• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዶ/ር ዐቢይ፤ ህወሃት ሚሊዮኖች ለምርጫ ከሚያባክን የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም?

July 29, 2020 03:26 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አይኖርም❗️ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በትግርኛ ቋንቋ በነበራቸው ቆይታ፥ “በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የፌዴራል መንግስት ይሁን እኔ በበኩሌ የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ይኖራል ብለን በፍፁም አናስብም” ብለዋል።

“የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ምስረታ ጀምሮ እስከሁን ድረስ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ቆይቷል አሁንም እየተጫወተ ነው” ሲሉም ገልፀዋል።

“ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ አሁን ባለንበት ወቅት ሶስት ችግሮች አሉ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ከእነዚህም የመጀመሪያው ከለውጥ ጋር የተያያዘ ችግር ነው፣ ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲና ህወሐት ካላቸው ግንኙነት ጋር የተያያዘ ነው፣ ሶስተኛው ደግሞ ልዩነት ማስፋት የሚፈልጉ አካላት የሚፈጥሩት ችግር ነው ብለዋል።

ሀሳብን በነፃነት ከመግለፅና ከሚዲያ ጋር በተያያዘ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ ይሁን በሁሉም ክልሎች አሁን ያሉ ሚዲያዎች ቀደም ሲል በሀገር ደረጃ ኖሮ አያውቅም፤ ይህ ሁሉም ሰው የሚያውቀው ሀቅ ነው ብለዋል።

ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ያሉ ሚዲያዎች በአጠቃላይ ችግር እንዳላቸው ይታወቃል። የመንግስት ይሁን፣ የግል ወይም የሀይማኖት ሚዲያዎች በተለያዩ ምክንያቶች ችግር አለባቸው። የትግራይ ሚዲያዎችም ከዚህ ድክመት ለፃ አይደሉም ሲሉም ተናግረዋል።

ሰሞኑን በብሮድካስት ባለስልጣን የተወሰደው እርምጃ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ በማባባስ ሚና ስለነራቸው ነው ብለዋል።

ባለስልጣኑ የወሰደው እርምጃ ሀገርን የማዳን ጊዜያዊ እርምጃ ብቻ ነው ብሎ መውሰድ ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ እርምጃው የትግራይ ህዝብ አፍ እንዳይኖረው ተብሎ የተወሰደ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም ብለዋል።

የሕግ የበላይነትና ዴሞክራሲን በተመለከተም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ የህወሓት መሪዎች በፌዴራል መንግስት የሕግ የበላይነትና ዴሞክራሲ እንዲረጋገጥ እንደሚፈልጉ ሁሉ በትግራይ ክልልም እንደዛ መፍቀድ አለባቸው ብለዋል።

“በፌዴራል ብቻ ዴሞክራሲ ብለህ በክልል ዴሞክራሲ ሊኖር አይገባም ማለት አትችልም” ያሉ ሲሆን፥ ዴሞክራሲ በፌዴራልም ይሁን በክልል ለሁሉም ህዝብ እና ፖለቲካ ፓርቲ አስፈላጊ እንደሆነ ሊያውቁ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ “በምርጫ አስፈላጊነትና ግዴታ ላይ ልዩነት ያለን አይመስለኝም፤ ለምርጫ ቀጠሮ በመያዝ እየተዘጋጀን እያለን ሁሉም ሰው እንደሚያውቀው የኮቪድ 19 ፈተና አጋጥሞናል። እንደሚታወቀው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫ እስኪደረግ በስልጣን ያሉ አካላት እንዲቀጥሉ ወስኗል። ይህ ውሳኔ ለብልፅግናም ለህወሓትም ይሰራል። ለህወሓት ለብቻው አትችልም የሚል ውሳኔ የለም” ብለዋል።

ምርጫ ከአንድ ዓመት በኋላ የሚደረግ ጉዳይ ሆኖ እያለ የትግራይ ክልል መንግስት በሚሊየኖች የሚቆጠር በጀት መድቦ ክልላዊ መርጫ አካሄዳለው ማለቱ ይገርማል ብለዋል።

“በአንድ በኩል የኮሮና ቫይረስ ለትግራይ ስጋት አይደለም ማለት ነው?፤ እዛ ያለው ሰው ኮሮና አይይዘውም አይገድለውም ማለት ነው?’ ወይ ደግሞ ዘመናዊ የሆነ ህክምና እና መድሃኒት ስላለን ችግር የለውም ማለት ነው። ለመረዳት አስቸጋሪ በመሆኑ እንደዚህ ዓይነት ጥያቄ ለማንሳት ያስገድዳል ያሉ ሲሆን፥ ቫይረሱ ለኢትዮጵያ ይቅር ለአሜሪካም አስቸግሯል፤ ትግራይ ለብቻው ኮሮና ችግር አይፈጥርብኝም ብሎ ማመን እንዴት ቻለ የሚል ጥያቄ መነሳት ያለበት ይመስለኛል ብለዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የትግራይ መንግስት ሚሊየኖች በመመደብ ምርጫ ከሚያደርግ ሁለት ሶስት የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም? የፌዴራል መንግስት ተበድሮ ነው በመቐለ ከተማ ውሃ እየሰራ ያለው። በአክሱምም የውሀ ችግር አለ። በበብዙ የትግራይ ዞኖች የውሀ ችግር በብዛት ይታያል። ወይ ደግሞ አንድ ሆስፒታል ለምን አይሰራም? አንድ ትምህርት ቤት ለምን አይገነባም? ሲሉም ይጠይቃሉ።

“ሁኔታው በዚህ መልኩ ሲታም ዝም ብሎ ምርጫ ከማካሄድ በዝርዝር ገምግሞ የተሻለ መንገድ መምረጥ ለህወሓት ይሁን ለትግራይ ህዝብ ጥሩ ይመስለኛል” ሲሉም ገልፀዋል።

“ከዚህ ውጭ የፌዴራል መንግስት በክልል ጉዳይ እጁን አስገብቶ አያውቅም፤ ለቀጣይም አያደርገውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ይህ ማለት ግን የፌዴራል መንግስት ሀላፊነት አሳልፎ ይሰጣል ማለት አይደለም፤ ህገ መንግስቱ ባስቀመጠው የፌዴራል ስልጣን መሰረት የሚሰራው ይሆናል ብለዋል።

የፌዴራል መንግስት ለትግራይ ክልል ከሚገባው በጀት ይሁን ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች አንድ ሳንቲምም ቢሆን አላጎደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ለወደፊትም እንደማያደርግ እና ይህን ለማድረግ ህጉ እንደማይፈቅድለትም አንስተዋል።

“የትግራይ ክልል መንግስት ግን የፌዴራል መንግስት ህጋዊ አይደለም፣ አናወቀውም፣ አናምንበትም፣ ከሱ ጋር ለመስራት አንችልም እያለ የበጀት ብቻ ጥያቄ በማንሳት እርምጃ ወሰደ ማለት የሚገባ አይመስለኝም” ሲሉም ተናግረዋል።

ከኤርትራ ጋር የተጀመረው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት በተመለከተም “በአሁኑ ወቅት መልካም የዲፕሎማሲእና ፀጥታን የተመለከተ ግንኙነት አለን” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ።

በኢኮኖሚ በኩልም የስልክ፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትና በሌሎች ዘርፎችም በጋራ መስራት መጀመሩን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ቀስ እያለ ወደ ተሻለ ደረጃ ሊደርስ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።

ከዚህ ግንኙነት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ከሆነች ትግራይም አብራ ትጠቀማለች፤ የትግራይ ጥቅምም የኢትዮጵያ ጥቅም ነው፤ ነጣጥለህ ትግራይ ብቻዋን ትጠቀማለች ወይም ትጎዳለች የሚል ግምገማ እንደማይሰራም ገልፀዋል።

በቅርቡ በኤርትራ በነበራቸው ቆይታም ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር በተለይም በልማት እና በሁለቱ ሀገራት ግኑኝነት ላይ መምከራቸውን አስታውሰው፤ በሁለቱም ሀገራት በኩል በተሻለ ደረጃ የመስራት ፍላጎት ስላለ በቅርቡ እየተሻሻለ እና እያደገ ይሄዳል የሚል እምነት እንዳላቸውም አስታውቀዋል። (ምንጭ፥ ፋና)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: abiy ahmed, tigray, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule