህን ስያሜዎች በሚጠቀሙ ሚዲያዎች ላይ ባለስልጣኑ ፈቃድ እስከመሰረዝ እርምጃ እንደሚወስድ” አስታውቋል። በአገር ውስጥ የሚታተመው ሪፖርተር ጋዜጣ ይህንን ሕግ እና … [Read more...] about የኢሰመኮና የሪፖርተሩ ጎዶሎ ሪፖርት ብዙ ይነግረናል – አለ ገና!!
“የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም
ከቶንሲልና ተያያዥ ህመሞች ጋር በተያያዘ የሚመጡ በተለይም ቦርቀው ባልጠገቡ ህጻናት ላይ የሚያጋጥሙ የልብ ህመሞችን በማከም ይታወቃሉ። መሳቅ፤ መጫወትም ሆነ መቦረቅ አቅቷቸው ነጋቸው የጨለመባቸውን በርካታ ህጻናት ለመታደግ በመቻላቸውም ስማቸው በብዙዎች ይጠቀሳል፤ ኢትዮጵያው ልብ ቀዶ ጠጋኝ ሃኪም ዶ/ር ፈቀደ አግዋር። ከባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና ህክምና ታሪክ አዲስ ምዕራፍን ከፍተዋል የሚባልላቸው ዶ/ር ፈቀደ በግላቸው 326 ገደማ ቀዶ ጥገናዎችን ማድረጋቸውን ከአል ዐይን አማርኛ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል። በገንዘብም ሆነ በአገልግሎት ለመገመት ሊያዳግት በሚችል ደረጃ በርካቶችን ረድተናል የሚሉት ዶ/ር ፈቀደ እነዚህን የብዙዎችን ህይወት የታደጉ ቀዶ ጥገናዎች በ4 ዓመታት ውስጥ ነው ያደረጉት። ከ326ቱ ውስጥ 290 ገደማዎቹ ቀዶ … [Read more...] about “የተባረኩ እጆች” – በአራት ዓመት 326 ገደማ የልብ ቀዶ ጥገና ያደረጉ ሐኪም
የፎቶ ሌብነትና የአምነስቲ ቅሌት
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ለምርጫ ያነሳሁትን ፎቶ ወስዶ የተጠቀመበትን መንገድ እንዲያስተካክል የተቻለውን ጥረት አድርጎ የማይፈታ ከሆነ ጉዳዩን በተመለከተ ተቋሙን ለመክሰስ እገደዳለሁ ሲል የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ አማኑኤል ስለሺ አስታወቀ። ጋዜጠኛ አማኑኤል በጉዳዩ ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገረው፤ አምንስቲ ኢንትርናሽናልን ለማነጋገር ጥረት እያደረገ ነው። "በስልክና በኢ-ሜይል ለማግኝት ጥረት እያረግን ቢሆንም እስካሁን ምንም ምላሽ አልሰጡንም። አሁን 22 ሰዓታት አልፎታል። በርካታ አለም አቀፍ ሚዲያዎችና ተቋማት ይህንን የተቀናበረ ምስል ተቀባብለውታል። ለራሳቸው ዓላማ የሚያውሉት እንኳን ቢሆን መቀየር የተከለከለ ነው" ሲል ተናግሯል። አምነስቲ ለመረጃው የተጠቀመውን ፎቶ ግራፍ በተመለከተ በውይይት ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ … [Read more...] about የፎቶ ሌብነትና የአምነስቲ ቅሌት
“ብቃት የለኝም፤ የሥነምግባር ችግር አለብኝ” ታምራት ላይኔ
https://youtu.be/fWtD-akMhSU?t=400 ታምራት ስለ ራሱ የሥነምግባር ጉድለት በአደባባይ የተናገረውን ቪዲዮውን በመጫን ይመልከቱ የወንበዴው ቡድን አምበል በሆነው መለስ ዜናዊ በያኔው “ፓርላማ” ፊት ሌብነቱ ተዘርዝሮ እና የሥነምግባር ብልሹነቱን አምኖ ከፓርላማው የተባረረው ታምራት ላይኔ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን እየተመኘ ነው። ከበረኻ ወዳጆቹ እነ ሰዬ አብርሃ ጋር በመሆን ነው በዚህ ሥራ የተጠመደው። ታምራት በመለስ ትዕዛዝ በፓርላማው ፊት ሌብነቱን፣ ሥነ ምግባሩ የጎደፈና መሪ መሆን የማይችል መሆኑን አምኖ መባረሩ ትክክል ነው በማለት ተቀብሎ የላሰውን ስኳር ሳያጣጥም ወዲያውኑ ወደ እስር ቤት ነበር የተወረወረው። ጥያቄያችን ያኔ በዚህ መልኩ ብቃት የለኝም፣ ሥነ ምግባሬ ለተቀመጥኩበት የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የመከላከያ ሚኒስትር … [Read more...] about “ብቃት የለኝም፤ የሥነምግባር ችግር አለብኝ” ታምራት ላይኔ
በአዲስ አበባ 325 የትህነግ አሸባሪዎች ከነመሣሪያቸው ተይዘዋል
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በጥናት ላይ በመመስረት እና ከህዝብ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በከተማችን በስጋትነት በተለዩ የተለያዩ ንግድ ቤቶች እና ድርጅቶች ላይ ባደረገው ብርበራ እና ፍተሻ ልዩ ልዩ የጦር መሳሪዎችን፣ ሰነዶችን እና የፀጥታ አካላት የደንብ አልባሳትን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ። መንግስት የህግ የበላይነትን ለማስከበር በህወሃት ጁንታ ቡድን ላይ እርምጃ መውሰዱን ተከትሎ ህግ የማስከበር ዘመቻው በድል ተጠናቆ የሀገር መከላከያ ሰራዊት መቀሌን ጨምሮ መላው ትግራይን መቆጣጠሩ ይታወቃል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ሐምሌ 11 ቀን 2013 ዓ/ም በሰጡት መግለጫ እንዳብራሩት በዚህ ሀገርን የማዳን እና ትግራይን የመታደግ ዘመቻ አብዛኞቹ የጁንታው አመራሮች ሲማረኩ፣ የተወሰኑት ደግሞ ተደምስሰዋል። ወቅቱ … [Read more...] about በአዲስ አበባ 325 የትህነግ አሸባሪዎች ከነመሣሪያቸው ተይዘዋል
“አደንዛዥ ዕጽ የሚሰጧቸው በበርሜል ሻይ አፍልተው ነው”
“አደንዛዥ ዕጽ የሚሰጧቸው በበርሜል ሻይ አፍልተው በመቀላቀል ነው” አሸባሪው ትህነግ (የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) ዜጎችን ወደ ውትድርና ተመልምለው ለውጊያ የሚያደርሰው በሁለት መንገድ ነው፤ አንዱ ምንም የጦር ዕውቀትና ልምምድ ሳይኖራቸው በግድ ከሽፍታው ቡድን ጋር እንዲቀላቀሉ የተደረጉ ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ አደንዛዠ ዕፅ አፍልተው ነው። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሰሞኑን የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው ትህነግ ህጻናት ልጆችን ለጦርነት እየመለመለ እንደሚሰማራ በማስረጃ ተረጋግጦበታል። ልጆቹ በተለይ ለዚህ ግዳጅ እንዲሰማሩ የሚደረግበትን አካሄድ በየኔታ ትዩብ ላይ የተናገረው በቅርቡ በምርጫ የተወዳደረው ማኅበራዊ አንቂ ብሩክ አበጋዝ ነው። ብሩክ እንደሚለው ትህነግ ልጆቹን ከሰበሰበ በኋላ የጠጡት ምን እንደሆነ በማያውቁበት ሁኔታ እንደ መደበኛ የሚጠጣ ነገር ሻይ … [Read more...] about “አደንዛዥ ዕጽ የሚሰጧቸው በበርሜል ሻይ አፍልተው ነው”
አሜሪካ በኢትዮጵያ ምን እያደረገች ነው? ምንስ ነው የምትፈልገው?
ምዕራባውያን ሌሎች አገራትን እንዳፈረሱ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚፈልጉበት ምክንያት ምዕራባውያን በዕርዳታ ሰበብ እንደ ሊቢያ፣ ሶሪያ፣ የመን ያሉ አገራትን እንዴት አፈረሷቸው? ተራዛሚ ተረጂነት በአንድ አገር ላይ እንዴትና ለምን እንደሚፈቅዱ? በኤርትራና በሶማሊያ የተደረገው እንዴት በኢትዮጵያም ለመፈጸም እያሤሩ እንደሆነ? ዕርዳታን ለጦር ጣልቃገብነት እንዴት እንደሚጠቀሙበት? በዚህ ሁሉ ውስጥ የኦባማ አስተዳደር የፈጸመው ሤራ፤ በተለይ ሊቢያን በማፍረስ በኩል እንዴት የፈጸመው ደባ እና አሁንም በኦባማ ዘመን የነበሩ ሰዎች ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚያደርጉት ሤራ ምን እንደሆነ በዚህ የሸገር ራዲዮ ዝግጅት ላይ ያገኙታል፤ ያድምጡት። https://youtu.be/Rsl980bo_Tw ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about አሜሪካ በኢትዮጵያ ምን እያደረገች ነው? ምንስ ነው የምትፈልገው?
ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል
በማይካድራ ንጹሃንን ጨፍጭፎ የሸሸው የአሸባሪው የህወሓት ወንጀለኛ ታጣቂ ቡድን በሱዳን መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ሴቶችን መድፈሩን በመከላከያ ሰራዊት የተማረኩት የህክምና ባለሙያና ወታደራዊ አመራር የሆኑት ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ማጋለጣቸውን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘግቧል። በሱዳን የስደተኛ ጣቢያ ውስጥ ከሚገኙ ከ170 በላይ የሚሆኑት የጁንታው አባላት ሴቶች ላልተፈለገ እርግዝናና ለአባላዘር በሽታዎች መጋለጣቸውንም ምረኮኛው ገልጸዋል። ወንጀል ፈፅመው ወደ ሱዳን የሸሹ የትህነግ ታጣቂዎች በስደተኞቹ ላይ ወሲባዊ ጥቃት እንደሚፈፀሙና በዚህም ያልተፈለገ እርግዝናና የአባላዘር በሽታዎች መስፋፋታቸውን ሲታዘቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል። ተክለወይኒ ታረቀ ሻምበል ተክለወይኒ ታረቀ ትውልዳቸውና ዕድገታቸው በሰሜን ምስራቅ ትግራይ ታህታይ አዲያቦ በባድመ አካባቢ ሲሆን ከሰራዊቱ … [Read more...] about ከ 170 በላይ ሴት የጁንታው አባላት በራሱ የጁንታው ታጣቂዎች ተደፍረዋል