• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የፎቶ ሌብነትና የአምነስቲ ቅሌት

July 20, 2021 01:10 am by Editor Leave a Comment

አምንስቲ ኢንተርናሽናል ለምርጫ ያነሳሁትን ፎቶ ወስዶ የተጠቀመበትን መንገድ እንዲያስተካክል የተቻለውን ጥረት አድርጎ የማይፈታ ከሆነ ጉዳዩን በተመለከተ ተቋሙን ለመክሰስ እገደዳለሁ ሲል የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ አማኑኤል ስለሺ አስታወቀ።

ጋዜጠኛ አማኑኤል በጉዳዩ ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገረው፤ አምንስቲ ኢንትርናሽናልን ለማነጋገር ጥረት እያደረገ ነው።

“በስልክና በኢ-ሜይል ለማግኝት ጥረት እያረግን ቢሆንም እስካሁን ምንም ምላሽ አልሰጡንም። አሁን 22 ሰዓታት አልፎታል። በርካታ አለም አቀፍ ሚዲያዎችና ተቋማት ይህንን የተቀናበረ ምስል ተቀባብለውታል። ለራሳቸው ዓላማ የሚያውሉት እንኳን ቢሆን መቀየር የተከለከለ ነው” ሲል ተናግሯል።

አምነስቲ ለመረጃው የተጠቀመውን ፎቶ ግራፍ በተመለከተ በውይይት ለመፍታት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አመልክቷል።     

“በኢትዮጵያ የሚገኘውን የአምኒስቲ ጽህፈት ቤት ለማናገር ጥረት አደርጋለሁ፤ ችግሩን በመግባባት ለመቋጨት እሞክራለሁ።  እንደ ባለሙያ በፍርድ ቤት ክስ መስርቶ መጠየቅም ይቻላል” ብሏል።

አምንስቲ ፎቶውን የማየነሳና ተገቢውን ማስተካከያ የማያደርግ ከሆነ ጉዳዩን ወደ ህግ ለመውሰድ እንድሚቻል በመጥቀስ ካላስፈላጊ እሰጥ አገባ ይልቅ በመግባባት ለመፍታት በሚል ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።  

“አምኒስቲ ኢንትርናሽናልን ለማነጋገር እስከ ለሊቱ 9:00 ሰዓት ስንሞክር ነበር። ነገር ግን ምንም ምላሽ አልሰጡንም። አሁንም ምላሻቸውን እየተጠባበቅን እንገኛለን” ሲል ፎቶግራፍ ጋዜጠኛ አማኑአል ጠቅሷል።

ፎቶው በኢትዮጵያ በተካሄደው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ወደ ምርጫ ጣቢያ ያመሩ መራጮች በፀጥታ ኃይሎች ፍተሻ ሲደረግላቸው የሚያሳይ መሆኑን ያስታወሰው ጋዜጠኛው፤ አምንስቲ በተቀነባበር መንገድ ከአውድ ውጭና ያለአግባብ ስሜን ተጠቅሞበታል ብሏል።

ደንበኞቻችን ምንም አይነት ፎቶ ሲጠቀሙ  ቀይረው እንዲጠቀሙ አይፈቀድም፣ ከአውድ ውጪ በሆነ መንገድ በማቀናበር መቀየር የሚከለክል የተቋማችን ህግም አለ፤ ከእዚህ በተጨማሪም ተዛማጅነት የሌለው መልዕክት ማስተላለፍ እንደማይቻል በህጉ ተጠቅሷል፤ ነገር ግን አምንሰቲ ህግ በመጣስ ላልተገባ ዓላማ አውሎታል ሲል ገልጿል።

“በቲውተር ገፄ ምስሉ ያላግባብ ተቀይሮ ላልተገባው ዓላማ መዋሉን አሳውቄያለሁ። የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትም ድርጊቱን ለማጋለጥ የሄደበትን መንገድ እንደ አንድ አማራጭ እወስደዋለሁ” ብሏል።

እኛ እንደ አንድ ትልቅ ተቋም በፍርድ ቤት የመክሰስ መብት አለን። ነገር ግን ነገሮች እንዳይካረሩ በሚል በንግግር ለመፍታት ጥረት እያደረግን እንገኛለን ሲልም ተናግሯል። (ዘላለም ግዛው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: AFP, amanuel sileshi, amnesty, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule