• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዶ/ር ዐቢይ፤ ህወሃት ሚሊዮኖች ለምርጫ ከሚያባክን የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም?

July 29, 2020 03:26 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አይኖርም❗️ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በትግርኛ ቋንቋ በነበራቸው ቆይታ፥ “በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የፌዴራል መንግስት ይሁን እኔ በበኩሌ የትግራይ ህዝብ የማይሳተፍበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ይኖራል ብለን በፍፁም አናስብም” ብለዋል።

“የትግራይ ህዝብ ከኢትዮጵያ ምስረታ ጀምሮ እስከሁን ድረስ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ቆይቷል አሁንም እየተጫወተ ነው” ሲሉም ገልፀዋል።

“ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ አሁን ባለንበት ወቅት ሶስት ችግሮች አሉ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ከእነዚህም የመጀመሪያው ከለውጥ ጋር የተያያዘ ችግር ነው፣ ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲና ህወሐት ካላቸው ግንኙነት ጋር የተያያዘ ነው፣ ሶስተኛው ደግሞ ልዩነት ማስፋት የሚፈልጉ አካላት የሚፈጥሩት ችግር ነው ብለዋል።

ሀሳብን በነፃነት ከመግለፅና ከሚዲያ ጋር በተያያዘ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ ይሁን በሁሉም ክልሎች አሁን ያሉ ሚዲያዎች ቀደም ሲል በሀገር ደረጃ ኖሮ አያውቅም፤ ይህ ሁሉም ሰው የሚያውቀው ሀቅ ነው ብለዋል።

ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ያሉ ሚዲያዎች በአጠቃላይ ችግር እንዳላቸው ይታወቃል። የመንግስት ይሁን፣ የግል ወይም የሀይማኖት ሚዲያዎች በተለያዩ ምክንያቶች ችግር አለባቸው። የትግራይ ሚዲያዎችም ከዚህ ድክመት ለፃ አይደሉም ሲሉም ተናግረዋል።

ሰሞኑን በብሮድካስት ባለስልጣን የተወሰደው እርምጃ ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ በማባባስ ሚና ስለነራቸው ነው ብለዋል።

ባለስልጣኑ የወሰደው እርምጃ ሀገርን የማዳን ጊዜያዊ እርምጃ ብቻ ነው ብሎ መውሰድ ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ እርምጃው የትግራይ ህዝብ አፍ እንዳይኖረው ተብሎ የተወሰደ ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም ብለዋል።

የሕግ የበላይነትና ዴሞክራሲን በተመለከተም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ የህወሓት መሪዎች በፌዴራል መንግስት የሕግ የበላይነትና ዴሞክራሲ እንዲረጋገጥ እንደሚፈልጉ ሁሉ በትግራይ ክልልም እንደዛ መፍቀድ አለባቸው ብለዋል።

“በፌዴራል ብቻ ዴሞክራሲ ብለህ በክልል ዴሞክራሲ ሊኖር አይገባም ማለት አትችልም” ያሉ ሲሆን፥ ዴሞክራሲ በፌዴራልም ይሁን በክልል ለሁሉም ህዝብ እና ፖለቲካ ፓርቲ አስፈላጊ እንደሆነ ሊያውቁ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ “በምርጫ አስፈላጊነትና ግዴታ ላይ ልዩነት ያለን አይመስለኝም፤ ለምርጫ ቀጠሮ በመያዝ እየተዘጋጀን እያለን ሁሉም ሰው እንደሚያውቀው የኮቪድ 19 ፈተና አጋጥሞናል። እንደሚታወቀው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫ እስኪደረግ በስልጣን ያሉ አካላት እንዲቀጥሉ ወስኗል። ይህ ውሳኔ ለብልፅግናም ለህወሓትም ይሰራል። ለህወሓት ለብቻው አትችልም የሚል ውሳኔ የለም” ብለዋል።

ምርጫ ከአንድ ዓመት በኋላ የሚደረግ ጉዳይ ሆኖ እያለ የትግራይ ክልል መንግስት በሚሊየኖች የሚቆጠር በጀት መድቦ ክልላዊ መርጫ አካሄዳለው ማለቱ ይገርማል ብለዋል።

“በአንድ በኩል የኮሮና ቫይረስ ለትግራይ ስጋት አይደለም ማለት ነው?፤ እዛ ያለው ሰው ኮሮና አይይዘውም አይገድለውም ማለት ነው?’ ወይ ደግሞ ዘመናዊ የሆነ ህክምና እና መድሃኒት ስላለን ችግር የለውም ማለት ነው። ለመረዳት አስቸጋሪ በመሆኑ እንደዚህ ዓይነት ጥያቄ ለማንሳት ያስገድዳል ያሉ ሲሆን፥ ቫይረሱ ለኢትዮጵያ ይቅር ለአሜሪካም አስቸግሯል፤ ትግራይ ለብቻው ኮሮና ችግር አይፈጥርብኝም ብሎ ማመን እንዴት ቻለ የሚል ጥያቄ መነሳት ያለበት ይመስለኛል ብለዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የትግራይ መንግስት ሚሊየኖች በመመደብ ምርጫ ከሚያደርግ ሁለት ሶስት የውሃ ጉድጓድ ለምን አይቆፍርም? የፌዴራል መንግስት ተበድሮ ነው በመቐለ ከተማ ውሃ እየሰራ ያለው። በአክሱምም የውሀ ችግር አለ። በበብዙ የትግራይ ዞኖች የውሀ ችግር በብዛት ይታያል። ወይ ደግሞ አንድ ሆስፒታል ለምን አይሰራም? አንድ ትምህርት ቤት ለምን አይገነባም? ሲሉም ይጠይቃሉ።

“ሁኔታው በዚህ መልኩ ሲታም ዝም ብሎ ምርጫ ከማካሄድ በዝርዝር ገምግሞ የተሻለ መንገድ መምረጥ ለህወሓት ይሁን ለትግራይ ህዝብ ጥሩ ይመስለኛል” ሲሉም ገልፀዋል።

“ከዚህ ውጭ የፌዴራል መንግስት በክልል ጉዳይ እጁን አስገብቶ አያውቅም፤ ለቀጣይም አያደርገውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ይህ ማለት ግን የፌዴራል መንግስት ሀላፊነት አሳልፎ ይሰጣል ማለት አይደለም፤ ህገ መንግስቱ ባስቀመጠው የፌዴራል ስልጣን መሰረት የሚሰራው ይሆናል ብለዋል።

የፌዴራል መንግስት ለትግራይ ክልል ከሚገባው በጀት ይሁን ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች አንድ ሳንቲምም ቢሆን አላጎደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ፥ ለወደፊትም እንደማያደርግ እና ይህን ለማድረግ ህጉ እንደማይፈቅድለትም አንስተዋል።

“የትግራይ ክልል መንግስት ግን የፌዴራል መንግስት ህጋዊ አይደለም፣ አናወቀውም፣ አናምንበትም፣ ከሱ ጋር ለመስራት አንችልም እያለ የበጀት ብቻ ጥያቄ በማንሳት እርምጃ ወሰደ ማለት የሚገባ አይመስለኝም” ሲሉም ተናግረዋል።

ከኤርትራ ጋር የተጀመረው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት በተመለከተም “በአሁኑ ወቅት መልካም የዲፕሎማሲእና ፀጥታን የተመለከተ ግንኙነት አለን” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ።

በኢኮኖሚ በኩልም የስልክ፣ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎትና በሌሎች ዘርፎችም በጋራ መስራት መጀመሩን ጠቅሰው፤ ይህ ደግሞ ቀስ እያለ ወደ ተሻለ ደረጃ ሊደርስ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።

ከዚህ ግንኙነት ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ከሆነች ትግራይም አብራ ትጠቀማለች፤ የትግራይ ጥቅምም የኢትዮጵያ ጥቅም ነው፤ ነጣጥለህ ትግራይ ብቻዋን ትጠቀማለች ወይም ትጎዳለች የሚል ግምገማ እንደማይሰራም ገልፀዋል።

በቅርቡ በኤርትራ በነበራቸው ቆይታም ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር በተለይም በልማት እና በሁለቱ ሀገራት ግኑኝነት ላይ መምከራቸውን አስታውሰው፤ በሁለቱም ሀገራት በኩል በተሻለ ደረጃ የመስራት ፍላጎት ስላለ በቅርቡ እየተሻሻለ እና እያደገ ይሄዳል የሚል እምነት እንዳላቸውም አስታውቀዋል። (ምንጭ፥ ፋና)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: abiy ahmed, tigray, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule