• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መቀሌን ከሽሬ ወይም ከበሻሻ የሚለያት የስበት ማዕከል የለም”

June 30, 2021 01:16 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ከትናንት በስቲያ አመሻሹን ከጋዜጠኞች ጋር ተገናኝተው ነበር። ሚዲያው በምርጫው ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለማመስገን በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር ላይም ሚዲያውን ካመሰገኑ በኋላ ስለ ምርጫው እና ስለ ትግራይ ሁኔታ ለጋዜጠኞች አብራርተዋል። ካነሷቸው ነጥቦች መሀከልም የተወሰኑትን በግርድፍ እንዲህ አስታውሻቸዋለሁ

በምርጫው እኛም ሆነ ተቃዋሚዎች የተመኘነውን ያህል ቡራቡሬ ፓርላማ አላገኘንም!

ተቃዋሚዎች በምርጫው ውጤት ደስተኛ ባይሆኑም በምርጫ ቦርድ፥ በፍርድ ቤት እና በሚዲያ ላይ ቅሬታ እንደሌላቸው ተስማምተናል!

ሚዲያው የትርክት ለውጥ ላይ በደንብ መስራት አለበት። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ከዚህም በላይ መስበክ አለበት!

በትግራይ ባካሄድነው ዘመቻ ተይዘውብን የነበሩትን መሳሪያዎች በሙሉ አስመልሰናል። ማስተካከል የምንፈልገውንም አስተካክለናል

መቀሌ ከዘመቻው በፊት የነበራትን የስበት ማእከልነት አጥታለች። ስለዚህ ከመቀሌ መውጣት ከሌሎች ቦታዎች ከመውጣት የተለየ ፋይዳ የለውም!

ከዘመቻው በፊት ጁንታው የነበረው ወታደራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ አቅም አሁን የለም።ከጦርነቱ በፊት በትግራይ ክልል እና በሌሎች ክልሎች መሀከል የነበረው ልዩነት ሰፊ ነበር። አሁን ግን እኩል ሆኗል ወይም ከዚያ በታች ወርዷል!

በዚህ ጦርነት ወደ 100 ቢሊየን ብር ገደማ አውጥተናል። ይህም ለትግራይ ከምንመድበው አመታዊ በጀት ከ13 እጥፍ በላይ ነው።ከአሁን በኋላ ግን እያወጣን ለመቀጠል ፍላጎት የለንም!

ጦሩ እየተጠቃ ያለው በህዝብ ነው።ራሳችን በምንቀልበው ህዝብ የምንጠቃ ከሆነ በእልህ አንዴ ገብተንበታል በሚል በዚያ መቆየት ፋይዳ የለውም!

ጦሩ በህዝብ ነው እየተገደለ ያለው።ስለዚህ በዚህ ሁኔታ  ጦሩ እንዲቆይ ካደረገን ጦሩ ወዳልተፈለገ እርምጃ ሊገባ ይችላል!

መጀመሪያ የገጠመን የተደራጀ ፥ የታጠቀ እና ዩኒፎርም የለበሰ ሀይል ነበር።እሱን በሁለት ሶስት ሳምንታት ውስጥ አስወግደናል። ከዚያም የተወሰነ የጎሬላ ውጊያ ነበር። አሁን ግን በየመንደሩ ስንሄድ የሚገጥመን ጦር የለም። የምናገኘው ህዝብ ነው።በቃ ሰላም ነው ብለን ስናልፍ ግን ከጀርባችን ህዝብ ነው ባልነው አካል እንጠቃለን!”

የትግራይ ህዝብ የጽሞና ጊዜ እንዲኖረው እና ነገሮችን በትክክል እንዲያገናዝብ እድል ሰጥተነዋል!

አሁን ፕራዮሪቲያችን ትግራይ ሳትሆን የህዳሴው ግድብ ነው። ስለዚህ ጦሩ ትኩረቱ ወደዚያ ነው!

እኛ ትግራይን ተቆጣጥሮ እንደ ቅኝ ገዢ የመቆየት አላማም አልነበረንም። የሚስተካከለውን አስተካክሎ ወደ ሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች መመለስ ነበር አጀንዳችን!

የጁንታው አላማ ማሸነፍ፥ ስልጣን መያዝ፥ ወዘተ አይደለም። እኔ አመድ ስለሆንኩ ኑ አብራችሁኝ አመድ ሁኑ ነው። እኛ በተቀደደልን ቦይ አንፈስም። ነገሮችን ቆም ብሎ አይቶ የራስን አካሄድ መምረጥ አስፈላጊ ነው። ስለዚህ ቆም ብለን አይተን ነው የወሰንነው!

በሳውዲ የነበሩ 45ሺ ኢትዮጵያውያንን የማንገላታቱ እንቅስቃሴ ክህዳሴ ግድቡ ጋር የተያያዘ ጫና የማድረግ ሂደት ነው!!

አማራ ክልል ከሁለት አመት በፊት ያለበት ስጋት የለበትም።ተክዷል የሚሉ ሀይሎች ህዝቡን እየናቁ ነው።የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አይደለም ዛሬ ለ30 አመታት ዱላ እየወረደበት እንኳን ከፍ ሲል ኢትዮጵያዊ ነው ዝቅ ሲል የበጌ ምድር ሰው ነው”

ጦሩ ከዚያ እንዲወጣ ከወሰንን በኋላ ትናንት እስከ እኩለ ሌሊት ብዙ የአለም መሪዎች ስልክ እየደወሉ ጦሩን ማውጣታችንን ሲቃወሙ ነበር!”

ጦራችን ተሸንፎ አይደለም የወጣው ነገር ግን ባለበት ቦታ ባእድ እንዲሆን ከተደረገ ደጀን ወደሚለው አካባቢ መሄዱ አግባብ ነው!

አሁንም ቢሆን ጦራችን መያዝ የሚገባው ቦታም ሆነ ሌላ ነገር ካለ ለመያዝ ከበቂ በላይ አቅም አለው!

እስከ ዛሬ እኩለ ቀን ድረስ መቀሌ የገባ አንድም የጁንታው ወታደር የለም!

አንጻንድ ነገሮችን መግዛት ፈልገን በገዛ ገንዘባችን እንዳንገዛ በአሜሪካ እና በጀርመን ያለን አካውንትን ዘግተውብናል!

ባለፉት ወራት ወጣቱ መከላከያን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበን ያገኘነው ሰው ብዛት ግን 5 ሺ ብቻ ነው!

የዚህ ጦሩን የማውጣት እርምጃን ውጤት በጥቂት ጊዜ ውስጥ እናየዋለን።ነገር ግን ዳግማዊ ድሉ የኢትዮጵያ እንደሆነች በእርግጠኝነት እነግራችኋለሁ!

(ንግግሮቹ ቃል በቃል የተወሰዱ ሳይሆኑ በግርድፍ የጻፍኳቸው ናቸው) በመቶዎች የሚቆጠሩ ከፌደራል እና ክልል ሚዲያዎች የተሰባሰቡ የሚዲያ ባለሙያዎች በተገኙበት በዚህ ፕሮግራም ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ረዘም ያለ ጊዜ ወስደው ሁኔታዎችን ባብራሩበት ወቅት አዳራሹ ውስጥ የነበረው ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን የሸራተን ሆቴል የመስተንግዶ ባለሙያዎች እንኳን ስራ አቁመው በትኩረት አዳምጠዋል። ባላጋንነው ለብዙ ደቂቃዎች አዳራሹ ውስጥ ሰው ያለ እስከማይመስል ድረስ ጸጥታ እና ሙሉ ትኩረት ነበር። በተለይ ጦሩ ባለፉት ሳምንታት በህዝብ ደረጃ የደረሰበትን ክህደት በገለጹበት ወቅት ብዙዎች ሲናደዱ ይታይ ነበር።

“አንድ ቦታ ላይ ህዝቡ መከላከያ ገብቶ ይጠብቀን ብሎ ጥሪ አቅርቦ መከላከያ በቦታው ከገባ በኋላ ሁኔታውን ለማስተካከል የተወሰኑ ወታደሮችን በቦታው አስቀምጦ ወደሌላ ስፍራ ለዘመቻ ሄደ። ነገር ግን ማታ ላይ በቦታው የቀረውን ወታደር፥ ይጠብቀን ብሎ የጠራው ህዝብ መሳሪያም ገጀራም ይዞ ወጥቶ ጨፍጭፎታል” ብለው ሲናገሩ በተለይ ብዙ ሰው ስሜቱ በንዴት በጣም ግሎ ነበር። በጥቅሉ ጦሩን ያወጡበት ፖለቲካዊ፥ ዲፕሎማሲያዊ፥ ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ ምክንያት ለብዙዎች አሳማኝ ሆኗል ማለት እችላለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእልህ ጦሩን መማገድ እንደማይፈልጉ እና ከዚህ ቀድም በነበሩ አገዛዞች የተሰራውን ስህተት መድገም እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል። ከኢኮኖሚያዊ ፥ዲፕሎማሲያዊ እና ፖለቲካው ምክንያት ባሻገር የጦሩን የጦር ሜዳ ሰሙናዊ ቆይታ ሲያብራሩ የነበረው ሁኔታ ሳውዲ እና UAE በየመን ከነበራቸው ዘመቻ ጋር አመሳስለውታል። እኔ ደግሞ Black hawk down የተሰኘው ፊልም ጥሩ ምሳሌ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።

በጥቅሉ ግን ያለው ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደርግን ስህተት መድገም እንደማይፈልጉ፥ በተዘረጋላቸው ወጥመድ ውስጥ ሰተት ብለው መግባት እንደማይፈልጉ፥ ትኩረታቸውን ወደ ሌሎች አጣዳፊ ጉዳዮች ለማድረግ እንደመረጡ የገለጹበት ሲሆን በትግራይ ጉዳይ ይህ ውሳኔያቸው ውጤታማ እንደሚሆንም እርግጠኛ ሆነዋል።በንግግራቸው ውስጥ ስለ ድርድር ያነሱበት አጋጣሚ ግን አልነበረም። (Ab Bela)

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ከዚህ በታች ይገኛል

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column Tagged With: abiy ahmed, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule