• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በ’ርግጥ በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል ጥላቻ፣ በደልና ቂም በቀል አለ?

December 21, 2017 01:38 am by Editor Leave a Comment

የትላንቱ እንቅፋት፣ ዛሬም ይመታናል
የትላንቱ ገመድ፣ ዛሬም ይጠልፈናል ፤
ሰምተንም – አልሰማን፣ ሳሰማም ሰምተናል
አይተንም – አላየን፣ ሳናይም አይተናል
ላለመማር – መማር እኛ ተምረናል።

አሁን… አሁን ”ከልሂቃኑ እስከ ኢ-ልሂቃኑ” ድረስ፤ ቀድም ብሎ ሙሰላዊያንና ሂተለራዊያን፤ ካለፉት ሃምሳ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ሻአቢያዊያንና ወያኔያዊያን እንዲሁም ኦነጋዊያን ከባንዳ አያቶቻቸውና አባቶቻቸው የተቀበሉትን የፈጠራና የጥላቻ ታሪክ ስላወሩትና የስልጣን ኮርቻውን ስለተፈናጠጡት፤ የሚንናገሩትና የሚጽፉት ሁሉ እንድ ዕውነት ተቆጥሮ ፤ “በኢትዮጵያ ህዝብ መሃከል ጥላቻ፣ በደልና ቂም-በቀል አለ!” መባሉ ነው።

ሌላውን ሁሉ ትተን ባለፉት 26 ዓመታት ብቻ ሻአቢያዊያን፣ ወያኔያዊያንና ኦነጋዊያን የሰሩትን ግፍና በደል፣ የዘሩትን ጥላቻና በቀል ብናስብ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ‘ርስ-በርሱ ተበላልቶ አይጨራረስም ነበር? የኢትዮጵያ ህዝብ ከአብራኩ በተከፈሉ ዜጎቹ እንዲተላለቅ ያልተቆፈረለት ጉድጉድ፤ ያለተሸረበበት ሴራ፣ ያለተነገረው የፈጠራ ታሪክ፣ ያለተወረወረበት ቦምብ፤ የለተኮሰበት ጥይትስ አለ ወይ? የኢትዮጵያ ህዝብ እንዳልሰማ ሰምቶና እንዳላየ አይቶ ስንቱን ፈታና አልፉል? አሁንስ ለአንድነቱና ለነጻነቱ እየታገለ ያለው በመሃከሉ ጥላቻና ቂም በቀል ወይም በደል ስላለ ነው? የጥላቻውም ሆነ የፈጠራ ታሪክ ተራኪዎቹ ነጻ አውጭ ነን የሚሉት ራሳቸውን የሾሙ ድኩማኖች አይደሉምን?

በኢትዩጵያዊያን መሃከል ጥላቻም ሆነ በደልና ቂም-በቀል የለም። ወደድንም ጠላንም ሀቁ ይህ ነው። እኛ ኢትዩጵያኖች እንደ ሸማ ድር ተሸምነን፤ ልዩነታችን እንድነታችን፣ አንድነታችን ልዩነታችን፣ ልዩነታችን ውበታችን ፤ ከምንም በላይ ደግሞ በሰውነታችን መከራውንና ደስታውን አብረን ለዘመናት ያሳለፋን መሆናችንና ወደፊትም በአንድነታችን ጸንተን እንደምንቀጠል፤ በዚች ሰዓት እንኳን ለተጠራጣሪዎች አይደልም፤ ለወያኔያዊያን፣ ኦነጋዊያንና ከምድረ-ገጽ መጥፋታችን እንደማለዳ ጸሃይ ለሚናፍቁ ሀሉ እያስተማርናቸው ነው።

ትላንትም ሆነ ዛሬ ያለው እውነታ ፤ ጥላቻ፣ በደልና ቂም በቀል ያለው ፤ …

1ኛ- ከታሪካዊ የሀገሪቱና የህዝቧ ጠላቶች ኢትዮጵያን የማፍረስ ዓላማ እውን ለማድረግ በተሰለፉ ባንዳዎች መንደርተኞች፤
2ኛ- የስልጣን ኮርቻ ለመፈናጠጥ አቋራጭ መንገድ በሚፈልጉ መሃይማንና ተማርን ባይ ጉልበተኛ ቡድኖችና ግለሰቦች፤
3ኛ- ምንም ዓይነት ሀገራዊ ሆነ ወገናዊ ስሜት ባልተፈጠረባቸው በግል ጥቅም በታወሩ ግለስቦችና ቡድኖች መሃከል ነው።

እውነታ ይህ ሆኖ ሳለ፤ ለማ መገርሳ ባህርዳር ሂዶ ገዱን ስለጎበኘ፤ ኢትዩጵያዊነትን የሚተርክ በተለቪዚዎን ስለታየ ፤ እርቅ እንደወረድና ወያኔም ችግር ላይ እንደወደቁ ተደርጎ ይሰበካል። የወያኔም ተራ ማታለል፣ እኛም መታለል ችሎታችን ሆኖ የሚቀጥለው እስከመቼ ነው? እድሜ ልካቸውን ውሸት ሲናገሩ የነበሩ ሰዎች ዛሬ ላይ ለፖለቲካ ፍጆታ በወያኔ ት’ዛዝ፣ የነበረንና ያለን እውነታ ስለተናገሩ እንዴት እንደታ’ምር ሊቆጠር ቻለ? እስከዛሬስ የት ነበሩ? እስቲ ሳምንታት ባልሞላ ግዜ ውስጥ ወያኔ ዘወር ብሎ ከጎንደር ህዝብ ጋር እርቅ ፈጠርኩ ብሎ “ሲቀረሻብን” ምን ታዘብን? እነ ለማ መገርሳ ባህርዳር ሄዱ ብለን ስንፈነድቅ፤ በጓሮ በር ፕ/ር ህዝቄየል የተባላ ግለሰብ ነጭ “የኢትዮጵያን ወዳጆችን” ሰብስቦ ”አማራ” ትላንትም፣ ዛሬም፣ ነገም፣ ጠላታችን ነው እያለ በጀርመኖች የተሰበከለትን ሲደነፋብን ለምንድነው እንደ አዲስ ነገር ያዙኝ! ልቀቁኝ የምንለው?

” …… በስምንተንኛው ሺ፣ በያዝነው ዘመን
ውሸት ገኖ አዘዘው፣ ሰው መስሎ ሰውን።….” አሉ አሉ ወሎየው ።

– በመጀመሪያ ደረጃ ማንና ማን ነው የተጣለውና ያጣለው?
– ለማና ገዱስ ማንን ነው የሚወክሉት? ማንስ ነው የወከላቸው?
– እነዚህ ሰዎች በወያኔ አዝማችነት በሀገርና በህዝብ ላይ ስንት ጉድ ሰርተዋል? አሁንስ ምን እያደረጉ ነው?
– ለመሆኑ ለማና ገዱ እንዲገናኙ ማን ፈቅዶላቸው ነው ? ከወንበሩስ ያስቀመጣቸው ማነው?
– ግድያውም ሆነ የጥላቻ ሰበካውና ሃውልት ማቆሙ የሚካሂደው ”ቦለቲከኛ” ነን በሚሉት እንጅ በየትኛው የህዝብ መሃከል ነው?
– ወያኔ ማጠፊያ ሲያጥረው አቅጣጫ ለማስለውጥና ለማታለል መሆኑ ሩብ ዓመታት አሳልፈንም እንዴት ግንዛቤ እናጣለን?

ተደራጅቶ የሚታገለው ያጣው ወያኔ፣ የህዝብ አመጽ ግን ግራ እያጋባው፣ ትቢያና አቧራ እየላሰ መነሳቱ ከ’ኛ ይልቅ እየገረመው የመጣው ለራሱ ለወያኔ ነው።

ታዲያ ወያኔ ወጥመድ ውስጥ እንዳለች አይጥ ሆኖ በሚሰራው ድራማ፤ እኛ ደግሞ ታዳሚዎች በመሆን አብረን እናጭበጭባለን። ”ወያኔ ተከፋፈለ!… አዜብ ‘ረግጣ ወጣች!… ኦህዴድና ብአዴን እንዲህ አሉ… እንዲህ ሆኖ…. የጡት አባታቼውን ወያኔን ተጋፉ!… ኦነጋዊያንና ጃዋራዊያን እንዲህ አሉ!…” እያልን የወያኔንና የሱን ተከታይ መንደርተኞች እሥስታዊ ባህሪ እናዳምቃለን። ግን ለምን ? ለምንድ ነው ከትላንቱ – ካለፈው የማንማረው? …

በወያኔና በኦነጋዊያን ቦይ መፍሰሳችን አቁመን፤ ስለአንደነት እያወራን አንደነት አተን ‘ርስ-በርስ መቆራቆሳችን ወደ ጎን ትተን የራሳችን የቤት ሥራ መሥራት፤ በወሬ ሳይሆን በተግባር ኢትዮጵያዊ ነኝ ከሚል ዜጋ የሚጠበቅ ነው። ግዜው ደግሞ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ አይደለም ፤ ዛሬ እንጅ። የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ ለድል የሚያበቃ መሪና አደራጅ አ’ቶ እንጅ መከፈል ከሚገባው በላይ መሰዋአትነቱን እየከፈለ ነው። እናም…

“እንዳትረግጡት…. የኢትዮጵያን ዐፈር- መሬት! ”
‘ባካችሁ ……… ’ባካችሁ……….
እናንት በምድረ- ኢትዮጵያ ያላችሁ፤
“አትሂዱ …..በ’ግራችሁ…”
ከቻላችሁ ….. “ብረሩ ክንፍ አው’ታችሁ።”
ግን…….. አደራ……….. ……….
አንዳትረገጡት ……. መሬቱን
እንዳታዩት……… አፈሩን፤
ብታርሱት…… አትዘሩበት
ብዘሩበት …….. አይበቅልበት፤……..
ደም ነውና – የትላንና- የዛሬ – የአሁን፣ ትኩስ…. የፈሰሰበት
አጥንት ነውና ያልደረቀ ፣ “አጸደ-ህይወት” የወደቀበት
እናንተም ከእንግዲህ ፣ ”ዐጽም – ‘ርስቴ” የማትሉት፤………..
ያውም ………………………………..
የባቶቻችሁ፣…….. የናቶቻችሁ
ያውም………………………………
የወንድሞቻችሁ፣…….. የህቶቻችሁ
ያውም……………………………………
የእቦቀቅላወቹ፣…… የታዳጊወቹ፣……..የልጆቻችሁ፤
ዓይናችሁ እያየ፣……. እየሰማ ጆሮ’ችሁ
የተመቱ! … የቆሰሉ!….. የተወጉ! …. የተፈነከቱ!…..
የተቀጠቀጡ!…. የተዘለዘሉ!……! ……የተረሸኑ!
….. በገዛ ወገኖቻችሁ………..
ያውም …………”ወገን እኮ ነን “ እያላችሁ።
በደመዋ ልባችሁ……………………………….
“ኤሉሄ …..ላማ ሰበቅተኒ!”……. ብላችሁ
ወሰን – ድንበር ለሌለው ሰቆቃችሁ
ብትነግሩትም “ለሰማይ አባታችሁ”፤
ግን….. ለምንም – ለማንም አይመችም
ሀዘናችሁ መልክ የለውም……….
ያልተነገረ እንጅ፣ ያልተፈጸመባችሁ ግፍ የለም።
ብትጎጉጡ፣ ደም አልቅሳችሁ፣….. እየየ …ብላችሁ –
ቢያዳርስም ዓለም ….. ሲቃ – ዋይታችሁ …
መቼም- መቼም ቢሆን፣ ምንጩ አይደርቅም የ’ምባችሁ::…..
እናማ………………………………………..
ሰላም፣ ፍትህ፣ እኩልነት – ሳታሰፍኑ – በመሀከላችሁ
አንድነትን ሳታነግሱ – በምድራችሁ
ይቅር ሳትባባሉ፣ ‘ርስ – በርሳችሁ
ሳይመለስ ክብራችሁ፣ ጠፈር – ድንበራችሁ
የድል ችቦው – ከፍ ሳይል ፣ ክብር ሰንደቅ ዓላማችሁ፤……
የወገናችሁን ደምና- አጥንት እንዳትረግጡት
“ይወጋችሁልና እሾኽ ሆኖ፣ የኢትዮጵያ ዐፈር – መሬት!”።

ከፊልጶስ/2010
E-mail: philiposmw@gmail.com (ፎቶ ከከቀኝ ወደ ግራ ለማ፣ ግዱ እና አብይ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: eprdf, Ethiopia, gedu, jawar, lemma, olg, Right Column - Primary Sidebar, tplf, unity

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule