• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፎቶ ሌብነትና የአምነስቲ ቅሌት

July 20, 2021 01:10 am by Editor Leave a Comment

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ለምርጫ ያነሳሁትን ፎቶ ወስዶ የተጠቀመበትን መንገድ እንዲያስተካክል የተቻለውን ጥረት አድርጎ የማይፈታ ከሆነ ጉዳዩን በተመለከተ ተቋሙን ለመክሰስ እገደዳለሁ ሲል የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ አማኑኤል ስለሺ አስታወቀ።

ጋዜጠኛ አማኑኤል በጉዳዩ ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገረው፤ አምንስቲ ኢንትርናሽናልን ለማነጋገር ጥረት እያደረገ ነው።

“በስልክና በኢ-ሜይል ለማግኝት ጥረት እያረግን ቢሆንም እስካሁን ምንም ምላሽ አልሰጡንም። አሁን 22 ሰዓታት አልፎታል። በርካታ አለም አቀፍ ሚዲያዎችና ተቋማት ይህንን የተቀናበረ ምስል ተቀባብለውታል። ለራሳቸው ዓላማ የሚያውሉት እንኳን ቢሆን መቀየር የተከለከለ ነው” ሲል ተናግሯል።

አምነስቲ ለመረጃው የተጠቀመውን ፎቶ ግራፍ በተመለከተ በውይይት ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አመልክቷል።     

“በኢትዮጵያ የሚገኘውን የአምኒስቲ ጽህፈት ቤት ለማናገር ጥረት አደርጋለሁ፤ ችግሩን በመግባባት ለመቋጨት እሞክራለሁ።  እንደ ባለሙያ በፍርድ ቤት ክስ መስርቶ መጠየቅም ይቻላል” ብሏል።

አምንስቲ ፎቶውን የማየነሳና ተገቢውን ማስተካከያ የማያደርግ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ህግ ለመውሰድ እንድሚቻል በመጥቀስ ካላስፈላጊ እሰጥ አገባ ይልቅ በመግባባት ለመፍታት በሚል ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።  

“አምኒስቲ ኢንትርናሽናልን ለማነጋገር እስከ ለሊቱ 9:00 ሰዓት ስንሞክር ነበር። ነገር ግን ምንም ምላሽ አልሰጡንም። አሁንም ምላሻቸውን እየተጠባበቅን እንገኛለን” ሲል ፎቶግራፍ ጋዜጠኛ አማኑአል ጠቅሷል።

ፎቶው በኢትዮጵያ በተካሄደው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ወደ ምርጫ ጣቢያ ያመሩ መራጮች በፀጥታ ኃይሎች ፍተሻ ሲደረግላቸው የሚያሳይ መሆኑን ያስታወሰው ጋዜጠኛው፤ አምንስቲ በተቀነባበር መንገድ ከአውድ ውጭና ያለአግባብ ስሜን ተጠቅሞበታል ብሏል።

ደንበኞቻችን ምንም አይነት ፎቶ ሲጠቀሙ  ቀይረው እንዲጠቀሙ አይፈቀድም፣ ከአውድ ውጪ በሆነ መንገድ በማቀናበር መቀየር የሚከለክል የተቋማችን ህግም አለ፤ ከእዚህ በተጨማሪም ተዛማጅነት የሌለው መልዕክት ማስተላለፍ እንደማይቻል በህጉ ተጠቅሷል፤ ነገር ግን አምንሰቲ ህግ በመጣስ ላልተገባ ዓላማ አውሎታል ሲል ገልጿል።

“በቲውተር ገፄ ምስሉ ያላግባብ ተቀይሮ ላልተገባው ዓላማ መዋሉን አሳውቄያለሁ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትም ድርጊቱን ለማጋለጥ የሄደበትን መንገድ እንደ አንድ አማራጭ እወስደዋለሁ” ብሏል።

እኛ እንደ አንድ ትልቅ ተቋም በፍርድ ቤት የመክሰስ መብት አለን። ነገር ግን ነገሮች እንዳይካረሩ በሚል በንግግር ለመፍታት ጥረት እያደረግን እንገኛለን ሲልም ተናግሯል። (ዘላለም ግዛው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Right Column Tagged With: AFP, amanuel sileshi, amnesty, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule