50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም። የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ … [Read more...] about አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል
operation dismantle tplf
ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ
የዓለም ምግብ ፕሮግራም (ተመድ) የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተጨማሪ 85 ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸውን አስታወቀ። የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው፡- በትግራይ እና አፋር ክልሎች ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የሚሰራጨው የሰብዓዊ እርዳታ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በዚህ መሰረትም በትናንትናው ዕለት የሰብዓዊ እርዳታ የያዙ ተጨማሪ 85 የጭነት ተሽከርካሪዎች መቀሌ መድረሳቸውን ነው የገለጸው፡፡ ከዚህ ባለፈም የሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተጨማሪ 130 ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ክልል እያቀኑ መሆኑን አስታውቋል፡፡ ይህም በተያዘነው የፈረንጆቹ ዓመት ወደ መቀሌ ከተጓጓዘው የሰብዓዊ እርዳታ በመጠን ትልቁ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ በተመሳሳይ በሰሜን አፋር አካባቢዎች ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች በሚቀጥሉት ቀናት በዓለም የምግብ ፕሮግም የተዘጋጀው … [Read more...] about ሰብዓዊ እርዳታ ወደ መቀሌ መግባት መቀጠሉ ተገለጸ
እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ
በየጊዜው እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ሰለባ ላለመሆን ዜጎች ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር በበይነመረብ በሚደረጉት ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ እንዲወስዱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ጥምር ግብረ- ኃይል አሳሰበ። ግብረ-ኃይሉ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማህበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች በይዘትም ሆነ በአፈጻጸም ስልታቸው ውስብስብ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባሻገር በርካታ ግለሰቦች የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ እያደረገ ነው። የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ ሀገር የሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች መሆኑንም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡ ኢትዮጵያዊያን በስፋት የሚጠቀሟቸው ማህበራዊ … [Read more...] about እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ
የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርኃኑ ጁላ ከዑጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ የሁለቱ አገሮች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይታቸው የሁለቱ አገሮች የመከላከያ ዘርፍ ስምምነት ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ ስምምነቱን ለማደስ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ሥምምነቱን የማደስ ሥራ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲፈፀም መመሪያ ተሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሁለቱ ኃላፊዎች በዋናነት ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘገብ ስለነበረውና አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የሥልጠናና ሌሎች ድጋፎችን በአሜሪካ፣በግብጽና በደቡብ ሱዳን በመታገዝ በዑጋንዳ አማካኝነት እገዛ እያገኘ ነው የሚለውን ወሬ የዑጋንዳ መከላከያ ሚኒስትር ፈፅሞ ከዕውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሀገራቸው ኢትዮጵያን የአፍሪካ እናት … [Read more...] about የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ
በማኅበራዊ ሚዲያ የትህነግን ጉይ እየተከታተለ መረጃ የሚያጋራው አስፋው አብርሃ በትግራይ ያለውን ሁኔታ አስመልክቶ ካጋራው መረጃ ጥቂቱ እንዲህ ይነበባል፤ በትግራይ ልጁን ለወያኔ ያልሰጠ ወላጅ እየታሰረ ነው። አሁን ይኼ ውጪ አገር የሚኖር ልጅ ነው። በአንድ ወቅት "ወያኔ ቅዱስ ነው " ብሎ FB ላይ ለጥፎ ነበር። አሁን “ወላጅ እናቴ ታስራለች። በሽተኞችን ሳይቀር እየተሸከሙ ያስሯቸዋል” ይላል የባይቶናው ክብሮም በርሄ። ("ልጆቻችሁን ደብቃችኋል ፤አምጡ" እየተባሉ ነው የሚታሰሩት..) የትግራይ ወጣቶች የሚመዘኑበት መስፈርት “ታግሏል ወይስ አልታገለም” የሚል ብቻ ሆኗል። ልጁን ለወያኔው ትግል አሳልፎ ያልሰጠ የትግራይ ወላጅ ደግሞ ለእስር የሚዳረግበት ትልቅ ወንጀል ሆኗል። ይሄ ፅሑፍ ገራሚ ነው። ፅሑፉ ልጃቸውን አምጡ ተብለው ስለታሰሩ አንድ አባት የሚያትት … [Read more...] about በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ
መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ከመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ የሚሰሙ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ ከትህነግ ጋር ወደ ዳግም ጦርነት ልትገባ እንደምትችል ጠቁመዋል። ትህግም ለውጊያ እየተዘጋጀሁ ነኝ ሲል ተሰምቷል። ኤርትራ ደግሞ በሩሲያ ሠራሽ ድሮኖች ራሷን አጠናክራለች። ከተለያዩ የዜና ምንጮች ለመገንዘብ እንደሚቻለው የኢትዮጵያ መካላከያ ሠራዊት አዲስ የማጥቃት ዘመቻ ሊጀምር ይችላል እየተባለ ነው። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ኢትዮጵያ አዳዲስ ድሮኖችን ጨምሮ ተጨማሪ ተዋጊ ጀቶችን ወደ አገር ቤት በዚህ ማስገባቷ ተሰምቷል። ቱርክ ሰራሹ ባይራክ 32 ድሮን እና ተጨማሪ ጀቶች ወደ አዲስ አበባ ሳይገቡ አልቀረም። ከዚህ በፊት በተለያየ ዙር ሲሰለጥኑ የኖሩና በመጀመሪያው የክተት አዋጅ፣ የተመዘገቡ ወታደሮች እስካሁን ማስልጠኛ ካምፕ ውስጥ ቆይተው ሰሞኑን ወደ ወደ ተለያየ ክልል በተለይም ወደ አማራ ክልል ገብተዋል። … [Read more...] about መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
ትህነግ ለሌላ አውዳሚ ጦርነት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሀይል እየመለመለ መሆኑን አንድ ዓለም አቀፍ ጋዜጠኛ አጋለጠ። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን በሚገባ ተገንዝቦ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት መወጣት እንዳለበትም ገልጿል። በአሸባሪው ትህነግ ጠብ አጫሪነት በተቀሰቀሰው ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት በደረሰባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች ጉብኝት ያደረገው "የስኩፕ ኢንዲፔንደንት ዜና" ዋና ኤዲተር አላስቴየር ቶምሶን፤ የአሸባሪው ትህነግ ዋነኛ ፍላጎት ዳግም ጦርነት መቀስቀስ መሆኑን ከኢዜአ ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል። የሽብር ቡድኑ ከዚህ ቀደም በርካቶችን በጦርነት በመማገድ ለሞት መዳረጉን አስታውሶ፤ ቡድኑ አሁንም ተመሳሳይ ተግባር ለመድገም እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ነው የተናገረው። ለዚህ ደግሞ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ተዋጊዎች እየመለመለና እያሰለጠነ መሆኑን በአስረጂነት … [Read more...] about ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ
ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች
ሩስያ የክፉ ቀን ወዳጄ ላለቻት ኤርትራ ድሮኖችን በድጋፍ የሰጠችው ለቀጠናው ሰላም ኤርትራ ወሳኝ ሃገር በመሆኗ እና ሩስያ ቀጣይ በኤርትራ ከምጽዋ 40 ኪ/ሜ ርቅት ላይ በኣፍኣቤት ለምትገነባው የጦር ሰፈር እንደ መጀመርያ ግብአትነት በመቁጠር ነው። የድሮን ድጋፉ የተሰጣት ኤርትራ ለአለፉት 3 ወራት በሩስያ ስልጠና የተሰጣቸውን 26 የድሮን ባለሙያዎቿን ጭምር አቀባበል በማድረግ ዛሬ በባፃ የድሮን ጣብያ በድምቀት ተቀብላለች። በዚህ ርክክብ ወቅት የተገኙት የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአደረጉት ንግግር "ይህ ከሩስያ የተደረገልን ድጋፍ የኤርትራን የጦር ኃይል በጥራት፣ በልምድ፣ በእውቀትና በታጠቀው የጦር መሳርያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ያደርገዋል" ሲሉ ተደምጠዋል። ባለፈው ወር የኤርትራው ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኦስማን ሳሌህ ሩሲያን በጎበኙት ወቅት የሩሲያው ውጭጉዳይ … [Read more...] about ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች
በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ
በወልዲያ ከተማ ለሶስት ወራት ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ የፋኖ አባላት ተመርቀዋል በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር ዳዊት መለሰ ፋኖ ተገኝተው “የመንግሥትን ጥሪ ተቀብሎ ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሰለፍ በርካታ ውጤቶችን አምጥቷል” ሲሉ ተናግረዋል። ፋኖ ምሬ ወዳጆ በበኩሉ “የተጋረጡብነን ችግሮች ከሌሎች የፀጥታ ኃይሎች ጋር በአንድነት እንወጣዋለን” በማለት መልዕክት አስተላልፏል። (የሰሜን ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ
“ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው
ሠራዊታችን እንደ አገር ሊቃጣብን የሚችልን ማንኛውም ትንኮሳና ጥቃት በብቃት መመከት በሚያስችል የዝግጁነት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ተናገሩ። የትህነግ ቡድን ከጀሌዎቹ ጋር በማበር የከፈተውን አገር የማፍረስ እቅድ መከላከያ ሰራዊቱ በውስብስብ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ማክሸፍ መቻሉን ያስታወሱት ጀኔራል ጌታቸው ከዘመቻ በኋላ የተገኘውን አንፃራዊ ሰላም በመጠቀም ተቋሙ በሞራል፣ በሰው ሃይል፣ በብቃትና በማቴሪያል የተሟላና ግዙፍ ኃይል እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ብለዋል። ሠራዊታችን እያንዳንዷን ሰዓት በስልጠና ላይ በማዋል መቺና ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ እንዲደርስ ማድረግ ተችሏል ያሉት ጄነራል መኮንኑ አገራችንን ለመድፈር በሚያስቡ አካላት ላይ መንግስት በሚያስቀምጠው አቅጣጫ መሰረት የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ … [Read more...] about “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው