የዓይን ምስክሮች በሰሜን ዕዝ ላይ ስለተፈጸመው ጥቂቱን ሲናግሩ እንዲህ ይላሉ፤ “ወደ ሰላሳ የሚጠጉ በሰሜን ዕዝ ውስጥ የሚገኙትን ወታደሮችን ገድለው፤ ልብሳቸውን አውልቀው፤ አስከሬናቸውን አንድ ላይ ከምረው ሌሊቱን ሲጨፍሩ አደሩ፤ አሁንም ድረስ አስከሬናቸው አልተቀበረም፤ አሞራና ጅብ እየበላው ነው።” ጄኔራል ባጫ ደበሌ ሰሞኑን አካባቢውን ቃኝተው ከተመለሱ በኋላ ሲናገሩ፤ “የታፈኑ አመራርና ወታደሮችን ጁንታው ልብሳቸውን አወላልቆ ራቁታቸውን ወደ ሻዕቢያ ሂዱ ብሎ ሰዷቸዋል፤ የባዕድ ጦር ልብስ ነው ያለበሳቸው፤ በመከላከያ ውስጥ ያሉ ትግርኛ ተናጋሪዎች የጁንታው ኔትዎርኮች ናቸው ጥቃቱን ያቀናጁት፤ … የተረሸኑ የመከላከያ አባላት ዘረኛው ጁንታ የሟቾችን አልባሳት አውልቆ ጸሃይ ላይ ለቀናት በማስጣት እንዲፈንዳዳ አድርጓል፤ የሌሎቹን አስከሬንም እንዳይቀበሩ በማድረግ ብዙዎች በጅብ … [Read more...] about የሰሜን ዕዝ እንዴት ሊጥቃ እንደቻለና ወንበዴዎቹ የፈጸሙት ሰቅጣጭ ግፍ
Archives for November 2020
ሕገወጥ የጦር መሣሪያ በቂርቆስ ተያዘ
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ የተለያዩ ሽጉጦች እና ጥይቶች እንደተያዙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ:: በከተማዋ ጥቃት ለመፈፀም እና ሰላም ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ የሚያደርገውን ክትትል አጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮሚሽኑ አስታውቋል። በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ስለሺ ሸንቁጤ እንደገለፁት ከቂርቆስ ወደ ቄራ አቅጣጫ በምሽት ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2A-41649 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ በክፍለ ከተማው ወረዳ 4 በተለምዶ 31 ቀበሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሲደርስ በፖሊስ አባላት ፍተሻ ሲደረግለት 4 የተለያዩ ሽጉጦች፣ 30 የክላሽ ጥይቶች ከነካርታው እና 39 የሽጉጥ ጥይቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል፡፡ በህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ላይ … [Read more...] about ሕገወጥ የጦር መሣሪያ በቂርቆስ ተያዘ
ህወሃት በአሶሳ ለጥፋት ሊጠቀምበት የነበረ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይና ገጀራ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ለህወሓት የጥፋት ተልዕኮ ማስፈጸሚያነት ሊውል የነበረ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይ የያዙ 59 የባንክ ሂሳብ ደብተሮች፣ ጥሬ ገንዘብ እና ገጀራዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ። በክልሉ ከህወሓት ተልዕኮ ወስደው ጥፋት ለመፈጸም በማሴር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች ቁጥር ከ70 በላይ መድረሱ ተገልጿል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አብዱልአዚም መሐመድ ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት፤ የህወሐት ጥፋት ቡድን ክልሉን ብሎም ሃገርን ለማተራመስ የሚያደርገውን ሴራ እየከሸፈ ነው። “ባለፉት ሶስት ቀናት የሃገር መከላከያ ሠራዊት፣ ፌደራል ፖሊስ፣ የክልሉ ልዩ ሃይል፣ ጸረ-ሽምቅ፣ ሚሊሻ እና በጎ ፈቃደኞች በተለይም አሶሳ ከተማን ትኩረት በማድረግ በቅንጅት እየሠሩ ይገኛሉ” ብለዋል። ግለሰቦች ስማቸውን እየቀያየሩ የቁጠባ ደብተሩን … [Read more...] about ህወሃት በአሶሳ ለጥፋት ሊጠቀምበት የነበረ ከ14 ሚሊዮን ብር በላይና ገጀራ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች የነበሩ ሁለት የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ
1. ህንፃ ተክለብርሃን ይባላል። የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 (መርካቶ) ዋና ሥራ አስፈፃሚ የነበረ በኃላ በእድገት የክፍለ ከተማው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ የነበረ ነው። 2. ገ/ትንሳኤ ዓርአያ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ዋና ሥራ አስፈፃሚ የነበረ በእድገት የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ጽ/ቤት ኃላፊ የነበረ በቅርብ ጊዜ ከአመራር የተቀነሰ ነው። ህብረተሰቡም ካሁን ቀደም ህዝብን እናገለግላለን በማለት ከተማችንን የእኩይ ተግባራቸው ማስፈጸሚያ ስፍራ ለማድረግ ከሚጥሩ ጸረሰላም አካላት በመራቅ የተለዩ እንቅስቃሴዎችን በተለይ በአገልግሎት መስጫ ተቋማት ፣ በሆቴሎች ፣በመዝናኛ ስፍራዎች እና በትራንስፖርት ስፍራዎች አጠራጥሪ ነገር ካጋጠመ በአካባቢው ለሚገኝ ፖሊስ እና የጸጥታ አካል … [Read more...] about በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች የነበሩ ሁለት የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ
ጠ/ሚ/ር ዐቢይ የህወሃት ወንበዴዎችን የሽምግልና ልመና ውቅድ አደረጉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የቀረበውን የሽምግልና ጥሪ ሳይቀበሉ ቀሩ። የቀጣናዊው ተቋም መሪ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በ4 የተለያዩ ጊዜያት ስልክ በመደወል የኢትዮጵያ አቻቸውን ለማግባባት ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ሱዳን ትሪቢውን የሃምዶክን ቢሮ አጣቅሶ የዘገበውን ሂቃያት ጋዜጣን ዋቢ አድርጎ በድረ ገጹ እንዳሰፈረው ዘገባ ከሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጉዳዩ ዓለም አቀፋዊ መልክ ሊይዝ የማይገባው የሃገር ውስጥ ጉዳይ ነው ብለዋል። ሃምዶክ ባለፈው ዓመት የኢጋድ ሊቀመንበር ሆነው ዐቢይ አህመድን መተካታቸው ይታወሳል። “የህወሀት ጁንታ ቡድን ትላንት የቀረቡለትን የድርድር እና የውይይት ዕድሎች ሁሉ አምክኖ ግብአተ መሬቱ ሊፈጸም ሲቃረብ የአደራዳሪ ያለ ብሎ መጮህ ጀምሯል” ሲል መግለጫ ያወጣው … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር ዐቢይ የህወሃት ወንበዴዎችን የሽምግልና ልመና ውቅድ አደረጉ
መከላከያ ሠራዊት የአማራ ክልል ሁመራ ኤርፖርት ተቆጣጣረ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የህውሓት ቡድን ከጠላት ጋር ጥምረት በመፍጠር ለእኩይ አላማ ሊጠቀምበት የነበረውን አውሮፕላን ማረፊያን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል። በርካታ ህወሓት ያደራጃቸው የልዩ ኃይል፣ የፖሊስ እና የሚሊሻ አባላት ለመከላከያ ሠራዊት እጃቸውን እየሰጡ መሆናቸውም ታውቋል። ሠራዊቱ ዘራፊው የህወሓት ቡድን ያደረሰበትን ድንገተኛ ጥቃት በመመከት የመልሶ ማጥቃት ስራ እየሰራ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማይዳሊ፣ ዳንሻ፣ ባዕከር፣ ልጉዲ እንዲሁም የሁመራ ሱዳን መንገድን እንደተቆጣጠረ መቆጣጠሩ ይታወቃል። (ፋና) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about መከላከያ ሠራዊት የአማራ ክልል ሁመራ ኤርፖርት ተቆጣጣረ
በስግብግቡ የህወሃት ጁንታ ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት ተጠናቋል
በስግብግቡ የሕወሓት ጁንታ ኃይል ላይ የተደረገው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት እንደተጠናቀቀ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። የአየር ኃይሉ በወሰደው እርምጃም በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ለማውደም መቻሉንም ገልፀዋል። "የአየር ኃይሉ በወሰደው እርምጃ በተለያዩ ስፍራዎች ላይ የነበሩ ሮኬቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ለማውደም ተችሏል። እነዚህ ሮኬቶች እስከ 300 ኪሎ ሜትሮች መወንጨፍ የሚችሉ በመሆናቸው እና በወንጀለኛው ቡድን ሮኬቶቹን የመጠቀም ፍላጎት በመኖሩ በመቐለ እና አካባቢዋ በነበረው የከባድ መሣሪያ ማስቀመጫ ላይ የአየር ኃይሉ እርምጃ እንዲወስድ ተደርጓል" ጠ/ሚ/ር ዐቢይ። አምባገነኑን እና ዘራፊውን የጁንታ ቡድን በአጭር ግዜ ውስጥ ይዘን … [Read more...] about በስግብግቡ የህወሃት ጁንታ ኃይል ላይ የተወሰደው የመጀመሪያው ዙር ኦፕሬሽን በስኬት ተጠናቋል
ጅቡቲ በህወሃት ዘመን በፈረመችው ውል መሠረት 16 የህወሃት ወታደሮችን አሳልፋ ሰጠች
ቁጥራቸው 16 የሆኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የህወሃት መኮንኖች ወደ ጅቡቲ ቢኮበልሉም ጅቡቲ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው እንደተሰጡ ተነገረ። የጅቡቲ ዜና ወይም Les Nouvelles de Djibouti በድረገጹ ይፋ ያደረገው ዜና ርዕስ “የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወታደሮችን ጅቡቲ ለኢትዮጵያ አሳልፋ ልትሰጥ ነው” የሚል ነበር። ይህ አሳልፎ የመስጠት ስምምነት የተፈረመው እኤአ በመጋቢት ወር 2017 ነበር። በወቅቱ ኢትዮጵያን ይጎበኙ በነበሩት ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጉሌህና ጠቅላይ ሚኒስትር በነበረው ኃይለማርያም ደሳለኝ መካከል ነበር። በስምምነቱ መሠረት ማንኛውም “ወንጀለኛ፣ አሸባሪ” ተብሎ የተጠረጠረና ከአንዱ አገር ወደሌላው ጥገኝነት ለመጠየቅ የሄደ አገራቱ አሳልፈው እንዲሰጡ የሚያደርግ ነበር። ይህንን ስምምነት በዋንኛነት የፈለገው ራሱን … [Read more...] about ጅቡቲ በህወሃት ዘመን በፈረመችው ውል መሠረት 16 የህወሃት ወታደሮችን አሳልፋ ሰጠች
ህጻናትን የሚማግደው የሌቦቹ ጀርባ
አዲሱ ህወሃት በአሮጌ አቁማዳ በትግራይ መቀሌ መሽገው የ13 አመት ልጅ እየመለመሉ ስልጠና ሲሰጡ የከረሙትና ትላንት በመከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት እንዲፈፀም ያደረጉት ሁለቱ ሙሰኛና የትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ጄኔራሎች በፎቶው የሚታዩት ናቸው! ብ/ጄ ተክለብርሃን ወ/አረጋይ፤ የዶ/ር ዐቢይ አስተዳደር ወደ ስልጣን ሲመጣ “ተደምሪያለሁ” በማለት ጊዜ ገዝቶ፤ ሚስቱንና ሶስት ሴት ልጆቹን አሜሪካ ወስዶ፤ ቤት ገዝቶ፤ አመቻችቶ፤ እንዲሁም ከመጀመሪያ ሚስቱ የወለደው ዳንኤል የተባለውን ልጁ በካናዳ እንዲኖር ያደረገው ተክለብርሃን፤ ከአሜሪካ ከተመለሰ በኋላ ወደ መቀሌ ሸሸ። ሁለት ትላልቅ ህንፃዎች በመገናኛ ወደ ሃያት በሚወስደው መንገድ ያሉት (ተገትረው የቀሩ) በኦሮሚያ በርካታ መሬቶች የሸጠ፣ ለበርካታ ዘመዶቹ በሃብት ጥግ ያደረሰ ሙሰኛ ነው! ሁለተኛው ብ/ጀነራል ኃ/ሥላሴ … [Read more...] about ህጻናትን የሚማግደው የሌቦቹ ጀርባ
መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ
ባለፉት 29ዓመታት ከተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆነ ከሲቪክና ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተሰምቶ በማያውቅ በሚያስብል ቁመና እና ክብደት፤ ወደፊት በታሪክ በሚጠቀስ መልኩ የዜጎችን የተግባር ድጋፍ የሚጠይቅ መግለጫ ከመንግሥት ተሰምቷል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፤ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመንግሥት የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከሁለት ዓመታት በፊት ግንባራቸውን ለጥይት፣ ደረታቸውን ለጦር ሰጥተው አደባባይ የወጡት የይስሙላ ፌዴራሊዝም ወገባቸውን አጉብጦት፣ ተስፋቸውን አጨልሞት ነው። ጥቂቶች ዜጎችን እያፈኑና እነርሱ እየከበሩ መምጣታቸው ቁጣቸውን አገዘፈው። ኢትዮጵያዊያን አገራቸው ሆና ለማየት ከሚያልሙት እጅግ እየራቀ መምጣት የቁጣቸውን ኃይል አገዘፈው። እውነተኛ የፌዴራል ስርዓትን ለመተግበር ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ዜጎች በጋራ የሚሳተፉበትና ተጠቃሚ የሚሆኑበት … [Read more...] about መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ