በለውጡ ዋዜማ የገጠመን መፈናቀል በሚሊዮን የሚቆጠር እንደነበርና በአንድ ጉድጓድ በርካቶችን የመቅበር ሂደት ይታይ ነበር፤ከለውጡ በፊት የአገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የተቋቋመ ተቋም የኦነግን ባንዲራ በገፍ በማሳተምና እሱን የያዙ ሰዎችን ኢሬቻ በዓል የሚከበርበት ቦታ ውስጥ በማስገባት ሰዎችን ለማፈን ይጠቀምበት ነበር፤ ሎጎ የሌላው ባንዲራም በተመለከተ ተመሳሳይ ነው፤ይህም በስልጣን ላይ የነበረው ቡድን ዜጎችን ለማሳዘንና የተፈራው ለውጥ እንዳይመጣ ለማድረግ ነው፤ከለውጡ ጋር በተያያዘ ለውጡን በቅርበት በሚመሩት አካላት ላይ የደህንነት አስጨናቂ ክትትልና ዛቻ እንዲሁም የእስር ማዘዣ እስከማውጣት ተደርሶ ነበር - በጁንታው ስብስብ፤ከኢህአዴግ ሊቀመንበር ምርጫ ጋር በተያያዘ የፈለጉት ሰው ለማስመረጥ የጁንታው አባላት ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም - ግን አልተሳካላቸውም፤ፍላጎቱ እኛን … [Read more...] about ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ፓርላማ ፊት ቀርበው ከተናገሩት
abiy ahmed
ኤርሚያስ ለገሰ፤ “ለምኖ ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል”
የኢህአዴግ ካድሬና እያለቀሰ ስለኢህአዴግ ይሰብክ የነበረው የበረከት ስምዖን የጡት ልጅ ኤርሚያስ ለገሠን በተመለከተ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” እና “የኤርምያስ ለገሰ ቪዲዮዎች ፉከራ ሲጋለጥ” በሚል ሁለት የአስተያየት ጽሁፎችን አቅርቦ ነበር። በወቅቱ እነዚህን ጽሁፎች በማተማችን ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶብናል። የተሰጡትንም አስተያየቶች አሁንም በጽሁፎቹ ግርጌ ማግኘት ይቻላል። ኤርምያስ ለረጅም ጊዜ እንደ ትልቅ ነገር አድርጎ ሲያወራው የነበረው ቪዲዮ የኔታ ቲዩብ ይፋ አድርጎታል። አበበ ገላው ደብቆ ያስቀመጠውና ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሚናገር ትልቅ ምሥጢር የያዘ የድምጽ ቅጂ አለ በማለት ኤርምያስ ቅጂው አንዲወጣ አበበን ባደባባይ ይገዳደር ነበር። አሁን በወጣውና ኤርምያስ ምሥጢር ሲለው በነበረው ድምጽ ቅጂ ውስጥ ግለሰቡ … [Read more...] about ኤርሚያስ ለገሰ፤ “ለምኖ ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል”
ዶ/ር ዐቢይ፤ ህወሃት ሚሊዮኖች ለምርጫ ከሚያባክን የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም?
የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አይኖርም❗️ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በትግርኛ ቋንቋ በነበራቸው ቆይታ፥ “በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የፌዴራል መንግስት ይሁን እኔ በበኩሌ የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ይኖራል ብለን በፍፁም አናስብም” ብለዋል። “የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ምስረታ ጀምሮ እስከሁን ድረስ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ቆይቷል አሁንም እየተጫወተ ነው” ሲሉም ገልፀዋል። “ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ አሁን ባለንበት ወቅት ሶስት ችግሮች አሉ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ከእነዚህም የመጀመሪያው ከለውጥ ጋር የተያያዘ ችግር ነው፣ ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲና ህወሐት ካላቸው ግንኙነት ጋር የተያያዘ ነው፣ ሶስተኛው ደግሞ ልዩነት ማስፋት የሚፈልጉ አካላት የሚፈጥሩት … [Read more...] about ዶ/ር ዐቢይ፤ ህወሃት ሚሊዮኖች ለምርጫ ከሚያባክን የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም?
ህወሃት “የመጨረሻ” ያለው ሤራ መክሸፉን መቀበል አቅቶታል
መንግሥት ህወሃትን ቀስ በቀስ ሥሩን እየቆራረጠ ቢቆይም አብዛኞች ባለመረዳትና በተገዙ ኃይሎች ውዥንብር ዕድሜው ሊራዘም እንደቻለ ለህወሃት ቅርበት ያላቸው እየገለጹ ነው። በተቀነባበረ ዕቅድ ሃጫሉ እንዲገደል ተደርጎ መንግሥትን ለመገልበጥ የታቀደውና የመጨረሻ የተባለው ሤራ መክሸፉ ህወሃት መንደር ግራ መጋባት መፍጠሩ ተስምቷል። የዐቢይ አስተዳደር እንደሚባለው ደካማ እንዳልሆነም አንዳንዶቹ በይፋ ሲናገሩ ተደምጧል። ለውጡን ተክትሎ ከህወሃት አሰልቺ የስብሰባና የግምገማ (ምይይጥ) ባህል በተቃራኒው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በፍጥነት መጓዛቸውና ለህወሃቶች ከጅምሩ የማሰቢያ ጊዜ የከለከለ ነበር። የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንደሚሉት፤ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች ሲነጋ ልክ እንደማንኛውም ተራ ዜጋ ከፍተኛና አዳዲስ ውሳኔዎችን ይሰማሉ። በዚህም እነርሱ ለአንዱ ጉዳይ አንድ ወር ሲሰበሰቡና … [Read more...] about ህወሃት “የመጨረሻ” ያለው ሤራ መክሸፉን መቀበል አቅቶታል
“የህዳሴ ግድብ ስምምነት ፊርማ እንዲዘገይ አመራር ሰጥቻለሁ” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የተገዙ ሌት ከቀን እየደከሙ ነው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ ከአደራዳሪዎቹ ጋር በስልክ ከተነጋገሩ በኋላ የህዳሴ ግድብ ስምምነት ፊርማ እንዲዘገይ አመራር መስጠታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ። ዐቢይ ከትራምፕ ጋር በስልክ መነጋገራቸው ይፋ ከሆነ በኋላ ራሳቸውን ተንታኝ ያደረጉ ወገኖች የስምምነት ፊርማው እንዲፈረም በተደራዳሪዎች ላይ ጫና እንደፈጠሩ በመግለጽ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲያጠልሹዋቸው ከርመው ነበር። ዶ/ር ዐቢይ ሰኞ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ባደረጉት ጥያቄና መልስ እንደገለጹት የህዳሴውን ግድብ አስመልክቶ የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፎ መስጠትን በተመለከተ የሚደረግ አንድም ዓይነት ስምምነት እንደማይኖር አረጋግጠዋል። ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ከአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስትር ስቴፈን ሙኑሺን እና ከዓለም ባንኩ ፕሬዚዳንት … [Read more...] about “የህዳሴ ግድብ ስምምነት ፊርማ እንዲዘገይ አመራር ሰጥቻለሁ” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
“ጦርነት የሲዖል ተምሳሌት ነው” የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኖርዌይ፣ ኦስሎ የኖቤል የሰላም ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች፤ • የኖርዌይ የኖቤል ኮሚቴ ለሰጠኝ እውቅና አመሰግናለሁ • ለኢትዮ-ኤርትራ የሰላም ስምምነት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ የሰላም ቁርጠኝነት ወሳኝ ነበር • ይህንን ሽልማት የምቀበለው የአፍሪካ እና የዓለም ህዝቦችን ወክዬ ነው፤ በኢትዮጵያውያን እንዲሁም በኤርትራውያን እና በኢሳያስ አፈወርቂም ስም ነው • እዚህ የደረስኩት በብዙ ጦርነት ውስጥ አልፌ በዕድል ነው፤ ይህን ሳያዩ ያለፉ ብዙ ናቸው፤ ከ20 ዓመታት በፊት በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት የሬድዮ ኦፕሬተር ነበርኩ • የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በርካታ ቀውሶችን አስከትሏል፤ ከ100 ሺህ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ተፈናቅለዋል፤ የንብረት መውደምም … [Read more...] about “ጦርነት የሲዖል ተምሳሌት ነው” የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ
ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
የህወሓት ዘመን ማብቂያው አካባቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ካለ በኋላ ለጠ/ሚ/ር ቦታ በተደረገው ሽኩቻ ዶ/ር ዐቢይ (የለማ ቡድን) አሸንፎ በወጣ ጊዜ የህወሓት ቡድን ወደ መቀሌ ሄዶ ሲመሽግ ስብሃት ነጋ በተፈጠረው ተናድዶ የሚከተለውን መናገሩ ታማጭ የመረጃ ምንጫችን አስታውቆናል። ስብሃት ነጋ በትግሪኛ የተናገረውና በአማርኛ ተተርጎመው የስብሃት ንግግር እንዲህ ይነበባል፤ “(ደመቀ) ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም 'ለምን?' ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ‘ፈርም’ ሲባል ‘አይሆንም አልፈርምም!’ ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ ጌታቸው (አሰፋ)ግን ‘አታስብ እሱ … [Read more...] about ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከአፍሪኮም ዕዝ አዛዥ በተነጋገሩ ማግስት አሸባሪው ህወሓት አሸባሪዎችን እያሠለጠነ መሆኑ ተሰማ
የኢትዮጵያ መንግሥት ባፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባል ተብሏል ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትሕነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኘው አሸባሪው ህወሓት አሸባሪዎችን እያሠለጠነ መሆኑ ተሰማ። መረጃው የአፍሪኮም አዛዥ ከጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር ከተመካከሩ በኋላ መውጣቱ የጉዳዩን አሳሳቢነት ብቻ ሳይሆን አቅጣጫ ጠቋሚም ነው ተብሏል። “ከባድ ሚስጥራዊ መረጃ፡- ጄ/ል ሳሞራ ዬኑስ በሱዳን 8ሺህ ወታደር እያሰለጠኑ ነው!” በማለት Ethiopian Think Thank Group የተሰኘው ድረገጽ ዛሬ ባስነበበው መሠረት መረጃው የተገኘው ከደኅንነት ሠራተኛ መሆኑን ተናግሯል። … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ከአፍሪኮም ዕዝ አዛዥ በተነጋገሩ ማግስት አሸባሪው ህወሓት አሸባሪዎችን እያሠለጠነ መሆኑ ተሰማ
“እርካብና መንበር” – ሙሴ እና ዐብይ*
ሳይታሰብ ብልጭ ብላ እንደገና ድርግም ያለችው የለውጥ ጭላንጭል፣ በእያንዳንዱ ልብ ውስጥ ተቋጥራ የነበረች የተስፋ ስንቅንም ይዛ ጭልጥ ያለች ይመስላል። አዕምሯችን ይህንን ቅጽበታዊ ለውጥ ለመቀበል ቢቸግረውም፣ በሌላኛው መነጽር ስንመለከተው ግን ይህ ሊሆን ግድ ይላል። በተዓምር የቆመች የዚህች የደም ምድር እጣ ፈንታን መጽሃፉ በአንዲት ምዕራፍ ውስጥ እንደቋጫት እንገነዘባለን። አይናችንን በደንብ ካልገለጥን ግን ነገሩን ላናየው እንችላለን። ስለዚህ መፅሐፉን ማንበብ ብቻ በቂ አይደለም። መረዳትንም ይጠይቃል። በደንብ የተረዳው ሰው፣ በለሆሳስ የተላለፈ መልዕክቱን ያገኘዋል። መልዕክቱም ግልጽ ነው። የነጻነት ተጋድሎ። በዚህ ፍልሚያ ውስጥ ሶስት ተዋንያን ይኖራሉ። ተሻጋሪ ሕዝብ፣ አሻጋሪ ሰው እና አሳዳጅ ሃይል። ከብዙ ትንቅንቅ እና ተጋድሎ በኋላ የአሳዳጁ ገቢር ከትዕይንቱ ይወጣና ሁለቱ … [Read more...] about “እርካብና መንበር” – ሙሴ እና ዐብይ*
“ኦሮሞ የሞተላትን አገር ጥሎ ወዴትም አይገነጠልም! ኦሮሞ ከኢትዮጵያ ውጭ አገር የለውም! አይኖረውም!” ዐቢይ አሕመድ
ህወሓት የሰየመለትን ስም፣ ዓርማና መዝሙር በማስወገድ ራሱን ነጻ ያወጣው የቀድሞው ኦህዴድ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የሚል ስያሜ በመውሰድ አዲስ ፓርቲ ሆኗል፤ የሚከተሉትን የኦዴፓ/ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት በማድረግ መርጧል 1. ዶክተር አብይ አህመድ፤ 2. አቶ ለማ መገርሳ፤ 3. ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፤ 4. አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ፤ 5. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ፤ 6. አቶ አዲሱ አረጋ፤ 7. አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ 8. አቶ ፍቃዱ ተሰማ፤ 9. ዶክተር ዓለሙ ስሜ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚከተሉትን 55 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትን መርጧል፤ እስካሁን ይፋ በሆነው የምርጫ ውጤት መሰረትም፦ ዶክተር አብይ አህመድ አቶ ለማ መገርሳ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ኢንጂነር ታከለ ኡማ አቶ ሽመልስ … [Read more...] about “ኦሮሞ የሞተላትን አገር ጥሎ ወዴትም አይገነጠልም! ኦሮሞ ከኢትዮጵያ ውጭ አገር የለውም! አይኖረውም!” ዐቢይ አሕመድ