መግለጫው ሲተረጎም ከኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ?? 尔,看起来是一句话,不过 尔,看起来是一句话,不过 木目心人尔,看起来是一句话,不过又是一句看不大懂得话,其实,ማንኛውም መርህ አልባ ቡድናዊ ትስስር – አደገኛ ጉዳይ ነው—ሊወገዱ እንደሚገባ ወስኗል? 个把两个字拆开成的一句话,木目心,就是想,人尔,就是你,合起来就是想你!!最初出现在一个网友的个性签名上,他的签名原来是:木目心人尔好好的!就是写给他心爱的人的哦! 想,其实就是一个人在木木的时候,双目看着一处一动不动的,这时候要是从ta的眼睛看进去,会看到有一个人在ta 的心里,而那个人就是ta 心爱的人!这就是恋爱中人对想的最好解释,也是木目心人尔真正的含义!心人尔,看起来是一句话,不过又是一句看不大懂得话,其实,它是把 字拆开成的一句话,木目心,就是想,人尔,就是尔,看起来是一句话,不过,合起来就是想你!!最初出现在一个网友的个性签名上,他的签名原来是:木目心人尔እንዲፈጠር በማድረጉም የተሰማውን … [Read more...] about የኢህአዴግ መግለጫ ግራ ላጋባቸው የተሰጠ ትንታኔ
Opinions
የኔ ሃሳብ
ግልጽ ደብዳቤ፦ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)
ጉዳዩ፦ በቂሊንጦ እሳት ሰበብ ስለታሰሩት ሰዎች የተደረገውን ምርመራ በተመለከተ እንደሚታወቀው ኢሰመኮ በቀን 20 ጥቅምት 2010፣ በደብዳቤ ቁጥር ሰመኮ/2.1/29/2010 እንደገለጸው ነሐሴ 1/2008 አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (ቂሊንጦ) ግቢ ውስጥ የተነሳውን እሳት መንስዔ ለማጣራት በተደረገው ምርመራ አሰቃቂ የመብቶች ጥሰቶች ተፈፅመዋል። በእነ መቶ ዐለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ (38 ተከሳሾችን) በተመለከተ መንግሥት ባለበት አገር ይፈፀማሉ ተብለው የማይጠበቁ የጥፍር መንቀል፣ በሚስማር ሰውነት የመብሳት፣ ግርፋት እና የመሳሰሉት አካላዊ ጉዳት የሚያደርሱ፣ ሰብኣዊ ክብርን የሚያዋርዱ የጭካኔ ተግባራት በተያዙ ሰዎች ላይ ተፈፅሞባቸዋል። ይሄ ሁሉ የሆነው ፍርድ ቤት በአደራ እንዲጠብቃቸው ያስረከበው የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ ነው። ሆኖም፣ ዋነኞቹ የምርመራው (ወይም … [Read more...] about ግልጽ ደብዳቤ፦ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)
“አውሬውን አቁስለነዋል፤ ይህ ግን በቂ አይደለም” ለማ መገርሳ
“አውሬው ቆስሏል*። ቆስሎ ስላልተኛ፣ ማቁሰሉ ብቻ በቂ አይደለም። ተመልሶ እንዳይመጣ እርግጠኞች መሆን አለብን።" የሚለው ቃል የወጣው ከ"ጽንፈኛው ዲያስፖራ" ወይንም ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አይደለም። ከአውሬው ጋር አጋር ሆኖ ከሚሰራ ድርጅት መሪ ነው። ያውም በገዥው ፓርቲ ልሳን። የ26 ዓመቱ ፖለቲካ እየተንከባለለ እዚህ ላይ ደርሷል። አንድ ሰው እውነትን በመናገሩ ጀርባው ተጠንቶ፣ ደሙ ተለክቶ፣ ግንባሩ ተገላልጦ፣ በሽብር በሚፈረጅባት ሃገር ውስጥ፣ ጥቂቶች የእድሜ-ልክ ፈራጅ ሆነው በተሰየሙበት ሃገር ይህ ተከሰት። እነ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዷለም አራጌ ከዚህ የባስ ነገር አልተናገሩም። በፍትህ ስም የሚቀለድባቸው እነ ፕ/ር መረራ ጉዲና እና በቀለ ገርባ ይህችን ያህል እንኳን አልተነፈሱም። መቀሌ ላይ በዝግ ስብሰባ፣ አዲስ አበባ ላይ በዝግ ስብሰባ፣ ፓርላማውም በዝግ … [Read more...] about “አውሬውን አቁስለነዋል፤ ይህ ግን በቂ አይደለም” ለማ መገርሳ
የኢትዮጵያውያን ህይወት ዋጋ ምን ያህል ወርዷል?
በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረ ሰው ህይወት ክቡር ነው። ከዚያም አልፎ ህይወት ያለውን ነገር ሁሉ በከንቱ አለማጥፋት በተፈጥሮ ህሊናችን ውስጥ ህግ ሆኖ ስለተቀመጠም ነው የሰው ብቻ ሳይሆን የሌላም ፍጥረት ህይወቱ አለአግባብ በጭካኔ ሲቀጠፍ የሚዘገንነን። የሰውን ህይወት ለማጥፋት መጀመርያ የራስን ህሊና ፍርድ መጣስና ማቆሸሽን ይጠይቃል። ዛሬ በኢትዮጵያ በየቀኑ በጭካኔ የሚቀጠፉ ለጋ ወጣቶች፣ ማምለጥ የማይችሉ ህፃናት፣ አዛውንት አባቶችና እናቶችን ለሚመመለከት፣ ብሎም ለሚያስብ ንፁህ ህሊና ላለው እረፍት የሚነሳ ነው። በተለይ ባለፉት አምሳ ዓመታት በግፍ የጠፋው ኢትዮጵያውያን ህይወት እጅግ የሚዘገንን ነው። አዎ አባቶቻችን የውጭ ወራሪን ለመከላከልና በነፃነት ለመኖር ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለዋል። አምባገነን የሆኑ የየአካባቢው መሳፍንት ግዛታቸውንና ሃብታቸውን ለማስፋት በሚያደርጉት … [Read more...] about የኢትዮጵያውያን ህይወት ዋጋ ምን ያህል ወርዷል?
በ’ርግጥ በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል ጥላቻ፣ በደልና ቂም በቀል አለ?
የትላንቱ እንቅፋት፣ ዛሬም ይመታናል የትላንቱ ገመድ፣ ዛሬም ይጠልፈናል ፤ ሰምተንም - አልሰማን፣ ሳሰማም ሰምተናል አይተንም - አላየን፣ ሳናይም አይተናል ላለመማር - መማር እኛ ተምረናል። አሁን… አሁን ''ከልሂቃኑ እስከ ኢ-ልሂቃኑ'' ድረስ፤ ቀድም ብሎ ሙሰላዊያንና ሂተለራዊያን፤ ካለፉት ሃምሳ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ሻአቢያዊያንና ወያኔያዊያን እንዲሁም ኦነጋዊያን ከባንዳ አያቶቻቸውና አባቶቻቸው የተቀበሉትን የፈጠራና የጥላቻ ታሪክ ስላወሩትና የስልጣን ኮርቻውን ስለተፈናጠጡት፤ የሚንናገሩትና የሚጽፉት ሁሉ እንድ ዕውነት ተቆጥሮ ፤ “በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል ጥላቻ፣ በደልና ቂም-በቀል አለ!" መባሉ ነው። ሌላውን ሁሉ ትተን ባለፉት 26 ዓመታት ብቻ ሻአቢያዊያን፣ ወያኔያዊያንና ኦነጋዊያን የሰሩትን ግፍና በደል፣ የዘሩትን ጥላቻና በቀል ብናስብ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ 'ርስ-በርሱ … [Read more...] about በ’ርግጥ በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል ጥላቻ፣ በደልና ቂም በቀል አለ?
የትግሬ ወያኔ ወደ እውነተኛ ቁመናው ሲመለስ!
የግለስብ ሁለንተናዊ ቁመናው የሚገለጥ ከሚመጣበት መህበረሰብ አኳያ ነው። ግለስቦቹ ተቧድነው የሚፈጥሩትም ማህበርና ድርጂትም ላይ የዚያው ማህበረሰብ አሻራ አብሯቸው ይኖራል። ለምሳሌ በአፍሪካ ቀንድ ያሉ ማህበረሰቦችን በዚህ አኳያ መዳሰስ ይቻላል። ይህን ማህበራዊ እይታ ያፍሪካ ቀንድ ወስጥ የሰፈሩ የተለያዩ ማህበረሰቦች የሚጋሩት ቢሆንም በሱማሌ፣ በኤርትራና በትግሬ ማህበረሰቦች መሀል ባያሌው የሚታየው በቤተሰባዊ (ክላን) አመለካከት ዙሪያ የሚታይ ማህበረሰባዊ መከፋፈል የላቀ ነው። በዚህ ረገድ ዛሬ ለነጻዪቱ ሱማሌ መበታትን ከፍተኛውን ሚና የተጫወተ የህዝቧ በክላን ዙሪያ ያጠነጠነ አመለካከት በማደግ ላይ የነበረውን ሀገራዊ አመለካከት ስለደፈጠጠው ነው። ዚያድ ባሬ የኦክቶበር አብዮት ብሎ የሰየመውን የ1962ዓም የመፈንቅ ለመንግስት ሲመሰርት ዋና የአገዛዙ መመሪያ አድርጎ ያስቀመጠው … [Read more...] about የትግሬ ወያኔ ወደ እውነተኛ ቁመናው ሲመለስ!
መኢአድ ሰማያዊ እና ሸንጎ ስምምነት መግለጫ
(መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው። … [Read more...] about መኢአድ ሰማያዊ እና ሸንጎ ስምምነት መግለጫ
የዘመናችን ሲኖድ የቱን ይመስላል?
በዚህ ዘመን ያለው ሲኖድ (ሸንጎ)የቱን ይመስላል? የዮቶርን ሸንጎ? የአርዮስፋጎስን ሸንጎ? ወይስ የክርስቲያኖችን የቱን ይመስላል? ይህንን ጥያቄ የፈጠረብኝ በጥቅምቱ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በተከሰተው ውዥንብር እንዴት ትመለከቱታላችሁ? በሚል ከህዝብ የቀረበ ጥያቄ ነው። በመጀመሪያ በዚህ ቅዱስ ስብሰባ ላይ ተሳሳቱ የተባሉ ወገኖች የሚታገዱበት የመነጋገሪያ አጀንዳ በሀራ ዘተዋህዶ ድረ ገጽ ተሰራጭቶ ተመለከትን። ቀጠለና አዲስ ተክል አባ ፋኑኤል በገንዘብ በገዙት ጵጵስና ወደ ቤተ ክርስቲያናችን ሰርገው ገብተው በየደረሱበት ህዝብ በማተራመስ ላይ እንዳሉ ከፓትርያርኩ አንደበት ተሰማ። በወቅቱ የቀረበውን ለመረዳት ከፈለጉ በቀይ ቀለም የተጻፈችውን ዓዲስ ተክል የምትለዋን ይጫኑ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) ቀሲስ አስተርአየ ታህሳስ 7 ቀን 2010 ዓ/ … [Read more...] about የዘመናችን ሲኖድ የቱን ይመስላል?
የኢትዮጵያ፤ የውይይትና መፍትሔ መድረክ መግለጫ
የሃገራችን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳሳቢ ሆኗል። ኢትዮጵያውያን በተለይ ላለፉት ሶስት ዓመታት በተከታታይና በመረረ ሁኔታ መንግስታቸውን ሲቃወሙ ይታያል። እንዲህ ያለ በተከታታይና በቆራጥነት የተካሄደ ሕዝባዊ ተቃውሞ በሃገራችን ታሪክ አልታየም። ገበሬዎች ሰልፍ ወጥተው “የህወሓት አገዛዝ በቃን” እያሉ ነው። የትናንሽ ከተማ ነዋሪዎች በነቂስ እየወጡ በመረረ ሁኔታ ሲጮሁ ይሄው ሶስት ዓመት ሆነ። ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አየወጡ ለውጥ እንፈልጋለን ሲሉ ይታያል። ነጋዴው ሱቁን እየዘጋ ተቃውሞውን ያሰማል። ኢትዮጵያውያን ያለ ልክ ለውጥ የፈለጉ መሆናቸውን የሚያሳይ መራራ ተቃውሞ በሃገሪቱ በሰፊው በየቀኑ ይታያል። ይሁን እንጂ ተቃውሞ በሚነሳባቸው አካባቢዎች የመንግስት ታማኝ ወታደሮች፤ በተለይ አጋዚ፤ የፌደራል ፖሊስና ልዩ ታጣቂዎች፤ ደህንነት በሚወስዱት ግብታዊ ርምጃ … [Read more...] about የኢትዮጵያ፤ የውይይትና መፍትሔ መድረክ መግለጫ
AHRE urges international investigation on the current ethnic violence in Eastern Ethiopia
Press Release Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE) is very troubled by repeated violent incidents of violence in Eastern Ethiopia that led to the killings of dozens of civilian ethnic Oromos and Ethiopian Somalis in the past week. The recent incident came amid ongoing tension in the border areas of Oromia and Ethio-Somali regional states that had already left several dead from both ethnic groups. Multiple sources reported that at least 16 Oromos were killed by Ethiopian … [Read more...] about AHRE urges international investigation on the current ethnic violence in Eastern Ethiopia










