• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መቀሌን ከሽሬ ወይም ከበሻሻ የሚለያት የስበት ማዕከል የለም”

June 30, 2021 01:16 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ከትናንት በስቲያ አመሻሹን ከጋዜጠኞች ጋር ተገናኝተው ነበር። ሚዲያው በምርጫው ላደረገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለማመስገን በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር ላይም ሚዲያውን ካመሰገኑ በኋላ ስለ ምርጫው እና ስለ ትግራይ ሁኔታ ለጋዜጠኞች አብራርተዋል። ካነሷቸው ነጥቦች መሀከልም የተወሰኑትን በግርድፍ እንዲህ አስታውሻቸዋለሁ

በምርጫው እኛም ሆነ ተቃዋሚዎች የተመኘነውን ያህል ቡራቡሬ ፓርላማ አላገኘንም!

ተቃዋሚዎች በምርጫው ውጤት ደስተኛ ባይሆኑም በምርጫ ቦርድ፥ በፍርድ ቤት እና በሚዲያ ላይ ቅሬታ እንደሌላቸው ተስማምተናል!

ሚዲያው የትርክት ለውጥ ላይ በደንብ መስራት አለበት። ኢትዮጵያዊ አንድነትን ከዚህም በላይ መስበክ አለበት!

በትግራይ ባካሄድነው ዘመቻ ተይዘውብን የነበሩትን መሳሪያዎች በሙሉ አስመልሰናል። ማስተካከል የምንፈልገውንም አስተካክለናል

መቀሌ ከዘመቻው በፊት የነበራትን የስበት ማእከልነት አጥታለች። ስለዚህ ከመቀሌ መውጣት ከሌሎች ቦታዎች ከመውጣት የተለየ ፋይዳ የለውም!

ከዘመቻው በፊት ጁንታው የነበረው ወታደራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ አቅም አሁን የለም።ከጦርነቱ በፊት በትግራይ ክልል እና በሌሎች ክልሎች መሀከል የነበረው ልዩነት ሰፊ ነበር። አሁን ግን እኩል ሆኗል ወይም ከዚያ በታች ወርዷል!

በዚህ ጦርነት ወደ 100 ቢሊየን ብር ገደማ አውጥተናል። ይህም ለትግራይ ከምንመድበው አመታዊ በጀት ከ13 እጥፍ በላይ ነው።ከአሁን በኋላ ግን እያወጣን ለመቀጠል ፍላጎት የለንም!

ጦሩ እየተጠቃ ያለው በህዝብ ነው።ራሳችን በምንቀልበው ህዝብ የምንጠቃ ከሆነ በእልህ አንዴ ገብተንበታል በሚል በዚያ መቆየት ፋይዳ የለውም!

ጦሩ በህዝብ ነው እየተገደለ ያለው።ስለዚህ በዚህ ሁኔታ  ጦሩ እንዲቆይ ካደረገን ጦሩ ወዳልተፈለገ እርምጃ ሊገባ ይችላል!

መጀመሪያ የገጠመን የተደራጀ ፥ የታጠቀ እና ዩኒፎርም የለበሰ ሀይል ነበር።እሱን በሁለት ሶስት ሳምንታት ውስጥ አስወግደናል። ከዚያም የተወሰነ የጎሬላ ውጊያ ነበር። አሁን ግን በየመንደሩ ስንሄድ የሚገጥመን ጦር የለም። የምናገኘው ህዝብ ነው።በቃ ሰላም ነው ብለን ስናልፍ ግን ከጀርባችን ህዝብ ነው ባልነው አካል እንጠቃለን!”

የትግራይ ህዝብ የጽሞና ጊዜ እንዲኖረው እና ነገሮችን በትክክል እንዲያገናዝብ እድል ሰጥተነዋል!

አሁን ፕራዮሪቲያችን ትግራይ ሳትሆን የህዳሴው ግድብ ነው። ስለዚህ ጦሩ ትኩረቱ ወደዚያ ነው!

እኛ ትግራይን ተቆጣጥሮ እንደ ቅኝ ገዢ የመቆየት አላማም አልነበረንም። የሚስተካከለውን አስተካክሎ ወደ ሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች መመለስ ነበር አጀንዳችን!

የጁንታው አላማ ማሸነፍ፥ ስልጣን መያዝ፥ ወዘተ አይደለም። እኔ አመድ ስለሆንኩ ኑ አብራችሁኝ አመድ ሁኑ ነው። እኛ በተቀደደልን ቦይ አንፈስም። ነገሮችን ቆም ብሎ አይቶ የራስን አካሄድ መምረጥ አስፈላጊ ነው። ስለዚህ ቆም ብለን አይተን ነው የወሰንነው!

በሳውዲ የነበሩ 45ሺ ኢትዮጵያውያንን የማንገላታቱ እንቅስቃሴ ክህዳሴ ግድቡ ጋር የተያያዘ ጫና የማድረግ ሂደት ነው!!

አማራ ክልል ከሁለት አመት በፊት ያለበት ስጋት የለበትም።ተክዷል የሚሉ ሀይሎች ህዝቡን እየናቁ ነው።የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ አይደለም ዛሬ ለ30 አመታት ዱላ እየወረደበት እንኳን ከፍ ሲል ኢትዮጵያዊ ነው ዝቅ ሲል የበጌ ምድር ሰው ነው”

ጦሩ ከዚያ እንዲወጣ ከወሰንን በኋላ ትናንት እስከ እኩለ ሌሊት ብዙ የአለም መሪዎች ስልክ እየደወሉ ጦሩን ማውጣታችንን ሲቃወሙ ነበር!”

ጦራችን ተሸንፎ አይደለም የወጣው ነገር ግን ባለበት ቦታ ባእድ እንዲሆን ከተደረገ ደጀን ወደሚለው አካባቢ መሄዱ አግባብ ነው!

አሁንም ቢሆን ጦራችን መያዝ የሚገባው ቦታም ሆነ ሌላ ነገር ካለ ለመያዝ ከበቂ በላይ አቅም አለው!

እስከ ዛሬ እኩለ ቀን ድረስ መቀሌ የገባ አንድም የጁንታው ወታደር የለም!

አንጻንድ ነገሮችን መግዛት ፈልገን በገዛ ገንዘባችን እንዳንገዛ በአሜሪካ እና በጀርመን ያለን አካውንትን ዘግተውብናል!

ባለፉት ወራት ወጣቱ መከላከያን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበን ያገኘነው ሰው ብዛት ግን 5 ሺ ብቻ ነው!

የዚህ ጦሩን የማውጣት እርምጃን ውጤት በጥቂት ጊዜ ውስጥ እናየዋለን።ነገር ግን ዳግማዊ ድሉ የኢትዮጵያ እንደሆነች በእርግጠኝነት እነግራችኋለሁ!

(ንግግሮቹ ቃል በቃል የተወሰዱ ሳይሆኑ በግርድፍ የጻፍኳቸው ናቸው) በመቶዎች የሚቆጠሩ ከፌደራል እና ክልል ሚዲያዎች የተሰባሰቡ የሚዲያ ባለሙያዎች በተገኙበት በዚህ ፕሮግራም ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ረዘም ያለ ጊዜ ወስደው ሁኔታዎችን ባብራሩበት ወቅት አዳራሹ ውስጥ የነበረው ጋዜጠኛ ብቻ ሳይሆን የሸራተን ሆቴል የመስተንግዶ ባለሙያዎች እንኳን ስራ አቁመው በትኩረት አዳምጠዋል። ባላጋንነው ለብዙ ደቂቃዎች አዳራሹ ውስጥ ሰው ያለ እስከማይመስል ድረስ ጸጥታ እና ሙሉ ትኩረት ነበር። በተለይ ጦሩ ባለፉት ሳምንታት በህዝብ ደረጃ የደረሰበትን ክህደት በገለጹበት ወቅት ብዙዎች ሲናደዱ ይታይ ነበር።

“አንድ ቦታ ላይ ህዝቡ መከላከያ ገብቶ ይጠብቀን ብሎ ጥሪ አቅርቦ መከላከያ በቦታው ከገባ በኋላ ሁኔታውን ለማስተካከል የተወሰኑ ወታደሮችን በቦታው አስቀምጦ ወደሌላ ስፍራ ለዘመቻ ሄደ። ነገር ግን ማታ ላይ በቦታው የቀረውን ወታደር፥ ይጠብቀን ብሎ የጠራው ህዝብ መሳሪያም ገጀራም ይዞ ወጥቶ ጨፍጭፎታል” ብለው ሲናገሩ በተለይ ብዙ ሰው ስሜቱ በንዴት በጣም ግሎ ነበር። በጥቅሉ ጦሩን ያወጡበት ፖለቲካዊ፥ ዲፕሎማሲያዊ፥ ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ ምክንያት ለብዙዎች አሳማኝ ሆኗል ማለት እችላለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእልህ ጦሩን መማገድ እንደማይፈልጉ እና ከዚህ ቀድም በነበሩ አገዛዞች የተሰራውን ስህተት መድገም እንደማይፈልጉ አስታውቀዋል። ከኢኮኖሚያዊ ፥ዲፕሎማሲያዊ እና ፖለቲካው ምክንያት ባሻገር የጦሩን የጦር ሜዳ ሰሙናዊ ቆይታ ሲያብራሩ የነበረው ሁኔታ ሳውዲ እና UAE በየመን ከነበራቸው ዘመቻ ጋር አመሳስለውታል። እኔ ደግሞ Black hawk down የተሰኘው ፊልም ጥሩ ምሳሌ ይሆናል ብዬ አስባለሁ።

በጥቅሉ ግን ያለው ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የደርግን ስህተት መድገም እንደማይፈልጉ፥ በተዘረጋላቸው ወጥመድ ውስጥ ሰተት ብለው መግባት እንደማይፈልጉ፥ ትኩረታቸውን ወደ ሌሎች አጣዳፊ ጉዳዮች ለማድረግ እንደመረጡ የገለጹበት ሲሆን በትግራይ ጉዳይ ይህ ውሳኔያቸው ውጤታማ እንደሚሆንም እርግጠኛ ሆነዋል።በንግግራቸው ውስጥ ስለ ድርድር ያነሱበት አጋጣሚ ግን አልነበረም። (Ab Bela)

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ከዚህ በታች ይገኛል

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Right Column Tagged With: abiy ahmed, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule