• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Law
የሕግ ያለህ

ተከሳሾቹ እነጃዋር “መንግሥት የለም” ብለው የመንግሥት አካል ነጻ እንዲያወጣቸው ተማጸኑ

October 7, 2020 12:45 am by Editor Leave a Comment

ተከሳሾቹ እነጃዋር “መንግሥት የለም” ብለው የመንግሥት አካል ነጻ እንዲያወጣቸው ተማጸኑ

በወንጀል ተከስሰው በእስር ቤት የሚገኙት ጃዋር ሲራጅ መሐመድ፣ በቀለ ገርባ ዳኮ፣ ሐምዛ አዳነ ታዬ እና ሸምሰዲን ጠሃ መሐመድ ከሰኞ መስከረም 25 ቀን ጀምሮ በሚመሠረተው የአደራ መንግሥት ለመሳተፍ ከእስር እንለቀቅ ብለው ተማጽንዖ አቅርበዋል። ተከሳሾቹ እነ ጃዋር ልቅም ባለ አማርኛ ከሽነው በጻፉት ደብዳቤ መንግሥታዊ አካል ለሆነው “የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች” ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ በግልባጭ “ለፌዴራል ዐቃቤ ሕግ” እና “ለፌዴራል ወንጀል ምርመራ” ጥያቄያቸውን ልከዋል። ተከሳሾቹ መቀሌ ከመሸገው የበረኻ ወንበዴዎች ቡድብ ህወሓት እና ከሌሎች ራሳቸውን ተቃዋሚ ፓርቲ ብለው ከሚጠሩ ጋር በመሆን ከመስከረም 25 ጀምሮ የአደራ መንግሥት እንመሠርታለን ብለው በተደጋጋሚ ሲናገሩና ሲሠሩ እንደነበር ይታወቃል። ተከሳሾቹ ያቀረቡት ደብዳቤ ከዚህ በታች ይገኛል፤ ጎልጉል የድረገጽ … [Read more...] about ተከሳሾቹ እነጃዋር “መንግሥት የለም” ብለው የመንግሥት አካል ነጻ እንዲያወጣቸው ተማጸኑ

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: chilot, jawar, jawar massacre, ችሎት

የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮች ፍርድ ቤት ውሎ

October 2, 2020 09:38 pm by Editor 1 Comment

የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮች ፍርድ ቤት ውሎ

የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን ጨምሮ ለ20 ተጠርጣሪዎች የእስር ፍርድ ቤት በፈቀደው ዋስትና ላይ እና ፖሊስ በጠየቀው የምርመራ ቀናት ላይ ብይን ለመስጠት ለመስከረም 27/2013 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ዛሬ በነበረው ችሎት በዋስትናው ጉዳይ እና ተጠርጣሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ላይ የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጹሁፍ ያቀረበውን የመልስ መልስ ተቀብሏል። ዛሬ በነበረው ችሎት ማናቸውም ተጠርጣሪዎች በፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን የ6ቱ ጠበቃ ተመስገን ዋጃና ተናግረዋል። በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ከተደረጉ 15 ተጠርጣሪዎች ውስጥ አስራ 2ቱ በዛሬው ችሎት የተወከሉት፤ በ3 ጠበቆች መሆኑንም ገልጸዋል። ቀሪዎቹ 3 ተጠርጣሪዎች በራሳቸው የሚከራከሩ ናቸው ብለዋል። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ማክሰኞ በነበረው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት፤ … [Read more...] about የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮች ፍርድ ቤት ውሎ

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: chilot, jawar massacre, tplf, wolaitta, ችሎት

ከአገር ሊወጣ የነበረ ከ132 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር 9.2 ኪሎ ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ

September 29, 2020 11:41 pm by Editor Leave a Comment

ከአገር ሊወጣ የነበረ ከ132 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር 9.2 ኪሎ ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ

በህገ-ወጥ መንገድ ከአገር ሊወጣ የነበረ 132 ሺህ 860 የአሜሪካን ዶላር እና 9.2 ኪሎ ግራም የሚመዝን ኮኬይን የተሰኘ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል። በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቴክኖሎጂ ተደገፎ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻና ክትትል ከአዲስ አበባ ወደ ናይጄሪያ ሊጓጓዝ የነበረ 9.2 ኪሎ ግራም ኮኬይን እንዲሁም መዳረሻውን ዝምባብዌ ያደረገ 132 ሺህ 860 የአሜሪካን ዶላር በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው። የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንደገለጸው፤ በህገወጥ ድርጊቱ ተጠርጥረው የተያዙት ግለሰቦች በኢትዮጵያ ለቀናት ባደረጉት ቆይታ ከግብረአበሮቻቸው ጋር ግንኙነት በመፍጠር በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ ነበር። ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ክትትል … [Read more...] about ከአገር ሊወጣ የነበረ ከ132 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር 9.2 ኪሎ ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ

Filed Under: Law, Middle Column, News Tagged With: fake birr, new birr notes, new currency, tplf

በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:39 pm by Editor Leave a Comment

በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ

መንግሥት በተለያዩ ሁኔታዎች በሙስና ወንጀል የተመዘበሩ ሀብቶችን ለማስመለስ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን በተደረገ ጥናት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝ ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት እንዳለ ተጠቆመ። የአመራር ለውጥ ከተደረገ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ሙስናን ለመዋጋት መንግሥት የአገሪቱ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየተንቀሳቀሰ፣ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ ሁኔታ እየቀነሰና አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና ተነሳሽነት የጨመረ ቢሆንም፣ በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ የሙስና ወንጀል በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑም ተገልጿል። ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ በተደራጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉ የተነገረው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ለሁለት ቀናት … [Read more...] about በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ

Filed Under: Law, News, Right Column Tagged With: corruption, new birr notes, tplf

160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:05 pm by Editor 1 Comment

160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ

ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውለውና ክስ ተመሥርቶባቸው የሚገኙ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው አለመሆኑን ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋዎችና ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ የጉዳዮች መገናኘት ካልሆነ በስተቀር፣ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም ከፖለቲካ አመለካከትቸና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ እንዳልሆነ አብራርተዋል። ሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ገላን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጥይት ተመትቶ የተገደለው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ከተከሰቱ አመፆችና … [Read more...] about 160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ

Filed Under: Law, Left Column, News Tagged With: chilot, jawar massacre, tplf, ችሎት

አሸባሪነትን ለመዋጋት ፔንታጎን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር እየሠራ ነው

September 29, 2020 08:32 pm by Editor 1 Comment

አሸባሪነትን ለመዋጋት ፔንታጎን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር እየሠራ ነው

አሜሪካ 2 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር የሚያወጡ የልምምድና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቀሶችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ማድረጓን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ይህ ድጋፍ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የሽብር ቡድን እና ሌሎች የሽብር ድርጅቶችን ሊፈጥሩት የሚችሉትን አደጋዎች ለመመከት የሚያግዘው መሆኑ ተጠቁሟል። የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) ከኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የገለፀው ኤምባሲው በተያዘው ዓመት የተደረገው ድጋፍም የዚሁ አካል ነው ተብሏል። ድጋፉም አምቡላንስ፣ ላንድ ክሮዘር፣ የእቃና የነዳጅ መጫኛ ተሸከርካሪዎችን እንዲሁም የምሽት አጉሊ መነፀር እንደሚያካትት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ሽብርተኝነትን ከመከላከል ጋር ተያይዞ የተደረገ አንደኛው የድጋፍ አይነት ነው … [Read more...] about አሸባሪነትን ለመዋጋት ፔንታጎን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር እየሠራ ነው

Filed Under: Law, News, Right Column

ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

September 29, 2020 01:57 am by Editor Leave a Comment

ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. አሥር የተለያዩ ክሶች የተመሠረተባቸው አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ 24 ተከሳሾች ክሱ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የተሰጣቸው ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 129 ድንጋጌ መሠረት ክሱ ለተከሳሾቹ በችሎት መነበብ ስላለበት፣ በችሎት ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጣቸው። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾን ለመስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ያልቀረቡ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ እንዲያቀርብና ክስ እንዲነበብላቸው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርብ ቀርቷል። በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ 14ኛ ተከሳሽና በአሜሪካ አገር ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃነ መስቀል አበበና አውስትራሊያ እንደሚኖሩ የሚነገረው አቶ ፀጋዬ … [Read more...] about ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, chilot, eskinder, hamza, jawar massacre, omn, tsgaye ararssa, ችሎት

ተከሳሾቹ እነ ጃዋር ወደ እስር ቤት እንዲዛወሩ ታዘዘ

September 24, 2020 10:44 am by Editor Leave a Comment

ተከሳሾቹ እነ ጃዋር ወደ እስር ቤት እንዲዛወሩ ታዘዘ

ባለፈው ሰኞ በዋለው ችሎት እነ ጃዋር ሲራጅ መሐመድ ከተጠርጣሪነት ወደ ተከሳሽነት የክስ ፋይላቸው መቀየሩ ተዘግቦ ነበር። የዚያን ዕለት የቀረበባቸውም ክስ ሃይማኖትና ብሔርን መሠረት በማድረግ፣ በተለይም በአማራ ብሔር ተወላጆችና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም የተለያዩ መገናኛ ብዙኃንና የትስስር ድረ ገጾችን በመጠቀምና በአካል በመገኘት፣ በተገለጸው አግባብ ባስነሱት የእርስ በርስ ግጭት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የ13 ሰው ሕይወት እንዲያልፍና 48,026,526 ብር የሚገመት ንብረት እንዲወድም አድርገዋል፣ በኦሮሚያ በተለያዩ ዞኖችና ከተሞች የ167 ሰዎች ሕይወት እንዲያልፍ፣ 360 ሰዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸውና 4,673,031,142 ብር ግምት ያለው ንብረት እንዲወድም ማድረጋቸውን በመጥቀስ ነበር ዐቃቤ ሕግ ክሱን … [Read more...] about ተከሳሾቹ እነ ጃዋር ወደ እስር ቤት እንዲዛወሩ ታዘዘ

Filed Under: Law, Middle Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, hamza, jawar, jawar massacre, tsegaye ararsa, ችሎት

“በርቱ አገሪቱ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጋችሁ አድርጉ” ጃዋርና ግብረአበሮቹ

September 23, 2020 11:58 pm by Editor Leave a Comment

“በርቱ አገሪቱ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጋችሁ አድርጉ” ጃዋርና ግብረአበሮቹ

የእርስ በርስ ጦርነት በማስነሳት፣ የሽብር ወንጀል ለመፈጸም በማቀድና በመዘጋጀት፣ እንዲሁም የፀና ፈቃድ የሌለው የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ከተመሠረተባቸው 24 ተከሳሾች አንዱ ጃዋር መሐመድ፣ እሱን ጨምሮ እስክንድር ነጋና ልደቱ አያሌው የተከሰሱት መንግሥት በምርጫ ያሸንፋሉ የሚል ሥጋት ስላለው እንጂ ወንጀል ፈጽመው አለመሆኑን ለፍርድ ቤት ተናገረ። ጃዋር ይኼንን የተናገረው የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በመዝገብ ቁጥር 260215 መስከረም 6 ቀን 2013 ዓ.ም. የከፈተውን ክስ፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ለተከሳሾች ሲሰጣቸው ነው። በሽብርተኝነት ሲከሰስ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን በማስታወስ የመጀመርያው በኢሕአዴግ ሥርዓት ውስጥ የቀረበበት ክስ ሲሆን፣ ሁለተኛው አሁን የተከሰሰበት መሆኑን ጠቁሞ፣ በዚህም ኩራት እንደሚሰማው … [Read more...] about “በርቱ አገሪቱ የቄሮ በመሆኗ እንደፈለጋችሁ አድርጉ” ጃዋርና ግብረአበሮቹ

Filed Under: Law, Right Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, chilot, eskinder, hamza, jawar massacre, omn, tsgaye ararssa, ችሎት

የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ

September 23, 2020 11:23 pm by Editor 1 Comment

የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ

የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ የቀድሞ የወላይታ ዞን አመራሮች የነበሩ ግለሰቦችን ጨምሮ 20 ተጠርጣሪዎች በወላይታ ሶዶ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ፤ ለተጠርጣሪዎች ተፈቅዶ በነበረው ዋስትና ላይ ፖሊስ የመልስ መልስ ይዞ እንዲቀርብ ለመጪው ሳምንት ማክሰኞ መስከረም 19 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ጠበቃ ተመስገን ዋጃና ለ"ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ተናግረዋል። ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የተጠርጣሪዎችን አቆያየት በተመለከተ በትላንትናው ዕለት ከሰዓት ብይን ለመስጠት ቀጠሮ ይዞ የነበረ ቢሆንም በጠዋት ችሎት ቀርበው የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎች አልተገኙም በሚል ብይኑን ለዛሬ ማሳደሩን ጠበቃው ገልጸዋል። እስከ ምሽት አንድ ሰዓት ድረስ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ሲጠብቁ የቆዩ ሰባት ተጠርጣሪዎችም በፍርድ ቤት ትዕዛዝ በሐዋሳ ፖሊስ ጣቢያ እንዲቆዩ … [Read more...] about የወላይታ ዞን የቀድሞ አመራሮችን በእስር እንዲቆዩ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ

Filed Under: Law, News, Right Column Tagged With: jawar massacre, wolaitta, ችሎት

  • « Previous Page
  • Page 1
  • Page 2
  • Page 3
  • Page 4
  • Page 5
  • Page 6
  • …
  • Page 11
  • Next Page »

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule