• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጅቡቲ በህወሃት ዘመን በፈረመችው ውል መሠረት 16 የህወሃት ወታደሮችን አሳልፋ ሰጠች

November 5, 2020 05:36 pm by Editor Leave a Comment

ቁጥራቸው 16 የሆኑ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውስጥ የነበሩ የህወሃት መኮንኖች ወደ ጅቡቲ ቢኮበልሉም ጅቡቲ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፈው እንደተሰጡ ተነገረ።

የጅቡቲ ዜና ወይም Les Nouvelles de Djibouti በድረገጹ ይፋ ያደረገው ዜና ርዕስ “የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወታደሮችን ጅቡቲ ለኢትዮጵያ አሳልፋ ልትሰጥ ነው” የሚል ነበር።

ይህ አሳልፎ የመስጠት ስምምነት የተፈረመው እኤአ በመጋቢት ወር 2017 ነበር። በወቅቱ ኢትዮጵያን ይጎበኙ በነበሩት ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጉሌህና ጠቅላይ ሚኒስትር በነበረው ኃይለማርያም ደሳለኝ መካከል ነበር።

በስምምነቱ መሠረት ማንኛውም “ወንጀለኛ፣ አሸባሪ” ተብሎ የተጠረጠረና ከአንዱ አገር ወደሌላው ጥገኝነት ለመጠየቅ የሄደ አገራቱ አሳልፈው እንዲሰጡ የሚያደርግ ነበር።

ይህንን ስምምነት በዋንኛነት የፈለገው ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር በማለት የሚጠራው የበረኻ ወንበዴዎች ቡድን ነበር። ቡድኑም በአገር ወስጥ የሚነሳበትን ተቃውሞ በማፈን በእጅጉ የተካነ በመሆኑ ከአገር ውስጥ አምልጠው ወደ ጎረቤት አገራት የሚሄዱትን በቁጥጥሩ ሥር ለማዋል ያደረገው እንደነበር ይታወቃል።

በዚህ ስምምነት ምክንያት የፖለቲካ አቋማቸው ከወንበዴው ህወሃት ጋር ያልተስማማ ተቃዋሚዎች በሙሉ እየተያዙ ተላልፈው ሲሰጡ መቆየታቸው ይታወቃል። ህወሃት በተመሳሳይ የኬንያን ድንበር በመጣስ ተመሳሳይ ተግባራት ሲፈጽም እንደነበር ይታወቃል።

ከሁለት ቀናት በፊት (ማክሰኞ) የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ወደ ጅቡቲ የሄዱት 16 የህወሃት ወታደሮች መካከል አንድ ኮሎኔል፣ አንድ ኮማንደር እና 12 ሌፍተናንቶች እንደሆኑ ዜናው ሲዘግብ ሁሉንም የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን በመጥቀስ ነበር።

ግለሰቦቹ ወደ ጅቡቲ ከገቡ በኋላ በጅቡቲው የሰነድና ደኅንነት አገልግሎት ምርመራ የተካሄደባቸው ሲሆን በነጋታው ማለትም ረቡዕ ማምሻው ላይ በጅቡቲ አየር ኃይል ተጭነው ወደ ኢትዮጵያ ተላልፈው ሲሰጡ ድርጊቱን ተቃውመው እንደነበር ዜናው ዘግቧል።

ጅቡቲ ኒውስ ዘገባውን ሲያጠናቅቅ “እነዚህ ግለሰቦች አዲስ አበባ የነበሩና ከህወሃት ጋር ሲሠሩ የቆዩ” መሆናቸውን በመጥቀስ ነበር።

አስራ ስድስቱ ከሃዲዎች ረቡዕ ዕለት አመሻሹ ላይ ወደ አዲስ አበባ ተጭነው በመጡበት ወቅት በጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሀመድ አሊ ዮሱፍ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡደን ረቡዕ ማምሻውን አዲስ አበባ መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መዘገቡ ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: 16 tplf, Djibouti, extradite

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule