በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ስሙ ኢንፎኔት ኮሌጅ አካባቢ አንድ በርሜል ገንዘብ ወድቆ ተገኘ። በዚህ ስፍራ በአንድ በርሜል ተጠቅጥቆ መገኘቱን የኢትዮ ኤፍ ኤም ሪፖርተር በአካል ተገኝቶ አረጋግጧል። የተገኘው ገንዘብ የኢትዮጵያ ብር እና ዶላር ሲሆን ገንዘቡን ማን እንደጣለው ያልተተረጋገጠ ሲሆን የአካባቢው ፖሊስ በመኪና ጭኖ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንደወሰደውም ሪፖርተራችን አረጋግጧል። በተያያዘ ዜና በዚሁ ወረዳ ጣልያን ሰፈር ልዩ ስሙ ጉሊት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ አዛውንት ቤት ቁጥሩ እስካሁን ያልተረጋገጠ ገንዘብ በማዳበሪያ እና በመዘፍዘፊያ አስቀምጠው ተይዘዋል። አዛውንቷ ለረጅም አመታት በልመና ስራ የሚተዳደሩ ናቸው የተባለ ሲሆን የገንዘቡን መጠን ለማወቅ የአካባቢው ወጣቶች እና ፖሊስ በጋራ ቆጠራ እየተካሄደ መሆኑን ሰምተናል። አዛውንቷ … [Read more...] about መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ በበርሜል ወድቆ ተገኘ
operation dismantle tplf
“የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”
በትግራይ ክልል መቀሌ ሀራ ገበያ ዓዲ ጉደም ምድር ባቡር ፕሮጀክት በሚጠብቁት ላይ ከተፈጸመ ጥቃት የተረፉት ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት አዲስ አበባ ከተማ ገብተዋል። የህዝብና መንግስት መሰረተ ልማቶችን በመጠበቅ ከ10 ዓመታት በላይ መቆየታቸውን የገለጸው ዋና ሳጅን ድረስ ስንሻው የተለመደዉን መደበኛ የጥበቃ ስራችን እያከናወን በነበርንበት ወቅት በፕሮጀክቱ ባሉ ሳይቶች ላይ የነበሩ የስራ ባልደረቦቻችንን ትጥቅ በማስፈታት፣ አፍነውና እጃቸውን በካቴና አስረው ወደ መቀሌ ሲወስዷቸው እጃችንን ከምንሰጥ ብለን ወደ ጫካ በመግባት ለሚተኮስብን ተኩስ ምላሽ በመስጠት ለማምለጥ ችለናል ብለዋል። እኛ ለአንድ ብሔር የቆምን ሳይሆን ከሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተውጣጣንና ሀገራችን ኢትዮጵያ በአንድነት ስንጠብቅ የኖርን በመሆኑ እንደዚህ አይነት የሀገር ክህደት ይፈጸምብናል ብለን አልጠበቅንም … [Read more...] about “የትግራይ ተወላጅ የፖሊስ አባላት አፈሙዝ ወደ እኛ በማዞር የፈጸሙብን ክህደት በጣም አሳዝኖናል”
በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ታጣቂው ህወሓት ልዩ ኃይል በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት እየተደመሰሰ ይገኛል። በዚህ ታላቅ ጀብድ ሰራዊቱ የህወሓት ስግብግብ ኃይል ለጦርነት እየተጠቀመባቸው የነበሩ ከ230 በላይ ክላሽንኮቭ፣ ከ1 ሺህ በላይ የእጅ ቦምብና ሌሎች ተተኳሽ መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ዕዝ የሰው ሐብት ልማትና የሚዲያ አስተባባሪ ኮሎኔል ደጀኔ ጸጋዬ ተናግረዋል። እየተካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ለህልውና ዘመቻ የአማራ ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት በተሰጣቸው ቀጣና በጠላት ላይ ከባድ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸምና በመደምስስ ግዳጃቸውን በብቃት እየፈጸሙ መሆኑንም ማመላከታቸውን ፋና ዘግቧል። በሌላ በኩል በጋምቤላ ከልል ዲማ ወረዳ በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 5 ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና አንድ F1 የእጅ ቦንብ ከስድስት ተጠርጣሪ ጋር መያዙን … [Read more...] about በርካታ ቁጥር ያለው የህወሓት የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ሥር ዋለ
ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!
በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ ያላቸውን የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ መወሰኑን ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎቹ በቀጠሯቸው የጥበቃ አባላትና ተባባሪዎቻቸው ባንኮችንና የተለያዩ ድርጅቶችን ሲዘርፉ እና ሲያዘርፉ ነበርም ብሏል። በተጨማሪም 'የህወሓትን ተልዕኮ ለመፈፀም የተለያዩ ግለሰቦችን ወደ ኤጀንሲዎቹ አስርገው በማስገባት እና የጦር መሣሪያ በማስታጠቅ በኅብረተሰቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ጥቃት ለመፈፀም እያሴሩ ነበር' ሲል አስታውቋል። በዚህም:- 1. ንስር የሰው ሃይል እና የጥበቃ አገ/ሃ/የተ/የግ/ማ 2. አጋር የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 3. ስብኃቱና ልጆቹ የንብረት አስ/ጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 4. ሰላም ሴኩሪቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ 5. ኃይሌ ተክላይ … [Read more...] about ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!
በወጋገን ባንክ በርካታ የጦር መሠሪያ፤ በሱር ኮንስትራክሽን ደግሞ የሬዲዮ መገናኛ ተገኘ
በወጋገን ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ለጥበቃ አገልግሎት ከሚያስፈልገው ውጭ የጦር መሠሪያ ተከማችቶ መገኘቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ለሸገር ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡ ከተገኙት መሣሪያዎች አንዳንዱ በፀጥታ ኃይሉ እጅ የሌሉ ጭምር መሆናቸውን ነው የገለጹት፡፡ በተያያዘ ዜናም 97 የእጅ ሬድዮ 23 የረጅም እርቀት የትከሻ መገናኛ ሬድዮ ከሱር ኮንስትራክሽን በብርበራ መያዙን ትላንት በተሰጠ መግለጫ ተጠቅሷል፡፡ በከተማው የተያዙ ባለሀብቶችም እንዳሉ ይሰማል ይህስ በምን መስፈርት ነው ሲል ሸገር ላቀረበላቸው ጥያቄ ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው የሕወሓትን ቡድን በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የደገፉ ባለሀብቶች በማስረጃ ስለመያዛቸው ለጣቢያው ገልጸዋል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በወጋገን ባንክ በርካታ የጦር መሠሪያ፤ በሱር ኮንስትራክሽን ደግሞ የሬዲዮ መገናኛ ተገኘ
በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው
የአገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙ የጁንታው ሕወሓት ቡድን ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የጥፋት ቡድኑ አባላት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀትም ከተለያዩ ክልሎች አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ያላቸውን ኃይሎች በመመልመል ትግራይ ክልል ድረስ በመውሰድ ለእኩይ ተልዕኮቸው ስኬት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በማድረግ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ብሄርን ከብሄር በማጋጨት እና በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ንፅሁን ዜጎች እንዲገደሉ፣ በአካልና በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡ እነዚህ የሀገር ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል እንዲሁም ህገ-መንግስቱንና … [Read more...] about በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው
የማይካድራ ዕልቂት
በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። በምዕራባዊ ትግራይ ሁመራ አቅራቢያ «ማይካድራ» በተባለው አካባቢ የትግራይ ልዩ ኃይል ባልታጠቁ የአማራ ተወላጆች ላይ በሌሊት አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን ከሞት ያመለጠ የዐይን እማኝ ገለፀ። ጥቃቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል ነው ሲል ደግሞ የአማራ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ዐስታውቋል። ድርጊቱ የተጀመረውን ሕግ የማስከበር ሂደት ህወሓት ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲቀየር የዘየደው መላ ነውም ብሎታል። አንዳንድ የአማራ ክልል ነዋሪዎች የህወሓት የተስፋ መቊረጥ ስሜት ነው፤ ኅብረተሰቡ ህወሓት በዘየደው የብቀላ ሂደት … [Read more...] about የማይካድራ ዕልቂት
የበረኻ ወንበዴዎቹ ያለከመከሰስ መብት ተነሳ
ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ዛሬ የተሰበሰበው የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ አቃቤ ህግ በተለያዩ ወንጀሎች የጠረጠራቸውን ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ በሙሉ ድምጽ አፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 4ኛ መደበኛ ስብሰባው በወንጀል የተጠረጠሩ የምክር ቤት አባላትን ያለመከሰስ መብት አንስቷል። በዚህም መሰረት፦ 1. ደብረጸዮን ገብረሚካኤል 2. አስመላሽ … [Read more...] about የበረኻ ወንበዴዎቹ ያለከመከሰስ መብት ተነሳ
በወልዲያ ከተማ የወንበዴዎቹን ተልዕኮ ሊያስፈጽሙ የነበሩ 25 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ 25 የህወሓት ተልዕኮ ተቀብለው የጥፋት ሴራቸውን በንፁሃን ላይ ለማድረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ውለዋል። የጥፋት ኃይሎቹ በነዋሪዎች እና በፀጥታ ኃይሉ የጋራ ጥረት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የወልዲያ ከተማ የህዝብ ሰላምና ደህንነት ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ትዕዛዙ ጫኔ አስታውቀዋል። ኢንስፔክተሩ ግለሰቦቹ በተያዙበት ወቅት የተለያዩ መታወቂያዎች መያዛቸውን ነው የተናገሩት። እንዲሁም ከአንድ ሰው ላይ እስከ ዘጠኝ የተለያዩ የባንክ ደብተሮች በውስጣቸውም እስከ 400 ሺህ ብር ድረስ ተገኝቶባቸዋል ነው ያሉት። ፖሊስ በተጠርጣሪዎች ላይ አስፈላጊውን ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝም ከአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።©ፋና ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በወልዲያ ከተማ የወንበዴዎቹን ተልዕኮ ሊያስፈጽሙ የነበሩ 25 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ
“ምዕራብ የትግራይ ክልል ነጻ ወጥቷል” የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ
ጠቅላይ ሚኒስትርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ አሕመድ ከጥቅት ደቂቃዎች በፊት በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ይፋ እንዳደረጉት ምዕራባዊ የትግራይ ክልል ነጻ መውጣቱን ተናግረዋል፡፡ ሆኖም የበረሃ ወንበዴዎቹ ስብስብ በመከላከያ ሠራዊት ላይ ያደረሰው ዘግናኝ ግፍ ነጻ በወጡ ከተሞች እየታየ እንደሆነ በመልዕክታቸው በመግለጽ “ሙት ይዞን እንዳይሞት” በማት ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። መልዕክታቸው እንዲህ ይነበባል፤ “ለስግብግቡ ጁንታ ግፍ እስትንፋሱ፣ ጭካኔ ነፍሱ ነው። ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ሽራሮን ሲቆጣጠር፣ እጅና እግራቸውን የፊጥኝ ታሥረው የተረሸኑ የመከላከያ አባላትን አግኝቷል። ጭካኔው ልብ ሰባሪ ነበር። ዓላማው ኢትዮጵያን መስበር ነው። አላወቁም ከአልማዝ የጠነከረች መሆኗን። ዓላማው ሠራዊታችንንና ሕዝቡን አስቆጥቶ ለበቀል ርምጃ ማነሣሣት ነው። አላወቁም … [Read more...] about “ምዕራብ የትግራይ ክልል ነጻ ወጥቷል” የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐቢይ