ትግራይ ክልል ሊዘረፍ የነበረ 430 ኩንታል የእርዳታ እህል በህበረተሰቡ ትብብር እና ጥቆማ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን መያዙ ተሰማ። ከትግራይ መዲና መቀሌ ወደ ምዕራባዊ ዞን 'ሰለክለካ' የእርዳታ እህል ከጫኑ 16 መኪናዎች አንዱ ከህግ ውጭ ወደተባለው ቦታ ሳያደርስ በመቐለ ከተማ የእርዳታ እህሉን ለማራገፍ ሙከራ ሲያደርግ ህብረተሰቡ ባደረገው ጥቆማ ተይዟል። እንደ ትግራይ ፖሊስ መረጃ፥ መኪናው ንብረትነቱ የ "ትራንስ ኢትዮጵያ" ሲሆን የታርጋ ቁጥሩ ኮድ 3-9672 የተሳቢው ቁጥር 2848 ኢት ነው። መኪናው ወደ ሰለክለካ 430 ኩንታል እህል ጭኖ እንዲሄድ የነበረ ሲሆን ነገር ግን በመቐለ ከተማ ሰሜን ክ/ከተማ በሚገኝ የትራንስ መጋዘን በማስገባት ከደላሎች እና ነጋዴዎች ጋር በመነጋገር እህሉ ሊሸጥ ነበር የታቀደው፤ ይህን ለማድረግ በህገወጥ መንገድ 2 ሲኖትራክ መኪና ወደ … [Read more...] about በትግራይ ሊዘረፍ የነበረ የእርዳታ እህል ተያዘ
operation dismantle tplf
“ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ዛሬ (ማክሰኞ) በተካሄደው 5ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፤ የኢኮኖሚው አጠቃላይ ገጽታ፤ የፍኖተ ብልጽግና እቅዳችን ያለፉትን 3 አመታት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፤የአገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም መሰረታዊ አጀንዳዎቻችንየብድር ጫና መቀነስተጀምረው የቀሩ በርካታ ፕሮጀክቶች በፈጠነ መንገድ ማጠናቀቅየወጪ ንግዱን ማሻሻልና ማሳደግገቢን ማሻሻልገበያን ማረጋጋትና የዕድገት ቀጣይነትን ማረጋገጥ፤የህዳሴ ግድብ በነበረበት ችግር ምክንያት የአገር ኢኮኖሚ እግሩ ተፈትቶ መሄድ እንዳይቻል አድርጎ ነበር፤የወጪ ንግድም ትልቅ ችግር ውስጥ ነበር፤ ባለፈው አመት ለመጀመሪያ ገፊዜ መሻሻል አሳይቷል፤እነዚህን አጀንዳ ስንቀርጽ ኮቪድ … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ህወሓት ማለት በነፋስ የተበተነ ዱቄት ነው” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ
እነ አቶ ስብሃት ነጋ ጉዳያችን በትግራይ ክልል ፍርድ ቤት ይታይልን ሲሉ አቤቱታ አቅርበው ነበር። ይህን አቤቱታ ያቀረቡት ዛሬ (ማክሰኞ) በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው። በችሎት የተገኙት የጠቅላይ አቃቤ ህግ ቡድን በበኩሉላቸው የፌዴራል መንግስትን ስልጣን ለመጣል በሚል የሽብር አዋጁን በመተላለፍ በመላው ሀገሪቱ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ መቀሌ ሆነው በሰጡት ትዕዛዝ ባህርዳር እና ጎንደርን በሮኬት ማስደብደባቸው አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ተከሳሾቹ ስልጣን ተከፋፍለው በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸመ ወንጀል ነው ያለው አቃቤ ህግ ዶክተር አዲስ አለም ባሌማ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ሆነው አዲስ አባባ ቁጭ ብለው ሲፈጽሙ የነበረው ወንጀል አንድ ቦታ አለመሆኑን ማመላከቻ ነው ብሏል በምላሹ። ይህ … [Read more...] about እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ
አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች
የፕሬዚዳንት ባይደን የቅርብ ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ክሪስቶፈር ኩንስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ለማነጋግር አዲስ አበባ መጥተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን አነጋግረዋል። የኋይት ሐውስ የፕሬዚዳንቱ የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ የሆኑት ጄክ ሱለቫን ባወጡት አጭር መግለጫ እንዳሰፈሩት በትግራይ አለ በሚባለው የሰብዓዊ መብት ገረጣና ሰብዓዊ ቀውስ ባይደን ያላቸውን ትልቅ ጭንቀት ሴናተር ኩንስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እንደሚያቀርቡ ነበር የጠቆሙት። በተጨማሪም ሁኔታው የአፍሪካ ቀንድን አለመረጋጋት ውስጥ ሊከተው የሚችል በመሆኑ ሴናተሩ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር እንደሚመክሩበት አማካሪ በመግለጫቸው አመልክተው እንደነበር ይታወሳል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በተገኙበት አቶ ደመቀ ተቀብለው አስፈላጊው ማብራሪያ እንደተሰጣቸው የውጭ ጉዳይ … [Read more...] about አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች
ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ
ቪኦኤ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል ጃል መሮ በሚል ስም የሚታወቀውን ሽፍታ ሽፋን ሲሰጠው ስለምንነቱና በትክክልም እሱ ስለመሆኑ መረጃ ሰጥቶ አያውቅም። በቢቢሲ አማርኛና በቪኦኤ እንዳሻው ጊዜ መርጦ ወንጀሉን የሚያስተባብለው ጃል መሮ፤ ሲያሻው የሰጠውን ቃለ ምልልስ ስልክ ደውሎ እንዳይተላለፍ የሚያዝ ለመሆኑ ናኮር መልካ “ጃል መሮ ቃለ ምልልሱ እንዳይተላለፍ በጠየቁት መሠረት ትቼዋለሁ” ሲል ያረጋገጠው ሃቅ ነው። ቀደም ሲል በሃጫሉ ግድያ ኦነግ ሸኔ እጁ እንዳለበት በመታወቁ እጅግ የተቆጣውን ህዝብ ለማብረድ በናኮር መልካ አመቻችነት የቪኦኤ ዘጋቢ የሆነችው ጽዮን ግርማ ጃል መሮ በሬዲዮ ጣቢያው ቀርቦ ሳይፈተን እንዲፈነጭና ሃጢያቱን እንዲያራግፍ ፈቅዳለት እንደነበር ይታወሳል። ቢያንስ ማንነቱን መጠየቅ ሲገባ፣ ንጹሃንን በየቦታው እያደፈጠ ለሚጨፈጭፍ ሽፍታ፣ ሚዲያውንም ሌላ ጫካ በማድረግ … [Read more...] about ቪኦኤ በወለጋ ሆሮ ጉድሩ ለተጨፈጨፉ ኦነግ ሸኔን ከደሙ ንጹህ አደረገ
በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት በትግራይ ክልል የሚደረገው ሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦት በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን አስታወቀ። ፅህፈት ቤቱ በክልሉ እየተደረገ ያለውን ሰብአዊ ድጋፍ አቅርቦት በተመለከተ ባወጣው መግለጫ፥ በክልሉ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሰብአዊ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን አስታውቋል። ከዚህ ጋር ተያይዞም እስካሁን በተመድ ስር በሚተዳደሩ ተቋማት የሚሰሩ 240 አባላት በክልሉ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቅሷል። ከዚህ ባለፈም ከሌሎች ተቋማትና ድርጅቶች የተውጣጡ ከ1 ሺህ በላይ የድጋፍ ሰጪ አባላት በክልሉ ድጋፍ እያደረጉ ስለመሆኑም ገልጿል። እስካሁንም 900 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆነ ሰብአዊ ድጋፍ ተደርጓልም ነው ያለው። ከተደረገው ድጋፍ ባሻገር ግን በክልሉ ሙሉ ምላሽ ለመስጠት ተጨማሪ 400 … [Read more...] about በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተካሄደ ነው – የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት
በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው
ሉዓላዊነት እና አብሮነትን የሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም እንዳሉት አንዳንድ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት በትግራይ ክልል ላይ የሰሯቸው ዘገባዎች በአጠቃላይ የጋዜጠኝነት ሙያ አስተምህሮ እና ሙያዊ ስነ ምግባር ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ናቸው። ሥራዎቻቸው በጣም የሚያስተዛዝቡ እና የሚያበሳጩ ጭምር መሆናቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ሚዲያውን እና ዘገባው የሰራውን ባለሙያ ለይቶ ማየት ያስፈልጋል ሲሉ አቶ ወንድወሰን ተናግረዋል። አንድ የሚዲያ ተቋም የላከው ጋዜጠኛ ስህተት ሰራ ማለት ሚዲያው ሙሉ በሙሉ ከእውነት፣ ከፍትህ እና ከሀቅ የተፋታ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ለመድረስ እንደማያስችልም አንስተዋል። የተዛቡ ዘገባዎችን … [Read more...] about በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው
በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ
በሲዳማ ክልላዊ መንግስት በግለሰብ ቤት ተከማችቶ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፌዴራል ፖሊስ ገልጿል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ከህብረተሰቡ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ ለረጅም ጊዜ ሲከታተል ቆይቶ መጋቢት 5 ቀን 2013 ዓ.ም በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጭኮ ከተማ አስተዳደር እና በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ በርካታ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጎሳዬ ለገሰ ገልፀዋል፡፡ በጭኮ ከተማ ላይ በተደረገው ክትትል 30 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ እና ሁለት መትረየስ የተያዘ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ ፋራ ቀበሌ ልዩ ቦታው ወልደ አማኑኤል ተብሎ በሚታወቅ አካባቢ በሚገኝ የግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ የፌደራል ፓሊስ እና የክልሉ ልዩ … [Read more...] about በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ
የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ
ሰሞኑን በትህነግ የማህበራዊ ሚዲያ ጀሌዎች (ዲጂታል ወያኔ) በአክሱም የተደረገ የጅምላ ጭፈጨፋ ማስረጃ ነው ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆኖ መገኘቱ ተገለጸ። በትግራይ አክሱም የተነሳ ነው ተብሎ ሰሞኑን የተሰራጨው ምስል ሐሰተኛ መሆኑን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ ነው። በትግራይ አክሱም የተጨፈጨፉ ሰለባዎች ተብሎ ሃሰተኛ መረጃ ሲሰራጭ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ለዚህም ማስረጃ እንዲሆን ከሰሞኑ ከማህበራዊ እስከ ዓለምአቀፍ ሚዲያ በምስል የተደገፈ መረጃ በስፋት ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል። ሆኖም በማስረጃ በተደገፈ የተሰራጨው ምስል ሐሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ ባደረገው ማጣራት ፎቶው በኖቬምበር 2020 በናይጀሪያ የተነሳ መሆኑን ማረጋገጡን የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ ጨምሮ … [Read more...] about የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ
በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ
75% ሆስፒታሎች ሥራ ጀምረዋል የአስቸኳይ ጊዜ አስተባባሪ ማዕከል ዘርፈ ብዙ ምላሽ ሰጪ ብሔራዊ ኮሚቴ ሳምንታዊ ስብሰባውን አካሂዷል፡፡ኮሚቴው በስብሰባው በትግራይ ክልል የአባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን የአስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት እንዲሁም የመልሶ ማቋቋም ስራዎች አፈፃፀምን ገምግሟል፡፡በክልሉ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት ዝግጅት መጠናቀቁ እና ትምህርት ቤቶቹን ስራ ለማስጀመርም ከመምህራን እና ወላጆች ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ትምህርት ቤቶቹ በቅርቡ ስራ እንዲጀምሩ የተወሰነ መሆኑ እና ይህን ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስ መሰራጨታቸውም ተመልክቷል፡፡በክልሉ ከሚገኙ ሆስፒታሎች መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም 10 በመቶ የሚሆኑት በከፊል ስራ መጀመራቸው ተጠቅሷል፡፡ለአብነትም ባለፉት 2 ሳምንታት 1,583 እናቶች በነዚሁ ተቋማት አገልግሎት … [Read more...] about በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ