ቴዲ ወደ ባህርዳር ሲያቀና "እንዘምራለን" ማለቱን ያስተውሏል! የጉዞውን አላማ እንዲያ ሲል ነበር ረቂቅ በሆነ መንገድ የገልጸው። በመዘመር እና በመዝፈን መሃል ያለውን ጥልቅ ልዩነት የማይረዳ ብቻ ነው ለሰሞኑ "አሲዮ ቤሌማ" እጅ የሚሰጠው። ከኮንሰርቱ ጀርባ ያለው "የፍቅር ጉዞ" የሚለው መሪ ቃል ውስጥም ከውቅያኖስ የጠለቀ መልዕክት አለ። ይህንን ቃል የተረዳ ብቻ ነው የተልእኮውን ስኬት ሊያበስር የሚችለው። ዝግጅቱ ኮንሰርት እንጂ ዳንኪራ አይደለም። ሁለት ወይንም ሶስት ሰዓት ብቻ የፈጀ ኮንሰርት። ጥላቻ ሳይሆን ፍቅር የነገሰበት ኮንሰርት። ትንሳዔን አብሳሪ ኮንሰርት። መዝሙር ውስጥ መልዕክት አለ። የሚያንጽ፣ የሚያነቃቃ መልዕክት። መላው በጠፋበት በዚህ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የምትሻው የተስፋ ቃል ብቻ የሚደሰኩርላትን ሳይሆን ድልድይ የሚዘርጋላትን ሰው ነው። ጥላቻ ነግሷል። በሃገራችን ስር … [Read more...] about “ጃ ያስተሰርያል!” አራት አመታት ተከልክሎ በነበረ መድረክ?
Left Column
ወልድያ የጦር ቀጠና ሆናለች – ትንቅንቁ ቀጥሏል!
ወልድያ የበቀል ዱላ አትፎባታል። ግድያና አፈናው ለሶስተኛ ቀን ቀጥሎ ውሏል። የወያኔ ቅልብ ጦር የጅምላ ግድያውን የፈጸመው ከዚህ ቀደም በወልድያ ስታድየም የተፈጠረውን ክስተት ለመበቀል መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ። ከልምድ እንዳየነው ህወሃት ሕዝብን መጨፍጨፍ ሲፈልግ - አጋዚ ወታደሮቹን ሕዝብ በሚሰበሰብበት ስፍራ ያሰማራና በመተንኮስ እንዲነሳሱ ያደርጋል። ብሶቱ ከቅጥ ያለፈበት ሕዝብ ድምጹን ማሰማት ሲጀምር ህወሃት የበቀል ስራውን ይሰራል። ከዓመት በፊት የእሬቻ በዓል ላይ የሆነው ይኸው ነበር። በወልድያው ጭፍጨፋም ያየነው ይህንኑ ነው። የቴዲ አፍሮ የባህርዳር ኮንሰርት ላይ አጋዚ ቢኖር ኖሮ እልቂቱ አይቀሬ ነበር። የዘንድሮው እሬቻ በዓል ከአጋዚ ነጻ ቢሆን እንደ አምናው ወገን ይገደል ነበር። እለተ ቅዳሜ፣ ጥር 12 ቀን 2010 ዓ.ም. የጥምቀት በዓልን ለማክበር የታደመ ሕዝብ … [Read more...] about ወልድያ የጦር ቀጠና ሆናለች – ትንቅንቁ ቀጥሏል!
“መንግሥት ሲኖረኝ ቀስቅሱኝ”
በዚህች ምድር ላይ የቆየው ለ40 ዓመታት ብቻ ነው፤ ከ1970 ዓ/ም እስከ ታህሳስ 2010 ዓ/ም። ተስፋዋና ፍሬዋ ለልጆቿ እንደ መንግሥተ ሠማያት መንፈስ ብቻ በሆነው ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ በመከረኛዋና ታሪካዊዋ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ - ጨርቆስ - ተወልዶ አደገ። ብሩህ አእምሮን የተቸረ በዕውቀት ቀሳሚነቱ የናረና ከሁሉም በላይ ግን ሀገራዊና ወገናዊ ሰብዕናን ከስነ ምግባር ጋር ያዋሃደ የኢትዮጵያ ልጅ ኢትዮጵያዊ ሆነ። ስለ ሀገሩና ስለህዝቧም ሲል በናዚስት የዘረኝነት አስተምህሮ ካበዱት ከግፍ ጠማቂዎቹ ናዚስት ወያኔ ገዢዎች የሀገሩን የፍዳ ገፈት ተግቶና ከሀገሩ ተገፍቶ በሰው ሀገር በስደት ተንከራትቶ አለፈ። እሱም ጋዜጠኛና የሰብዐዊ መብት ተሟጋቹ ኢብራሂም ሻፊ ይባላል። ግፈኞቹና በግፍ ዘመነ ሥራ ዕድሜ የጠገቡት ሀገሩን ኢትዮጵያን ሲቆጣጠሩ በ1983 ዓ/ም እሱ ገና አስራዎቹን … [Read more...] about “መንግሥት ሲኖረኝ ቀስቅሱኝ”
የኢትዮጵያ የሽግግር ጊዜ መተዳደሪያ ደንብ!
መግቢያውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ የዐኅኢአድ የሽግግር ጊዜ ሰነድ ረቂቅ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው። … [Read more...] about የኢትዮጵያ የሽግግር ጊዜ መተዳደሪያ ደንብ!
ገና (ልደት) እና Hockey
ባለፈው ሳምንት ስለ ልደት በዓል በቤተ ክርስቲያናችን አውደ ምህረት ላይ የቀረበውን በቪዲዮ የተመለከቱ ወገኖች፤ “ኢትዮጵያ በወያኔ እጅ ከመውደቋ በፊት ከጌታችን ልደት በዐል ጋራ ተያይዞ ህዝቡ ገና በሚል ስም የሚጫወተው ጨዋታ ነበረው። ሊቃውንቱ ስለገናው ጭዋታ የሚሉት ነገር ካለ አካፍለን” ብለው ጠይቀዋል። ራሴ እየተጫወትኩት፤ በቅኔውና ባብነቱ ትምህርት እየተማርኩትና እየሰማሁት ያደኩበት ስለሆነ በወያኔ ዘመን ተወልደው ስለ ገናው አመታዊ ጨዋታ ምንም ለማያውቁት ባህላቸውንና ወኔያቸውን ለተዘረፉትና ለጠየቁኝ ኢትዮጵያውያን ከሞላ ጎደል አቅሜ የፈቀደልኝን ለማቅረብ እሞክራለሁ። ከክርስቶስ ልደት ጋራ ተሳስሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገር ከዳር እስከዳር ህዝብ ሲያንቀሳቅ (ሲያቆራቁስ) የነበረ የገናን ጨዋታ የመሰለ ህዝባዊ ነገር ይቅርና፤ ባንዲት መንደር የምትታይ ትንሽ ጥንታዊት … [Read more...] about ገና (ልደት) እና Hockey
ኢትዮጵያን እንቀኝ
ርዕዮት ሚድያ እሁድ January 28, 2018 የኢንተርኔት ስርጭቱን የጀመረበትን አንደኛ ዓመት ክብረ-በዓል “ኢትዮጵያን እንቀኝ” በሚል መሪ ቃል በታላቅ ድምቀት እንደሚያከብር ሲገልጽ ደስታ ይሰማዋል፡፡ ዝግጅቱ በእለቱ ከ4 PM ጀምሮ 7701 16th Street, NW Washington, DC 20012 በሚገኘው Tifereth Israel አዳራሽ በርካታ ታዳሚዎችና የክብር እንግዶች በተገኙበት ይመደረካል፡፡ ርዕዮት ሚድያ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነትን የመኖር ምክንያትና ዋና መርህ ያደረገ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን የሚመለከቱ ማናቸውንም ጉዳዮች በልዩ ልዩ የአቀራረብ ስልቶች የሚዳስስ ሚድያ ነው፡፡ ግባችንም ለኢትዮጵያና ለዜጎቿ መሻል አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የዜና፣ የትንተናና የመዝናኛ ፕሮግራሞችን አሰናድቶ በበርካታ መንገዶች ኢትዮጵያውያን ዘንድ በያሉበት መድረስና የኢትዮጵያዊ … [Read more...] about ኢትዮጵያን እንቀኝ
ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወድያ
ሰሞኑን አየሩን የሞላው “የበላይነት” የሚለውን ጽንሰሃሳብ በመለጠጥና በማጥበብ ዙርያ ሆኗል። የህወሃት የበላይነት፣ የትግራይ የበላይነት፣ የትግራይ ህዝብ የበላይነት በሚሉ ብዙም በማይራራቁ ጽንሰ ሃሳቦች ዙርያ ከዝንብ መላላጫ የማውጣት ያህል ከየአቅጣጫው እየተሰነዘሩ ነው። እነዚህ እሰጥ አገባዎች አብዛኛውን ጊዜ ስሜታዊነትና ጥላቻም ተቀላቀሎባቸው ሶሻል ሚድያውን፣ የርስ በርስ ውይይቱንና መገናኛ አውታሮችን ያጣበቡ ሲሆን በጣም ጥቂቶች በአጋጣሚው የጠለቀ ትንተና በመስጠት በነገሮች ላይ ያለንን እይታ እንዳሰፉት እሙን ነው። ወያኔም ህብረተሰቡ በዚህ ስሜታዊ እንካስላንትያ ሲጠመድ ሊያገኝ የሚችለውን እፎይታና የተቃውሞው ጎራ መከፋፈል ሊያተርፍበት ሲንደፋደፍ ይታያል። ለእኔ ደግሞ “የበላይነት” አለ፣ የለም የሚለው ጉንጭ አልፋ ውይይት ላይ ጊዜና ጉልበታችን ሲጠፋ አግባብ ሆኖ አይታየኝም። … [Read more...] about ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወድያ
ስለ ለማ መገርሣ ጥቂት ምልከታዎች
ማሳሰቢያ፤ ከዚህ በታች የሰፈሩት ጽሁፎች በቀጥታ ከተለያዩ ጸሐፍት (በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ከሚሳተፉ) የተወሰዱ አስተያየቶችና ምልከታዎች ናቸው እንጂ የጎልጉል አቋም አይደሉም። ዮሐንስ ሞላ እንዲህ ይላል፤ አቶ ለማ መገርሳ የመንግስት ባለስልጣን ሆኖ በቆየበት ጊዜ ሁሉ ሲያስገድል፣ በሀሰት ሲያስወነጅል፣ ሕዝብን ከሕዝብ ሲያባላ እና በድህነት እንድንሰቃይ ለሙስና ሲያጋፍር ነው የኖረው። ሌላውን የኢህአዴግ ባለስልጣን አስኮንኖ፣ አቶ ለማ እና ዶ/ር ዐብይን ነጻ የሚያስወጣ ምንም ዓይነት ምክንያት የለንም። ማሽሞንሞን ሳያስፈልግ፥ አቶ ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ሽንት ጨርቅ ነው። የአምባገነን ስርዓት ሽንት እንዳይታይ በማድረግ ረገድ የሚጫወተው የዳይፐርነት ሚና ከደረሱብን ጉዳቶችም የሚልቅ እና፣ ለዚህ ግብሩ መጨፈር እና መቀኘታችን ወደፊት ብዙ የሞራል ዋጋ የሚያስከፍለን … [Read more...] about ስለ ለማ መገርሣ ጥቂት ምልከታዎች
Abebe Kassie, a Brave Ethiopian and a Victim of a TPLF Terror House
(Note: Ethiopia is a current member of Human Rights Council of the United Nations) Below is a translation based on a letter obtained from one brave Ethiopian among many victims who have fallen into the hands of the terrorist regime of the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) currently ruling Ethiopia. My name is Abebe Kassie, I am a forty-one-year-old from Armachoho Woereda in Northern Gonder. I am currently in Kilinto prison in the Akaki area. I was imprisoned by the TPLF on the 20th of … [Read more...] about Abebe Kassie, a Brave Ethiopian and a Victim of a TPLF Terror House
ዳግም ተገናኘን!
... “ያሰብኩት ተሳካ ያለምኩት ደረሰ፣ ሃሳቤም ተሟላ መንፈሴም ታደሰ፤...” ለዛሬዋ ጽሁፌ መግቢያነት የመረጥኳት ግጥም፣ በእውቁ ድምጻዊ በጥላሁን ገሠሠ ከተቀነቀኑት አያሌ የማኅበራዊ ዘርፍ ዘፈኖች አንዱ የሆነው ዘፈን አዝማች ናት(በሃሳባችሁ ዜማውን እያስታወሳችሁ ተከተሉኝ፤ በተለይ ከአጃቢ የሙዚቃ መሳሪያዎች መካከል ጎልታ የምትሰማዋን፣ የአየለ ማሞን የማንዶሊን ዜማ እያዳመጣችሁ)። ... ከዛሬ አንድ ዓመት በፊት “አማኒ ኢብራሂም — ’ያልታወቀው‘የጥበብ ሰው” በሚል ርዕስ አንድ መጣጥፍ ቢጤ በኢትዮጵያውያኑ ድረ-ገጾች (በኢትዮ-ሚድያ፣ በኢኤምኤፍ፣ በቋጠሮ፣ በጎልጉል...) ላይ ለንባብ አብቅቼ ነበር። ጽሑፉ እንደወጣ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ፣ ከሰላሣ ዓመታት በላይ የትና እንዴት እንዳለ ያላወኩትን፣ በሙዚቃ ሙያ በእጅጉ የተካነውን፣ ሁሌም ብዙዎች በአርዓያነት የሚጠቅሱትንና … [Read more...] about ዳግም ተገናኘን!










