• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የትህነግ አመራሮች አንገታቸውን በመቅላት አስከሬናቸውን ደብቋል” የዓይን እማኞች

September 2, 2021 01:26 pm by Editor Leave a Comment

አሸባሪው ህወሓት በደብረ ዘቢጥ ግምባር በተወሰደበት እርምጃ የተደመሰሱበትን የጦር አመራሮች አንገታቸውን በመቅላት አስከሬናቸውን እየደበቀ መሸሹን በግምባሩ ላይ በውጊያ የተሳተፉ የዓይን እማኞች ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ገልጸዋል።

በደብረ ዘቢጥ ግምባር ላይ ያሉት ሻምበል ጌታሁን ካሳዬ በስፍራው ለሚገኙት  ዘጋቢዎቻችን በሰጡት መረጃ፤ በአውደ ውግያው  አሸባሪው  ቡድን የጦር አመራሮቹ ሲደመሰሱበት አንገታቸውን ቆርጠው በመደበቅ ማንነታቸውን ለመደበቅ እንደሚሞክሩ ተናግረዋል።

እንደ ሻምበል ጌታሁን ገለጻ፤ የአሸባሪው ቡድን ከዚህ ቀደም በነበረው የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት አዋጊዎቹ ሲሰው ማንነታቸው ይፋ እንዳይወጣ አንገታቸውን ይቆርጥና ይደብቅ ነበር። በህልውና ዘመቻ ወቅትም ተመሳሳይ ድርጊት በመፈጸም በተለይም በደብረ ዘቢጥ ግምባር የተሰውበትን በርካታ የጦር አመራሮች አንገታቸውን በመቁረጥ እጅግ አስነዋሪ ተግባር እየፈጸመ ይገኛል።

ይህ የጠላት ቡድን ህጻናትን ፊት ለፊት በማሰለፍ እያስፈጃቸው ነው ያሉት ሻምበል ጌታሁን፤ በግምባሩ በኢትዮጵያ ሰራዊት በተወሰደበት ከፍተኛ ጥቃት በርካታ የጦር መሪዎቹም  ተደምስሰውበታል። እውነቱ ይፋ እንዳይወጣ በሚልም የለመደውን አንገት የመቁረጥ ተግባር  መፈጸሙን ገልጸዋል።

የሚሊሻ ቡድኑን ተቀላቅሎ  በደብረ ዘቢጥ በግምባር ለውግያ የተሰለፈው ሰፊው በቀለ አሸባሪው በአውደ ውግያው ከፍተኛ ኪሳራ እየደረሰበት ስለመሆኑ ይናጋራል።

የጦር አመራሮቹ ጭምር እየተመቱ እንዳሉና በተለይም የተሰውበትን አመራሮች ዘግናኝና ኢ ሰብዓዊ በሆነ መልኩ አንገታቸውን በመቅላት ማንነታቸው እንዳይታወቅ በማድረግ ጥለው ከሸሿቸው አስከሬኖች መመልከቱን ገልጾልናል። (ኢ.ፕ.ድ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ከዝግጅት ክፍሉ፤ አንገታቸው የተቆረጡ የትህነግ ሰዎች ፎቶ ቢኖሩንም ከጋዜጣችን ሥነምግባር አንጻር አግባብ ስላልሆነ አላተምነውም።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule