• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገና (ልደት) እና Hockey

January 17, 2018 05:52 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው ሳምንት ስለ ልደት በዓል በቤተ ክርስቲያናችን አውደ ምህረት ላይ የቀረበውን በቪዲዮ የተመለከቱ ወገኖች፤ “ኢትዮጵያ በወያኔ እጅ ከመውደቋ በፊት  ከጌታችን ልደት በዐል ጋራ ተያይዞ ህዝቡ ገና በሚል ስም የሚጫወተው ጨዋታ ነበረው። ሊቃውንቱ ስለገናው ጭዋታ የሚሉት ነገር ካለ አካፍለን” ብለው  ጠይቀዋል። ራሴ እየተጫወትኩት፤ በቅኔውና ባብነቱ ትምህርት እየተማርኩትና እየሰማሁት ያደኩበት ስለሆነ በወያኔ ዘመን ተወልደው ስለ ገናው አመታዊ ጨዋታ ምንም ለማያውቁት ባህላቸውንና ወኔያቸውን ለተዘረፉትና ለጠየቁኝ ኢትዮጵያውያን ከሞላ ጎደል አቅሜ የፈቀደልኝን  ለማቅረብ እሞክራለሁ።

ከክርስቶስ ልደት ጋራ ተሳስሮ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገር ከዳር እስከዳር ህዝብ ሲያንቀሳቅ (ሲያቆራቁስ) የነበረ የገናን ጨዋታ የመሰለ ህዝባዊ ነገር ይቅርና፤ ባንዲት መንደር የምትታይ ትንሽ ጥንታዊት ነገር፤ ያለ ምንም መነሻ የመጣች አይደለችም። ከኛ በፊት የነበሩት ሊቃውንት አባቶቻችን  ይህንን ተገንዝበው  እያንዳንዷን ጥንታዊት ነገር በጥንቃቄ እያጠኑ፤ ለሀገር ግንባታ ለህዝብ አንድነት እንዲጠቀም አርገው በመስራት ከትውልድ ወደ ትውልድ እያሻገሩ ኢትዮጵያን በመጠበቅ እስከወያኔ ዘመን አድርሰዋታል።

በወያኔ ዘመን ግን በጥራዝ ነጠቅነት፤ በራስ ክብር ወዳድነት፤ በጥቅምና በባዶ ጭንቅላት እየተገፉ በድፍረት በመቅለብለብ የሚገሰግሱ ሰዎች በየጎራው በየደብሩ ተሰልፈው  ሊቃውንቱን እየደመሰሱ ራሳቸውን ሰየሙ። እነዚህ የተሰየሙት ሰርጎ  ገቦች የአገር ጠላትና የማርያም ጠላት እያደረጉ በሊቃውንቱና በተሰሩት ጠቃሚ ቅርሶች ላይ ዘመቱ። ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ስለጥንቱ ትምህርትና ታሪክ የሚናገሩትንና የሚመሰክሩትን ሁሉ እንዲታፈኑ እንዳይሰሙ ጭራሽ እንዲጠፉ ዘመቱባቸው። የገናው ጨዋታም ከሚመሰክሩለት ሊቃውንት ጋራ አብሮ የተዘመተበት እና ከኢትዮጵያ አካላዊ ቅርጿና ለዛዋ ጋራ የፈረሰና የተመታ ይመስለኛል።

ገና የምንለው ጨዋታችን hockey ከሚባለው ከበፈረንጆች ጨዋታ ጋራ ይመሳሰላል። በፈረንጁ ዓለም ጨዋታው ከእስፖርት ክፍል እንዳንዱ ሆኖ እንደሚታወቅና በክብር ተጠብቆ ለትውልድ በመተላለፍ ላይ እንደሆነ ከኔ የበለጠ ሁሉም በማጥፋት ላይ ያሉት ወያኔወች ሳይቀሩ ያውቁታል።

hockey የሚባለው የፈረንጆች ጨዋታ ball  & crooked ከሚባሉት መሳሪያወቻቸው፤  እኛ ገና የምንለው ጠማማ ብትርና ጥንግ ከምንላት ጋራ ይመሳሰላሉ። ፈረንጆች hockey ለሚሉት ጨዋታቸውና  ball & crooked ለሚሏቸው መሳሪያወች ምን ትርጉም እንደሚሰጧቸውና፤ ጨዋታውንም እንዴት እንደጀመሩት አላውቅም። ፈረንጆች ከኛ ይውሰዱት እኛ ከፈረንጆች እንገልብጠው አላውቅም።

ያም ሆነ ይህ የገናው ጨዋታ ረዥም ዘመን ስለቆጠረና ወደቅርስነትም ስለተሻገረ በሁለት መንገዶች፦ ማለትም በcultural anthropology  እና በcultural theology ሊጠና ሊተረጎም የሚችል ይመስለኛል። ከcultural theology ጋራ ያገናኘሁበት ምክንያት ከጌታችን ልደት ጋራ ተሳስሮ የመንፈሳዊ ባህል ገጽ በመያዙ ነው።

በአገራችን በዓሉ እጅግ ገኖ የሚታወቀው ልደት ከሚለው ይልቅ ገና በሚለው ነው። በዓሉን ለመቀበል የሚደረገው ዝግጅት ጾም ነው። ከጾሙ ጎን ሌላው ትልቁ ዝግጅት የገናው ጭዋታ ነው። ጨዋታውን እኔም ባደኩባት መስክ ተሳትፌዋለሁ።

ጨዋታውን ሊቃውንት አበው የህብረተ ሰብን ስነባህርይ እንዲገልጽ አርገው ከህዝብ ስነ ልቡና ጋራ አዋህደውታል። ህብረተ ሰባዊ ለዛና ስነ ልቡና የያዘውን የገናን ጨዋታ እንደቅርስ ጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግ ሲገባ፤ ባጭር ዘመን እስከመረሳት ደርሶ እንዴትና ለምን ነበር?ንገሩን በሚል ጥያቄ መቅረቡ እጅግ የሚያሳዝን ነው።

ፈረንጆቹ  ሥጋዊ አካላቸውን ለሚጠብቀው ለስፖርት ብቻ ሲሉ  ለጨዋታው hockey የሚል ስም ሰጥተው ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ሲያደርጉ፤ የኛ አባቶች ለሰውነት ብቻ ሳይሆን፤ የሰሩትን፤  “ሃይማኖትየኒ ዐቀብኩ” (1ኛ ጢሞ 4፡7᎗8)ሲል ቅዱስ ጳውሎስ ባሳየው መንገድ፤ ለዘላቂው ስነ ባህርይ እጅግ  እንዲጠቅም አርገው የሰሩልን፤ እምነቴን ሞራሌንና ጠቅላላ ስነ ባህርየን ጠበኩት እያልን እንድንኮራበት ነበር። ወያኔወች ይህንን በማፍረሳቸው  ጭራሽም እንዲዘነጋ በማድረጋቸው በትውልድ በሀገር ላይ ጥፋት ፈጸሙ እየተባሉ ከሚከሰሱት ከወራሪዎች ከጣሊያኖች የባሱ እጅግ የከፉ ናቸው ብንል በሽተኛ ካልሆነ በቀር ጤነኛ የሆነ ሰው ውሸት ነው ሊል የሚችል አይመስለኝም።

እነ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ ወራሪውን ጠላት ተፋልመው ካስለቀቁ በኋላ  “ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት” እያሉ የመከሩን ከምዕራቡ የምንቀበለውን ትምህርት የራሳችንን የበለጠ እንድንረዳበትና ለበለጠ እድገት እንድንጠቀምበት እንጅ፤ እርስ በርሳችን እየተመቀኛኝን ለመጠፋፋት በምናደርገው በቂምና በበቀል የገና ጨዋታውን የመሳሰሉትን በየትም የማይገኘውን ቅርሶች ነቃቅለን ጥለን ኢትዮጵያን እዚህ ለማድረስ አልነበረም።

እነ መላከ ብርሀን አድማሱ “ወጣት ተመልከት እንዳትሳሳት” እያሉ የመከሩንን ከመስማት ይልቅ በባእድ ተንኮለኞች ትምህርት በተወረረና በተመረዘ  ጭንቅላት የሰከሩ አንዳንድ ተወላጆች ለህዝብ መጎዳት እንቆረቆራለን እያሉ በሚያስመስልና የህዝብ ልብ በሚሰርቅ ንግግራቸው ህዝቡን እያታለሉ ፈጣሪ ይቅር የማይለውና ተፈጥሮ የማይረሳው በደል በህዝባችንና በአገራችን ፈጽመዋል። አሁንም እየፈጸሙ ናቸው። ከጎንደር ከጎጃም ከወሎ ለመላው ህዝብ የቀረበውን ህዝባዊ ጥሪና ከኦሮሞው ከውራጌውና ከወላይታው ከጋምቤላው  የተመለሰውን ህዝባዊና ብሔራዊ ተሰጥኦ ለመቀበል አቅመ ቢስ የሆኑ ለመስማት የደነቆሩ ተማርን የሚሉ ጅሎች አሁንም ሲጃጃሉ ይታያሉ። ህዝቡ እንደነቃባቸውና እንደታዘባቸው የማይረዱ እርቃናቸውን መቆማቸውን የማይገነዘቡ ግብዞች ናቸው።

በተለይ፦የኢትዮጵያን አካላዊ ቅርጿን ያሳጣ ድንበሯን የቆረሰ ህዝቧን በቋንቌ ከፋፍሎ በጠላትነት እያሰለፈ በማፋጀት ላይ ያለው ወያኔ፦ “የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጭ ግንባር በ1979 አመተ ምህረት አስተሳሰብ ለዋጭ የፕሮፓጋንዳ መርሀ ግብር ለሚመለምላቸው ቀሳውስት ዘረጋ። የማሰልጠኑ ዓላማ ቤተ ክርስቲያኗን ከህዝብ ለይቶ በመምታት ስፋቷን ማጥበብና በትግሬአዊነት ላይ ብቻ የተመሰረተ ስሜት በትግራይ ተወላጆች ጭንቅላት መክተት ነው። ቤተ ክርስቲያኗ ለረዥም ዘመናት በህዝቡ አዕምሮ ላይ ስትተቀርጸው የኖረችውን ብሄራዊ የኢትዮጵያነትን ስሜት ከትግራይ ህዝብ አዕምሮ ጠራርጎ በጠባቡ ትግሬአዊነት ስሜት በመተካት የቤተ ክርስቲያኒቱን ይዘት እያጠበቡ ራሷን ቤተ ክርስቲያኒቱን መምታት ነው” ብሎ  በቀየሰው የጥፋት መርሆ ለ27 ዓመታት እስከ ዚች ደቂቃ ድረስ ሲያፈርስ የኖረው የገናን ጨዋታ የመሳሰሉትንና ሌሎችን ኢትዮጵያ ነክ የሆኑትን ለአገር ለህዝብ ቤዛ የሆኑትን ሁሉ ቅርሶች እያደነ ማጥፋቱ፤ ወያኔ አገሪ አጥፊ እንደሆነ በግልጽ የሚያስረዳ ነው። በገና ጨዋታችን ያለው ጽንሰ ሀሳብ ወያኔ ካጠፋቸው ቅርሶች ጋራ በሙሉ ተካተው በተረጋጋ ጊዜ በጽሁፍ ተዛጋጅቶ ለትውልድ እንደሚቀርብ ተስፋ አደርጋለሁ።

ቃል ኳሄላ የመከነ ነባር ቃል ነው፤ የሚወልድ ግስ አይደለም ከየት ሰርጎ እንደገባ አላውቅም። ጥንግ የምትለው ግን፦“ያመነድቡኒ ወያጸነግ(ጵ)ውኒ አዕጽምትየ” (መዝ 41፡9) ።  ከሚለው ሀረግ እንደተወሰደች ይናገራሉ። ሙሉ አረፍተ ነገሩ፦ “ለምንት ተሀድገኒ ወለምንት ትኩዝየ አንሶሱ፤  ሶበ ያመነድቡኒ ወያጸነጵኡኒ (ያጸነግኡኒ) አእጽምትየ  ጸላእትየ” (መዝ 41፡9)። የሚለው ነው። ይህም ማለት፦ ይቃለቡኛል፤ ከለብ ወደለብ ይለጉኛል፤ ያጠነጉኛል ”

ጥንግ የምትባለው ቃል ከዚህ ሀረግ እንደተወሰደች  ያብነቱ መምህራን አበው ይናገራሉ። ታዲያ ጥንግ ማለት  እየተለጋች እየተጠነጋች ከለብ ወደለብ“ትኩዝየ አንሶሱ” የሚቃለቧት ማለት ነው።  በባንቱ ጎል ሲባል ሰምቼ አላውቅም። ጎል የሚባለውን ቃል የሰማሁት አዲስ አበባ ነው። ያም ሆነ ይህ በቁርቁስ ተጀምሮ በሆታ የሚያልቀው የገናው ጫወታ፤ የሚካተቱት  መሳሪወችና የተጫዋቾች ባህርያት በቅኔው፤  በምስጢራተ መጻህፍትና በማህበራዊ ግንዛቤ ትኩረት የላቁ አባቶቻችን የሚገልጹበት መንገድ Ethiopic  (cultural)theology ተብሎ ሊገለጽ የሚችል ይመስለኛል” በማለት በከንሳስ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን አውደ ምህረት ላይ የቀረበውን  ትምህርት እንድትከታተሉት ከዚህ በታች ቪዲዮውን አቀረብንላችሁ።

በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ nigatuasteraye@gmail.com

ታህሳስ ሁለት ሽ አስር ዓ.ም.


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: ethiopian christmas, genna, hockey, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule