የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ወንበዴው ህወሃት/ትህነግ አገር ለማፍረስ ዓላማ ሲጠቀምባቸው የነበሩት 34 የፋይናንስ ተቋቱን ማገዱን ይፋ አድርጓል። እንደ ኢቲቪ ዘገባ ከታገዱት የበረኻ ወንበዴዎቹ ድርጅቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፤ ሜጋ ማተሚያ፣ ሱር ኮንስትራክሽን፣ ጉና የንግድ ሥራዎች፣ ኢፈርት ኤሌክትሪካል ቢዝነስ፣ ትራንስ ኢትዮጵያ፣ መስፍን ኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ፣ ሠላም የህዝብ ማመላለሻ ማህበር፣ ኢፈርት ኃ/የተ/የግ ማህበር እገዳው ከተላለፈባቸው መካከል ናቸው። ጎልጉልን ጨምሮ የተለያዩ የሚዲያ አውታሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ወዘተ ለትህነግ የፋይናንስ ምንጭ የሆነው ኤፈርት ወደ ሕዝብ ሃብትነት እንዲመለስ ሲወተውቱ መቆየታቸው ይታወሳል። ስብሃት ነጋና ቤተሰቡ የተቆጣጠረው ኤፈርት ግብር … [Read more...] about 34 የወንበዴው ትህነግ የፋይናንስ ተቋማት ታገዱ
Left Column
ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!
በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበሩ ያላቸውን የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ መወሰኑን ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎቹ በቀጠሯቸው የጥበቃ አባላትና ተባባሪዎቻቸው ባንኮችንና የተለያዩ ድርጅቶችን ሲዘርፉ እና ሲያዘርፉ ነበርም ብሏል። በተጨማሪም 'የህወሓትን ተልዕኮ ለመፈፀም የተለያዩ ግለሰቦችን ወደ ኤጀንሲዎቹ አስርገው በማስገባት እና የጦር መሣሪያ በማስታጠቅ በኅብረተሰቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ ጥቃት ለመፈፀም እያሴሩ ነበር' ሲል አስታውቋል። በዚህም:- 1. ንስር የሰው ሃይል እና የጥበቃ አገ/ሃ/የተ/የግ/ማ 2. አጋር የጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 3. ስብኃቱና ልጆቹ የንብረት አስ/ጥበቃ አገልግሎት ኃ/የተ/የግ/ማ 4. ሰላም ሴኩሪቲ ሶሉሽን ኃ/የተ/የግ/ማ 5. ኃይሌ ተክላይ … [Read more...] about ህወሃትን ያገለግሉ የነበሩ የግል ጥበቃ ኤጀንሲዎች እንዲታገዱ ተወሰነ!
በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው
የአገር ክህደት ወንጀል በፈፀሙ የጁንታው ሕወሓት ቡድን ላይ የፍርድ ቤት የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የጥፋት ቡድኑ አባላት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች ፀረ-ሰላም ሃይሎች ጋር በመቀናጀትም ከተለያዩ ክልሎች አገርን የማፍረስ ተልዕኮ ያላቸውን ኃይሎች በመመልመል ትግራይ ክልል ድረስ በመውሰድ ለእኩይ ተልዕኮቸው ስኬት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፎችን በማድረግ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች ብሄርን ከብሄር በማጋጨት እና በሃይማኖት ሽፋን ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር በማድረግ በርካታ ንፅሁን ዜጎች እንዲገደሉ፣ በአካልና በንብረት ላይም ከባድ ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸውን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡ እነዚህ የሀገር ህልውናን አደጋ ላይ በመጣል እንዲሁም ህገ-መንግስቱንና … [Read more...] about በ96 የህወሃት ወንበዴዎች ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ ወጣባቸው
የሶስቱ ቀናት ፈታኝ ተጋድሎ በብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንደበት
ዳንሻ ከተማ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር ካምፕ ጊቢ ውስጥ የመከላከያ መኪናዎች በጥይት ተበሳስተው ይታያሉ። መስታወታቸው ረግፏል፤ ዛፎቹም የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል፤ መጥረቢያ እንጂ የጥይት ውርጅብኝ የቆረጣቸው አይመስሉም። የግንብና ቆርቆሮ ቤቶች እንደ ወንፊት ተበሳስተዋል። የጥይቶች ቀላሃ እንደ ጠጠር ተብትኗል። ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2013ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በዳንሻ ከተማ ያልተጠበቀ፣ አሳዛኝ፣ አስደጋጭ ድርጊት ነው የተፈጸመው። በከተማዋ የሚገኘው የሰሜን ዕዝ የአምስተኛ መካናይዝድ ክፍለ ጦር የተደገሰለትን ጥቃት አያውቅም። በመካናይዝድ ክፍለ ጦሩ ስታፍ ውስጥ የሚሰሩት መደበኛ ስራቸውን ከውነው እንቅልፍ ላይ ናቸው። በዚህ ምሽት ግን የትግራይ ልዩ ኃይል አባላት ወደ ካምፑ ዘለቁ፤ ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አድማሱን … [Read more...] about የሶስቱ ቀናት ፈታኝ ተጋድሎ በብርጋዴር ጀኔራል ሙሉዓለም አንደበት
ጠ/ሚ/ር ዐቢይ የህወሃት ወንበዴዎችን የሽምግልና ልመና ውቅድ አደረጉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) የቀረበውን የሽምግልና ጥሪ ሳይቀበሉ ቀሩ። የቀጣናዊው ተቋም መሪ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በ4 የተለያዩ ጊዜያት ስልክ በመደወል የኢትዮጵያ አቻቸውን ለማግባባት ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል። ሱዳን ትሪቢውን የሃምዶክን ቢሮ አጣቅሶ የዘገበውን ሂቃያት ጋዜጣን ዋቢ አድርጎ በድረ ገጹ እንዳሰፈረው ዘገባ ከሆነ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጉዳዩ ዓለም አቀፋዊ መልክ ሊይዝ የማይገባው የሃገር ውስጥ ጉዳይ ነው ብለዋል። ሃምዶክ ባለፈው ዓመት የኢጋድ ሊቀመንበር ሆነው ዐቢይ አህመድን መተካታቸው ይታወሳል። “የህወሀት ጁንታ ቡድን ትላንት የቀረቡለትን የድርድር እና የውይይት ዕድሎች ሁሉ አምክኖ ግብአተ መሬቱ ሊፈጸም ሲቃረብ የአደራዳሪ ያለ ብሎ መጮህ ጀምሯል” ሲል መግለጫ ያወጣው … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር ዐቢይ የህወሃት ወንበዴዎችን የሽምግልና ልመና ውቅድ አደረጉ
መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ
ባለፉት 29ዓመታት ከተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆነ ከሲቪክና ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተሰምቶ በማያውቅ በሚያስብል ቁመና እና ክብደት፤ ወደፊት በታሪክ በሚጠቀስ መልኩ የዜጎችን የተግባር ድጋፍ የሚጠይቅ መግለጫ ከመንግሥት ተሰምቷል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንዲህ ይነበባል፤ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከመንግሥት የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝቦች ከሁለት ዓመታት በፊት ግንባራቸውን ለጥይት፣ ደረታቸውን ለጦር ሰጥተው አደባባይ የወጡት የይስሙላ ፌዴራሊዝም ወገባቸውን አጉብጦት፣ ተስፋቸውን አጨልሞት ነው። ጥቂቶች ዜጎችን እያፈኑና እነርሱ እየከበሩ መምጣታቸው ቁጣቸውን አገዘፈው። ኢትዮጵያዊያን አገራቸው ሆና ለማየት ከሚያልሙት እጅግ እየራቀ መምጣት የቁጣቸውን ኃይል አገዘፈው። እውነተኛ የፌዴራል ስርዓትን ለመተግበር ጉዞ ከመጀመሩ በፊት ዜጎች በጋራ የሚሳተፉበትና ተጠቃሚ የሚሆኑበት … [Read more...] about መንግሥት ከዜጎች የተግባር ድጋፍ ጠየቀ
መቀሌ በዛሬው ዕለት ሰላም ውላለች፤ የትግራይ ልዩ ኃይል እየከዳ ነው ተባለ
የዛሬውን የመቀሌ ውሎ አስመልክቶ ግርማይ ገብሩ እንደዘገበው በከተማዋ ያለው እንቅስቃሴ ሰላማዊ እንደሆነ የጠቀሰ ሲሆን ባንኮች፣ መስሪያ ቤቶች እና ቴሌ ግን ዝግ ሆነው ነው የዋሉት። በሌላ በኩል አሸባሪው የበረኻ ወንበዴዎች ስብስብ የሆነው ህወሃት ሲመካበት የነበረው ነፍጥ ታጣቂ በሺህ የሚቆጠር እየሆነ ከነመሣሪያው እጁን በመስጠት ላይ ይገኛል። Eritrean Press በፌስቡክ ገጹ እንደዘገበው በርካታ ሺህ የሚሆኑ ልዩ ታጣቂዎች በጎንደር በኩል እጃቸውን እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጿል። የነዋሪዎች መደበኛ ህይወት እንደወትሮው ሁሉ ሰላም ነው። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about መቀሌ በዛሬው ዕለት ሰላም ውላለች፤ የትግራይ ልዩ ኃይል እየከዳ ነው ተባለ
ህወሓትና ተላላኪዎቹ በአሸባሪነት እንዲሰየሙ ተጠየቀ
ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት/ትህነግ) በማለት የሚጠራውና በኢትዮጵያ እጅግ አስከፊ የሚባልና ትውልድን ያወደመ ርዕዮት በመከተል አገር ያፈረሰው የወንበዴዎች ጥርቅም፤ እስካሁንም በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት በአሸባሪነት ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል። አባላቱና ደጋፊዎችም በዚሁ ሁኔታ የሚታዩ መሆናቸውን ብዙዎች የሚስማሙበት ነው። ለአብነት ያህል፤ በአዲስ አበባ በሚኒባስ የፈነዳ ቦምብ በኦነግና በኤርትራ ላይ የተሳበበ መሆኑን የሚያስታውሱ ወገኖች ህወሓት ያኔ የፈጸመውን የአሸባሪነት ተግባር ላሁኑ እንደ ግብዓት ያነሳሉ። ሆኖም ቆየት ብሎ የታተመው የዊኪሊክስ (ሹልክ ዓምድ) ዘገባ ፍንዳታውን አቀነባብሮ ያከናወነው ህወሓት ስለመሆኑ እዚህ ላይ በዝርዝር አስረድቷል። ከበረሃ ጀምሮ ማሸበር ሙያው የሆነው ህወሓት ሥልጣን ይዞም ይህንኑ በደም የተነከረ … [Read more...] about ህወሓትና ተላላኪዎቹ በአሸባሪነት እንዲሰየሙ ተጠየቀ
የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት
ቒጫ የጉራግኛ ቃል ሲሆን ጥሬ ትርጉሙም ደንብ፣ ስርዓት፣ ህግ ማለት ነው፡፡ የጉራጌ ህዝብ ባህላዊ ስርዓት ህግ ራሱን በራሱ መገልገል የጀመረው በስሙ እየተጠራ ባለበት ሀገር ከሰፈረበት ዘመን ጀምሮ እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ህብረተሰቡ በየክፍሉ የሸንጎ ማእከላት በክፍለ ህዘብ ምድብ ባለበት ሁሉ የስሙ አሰያየሙ ይለያያል፡፡ መደበኛ ህግ ክፍሎች አሉት፡፡ የፍትሃብሄር፣ ወንጀለኛና የቤተሰብ (የጋብቻ) ስነስርዓት (ህግጋት) በውስጡ ይዟል፡፡ ይኽውም፡- የአንቂት ቒጫ - ይህ ደንብ በአጠቃላይ የጋብቻና የፍቺ ስነስርዓት የተደነገገበት ሲሆን የአተጫጨት፣ የቸግ ወይም የኒካ የሰርግ እና ፍቺ አፈጻጸም የሚዳኝበት ስርዓት (ደንብ) ነው፡፡የቅየ ቒጫ - ይህ ደንብ በሁለት ወሰንተኞች መካከል የድንበር መገፋፋት እንዳይኖር በሁለት ወገኞች ስምምነት በሚመረጡ ሽማግሌዎች አማካይነት … [Read more...] about የጆካ ዳኞች ባህላዊ የዳኝነት ሥነ-ሥርዓት
ኦሮሚያን አቋርጠው የሚያልፉ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፈተና
ከቅርብ ወራት ወዲህ ከአማራ ክልል በደጀን መስመር ወደ አዲስ አባባ የሚሄዱና የሚመለሱ ከባድ የደረቅ የጭነት ተሸከርካሪ አሽከርካሪዎች በተለይ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከጎሐጽዮን ደብረጉራቻ ባለው መስመር ማለፍ ፈተና ሆኖባቸዋል። አስተያየታቸውን ከሰጡት አሽከርካሪዎች መካከል አንዱ ”ከፍቼ ከተማ የቅርብ ርቀት ከምትገኝ ‘አሊ ዶሮ’ ከተባለች ቦታ ላይ መስከረም 30/2013 ዓ. ም የክልሉን የፀጥታ ኃይሎች የደንብ ልብስ የለበሱ ታጣቂዎች ተኩስ ከፍተው የቆሰሉና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አሽከርካሪዎችና ከ10 በላይ የተሰባበሩና የተቃጠሉ መኪናዎች አሉ” ብሏል።እየደረሰ ያለውን ጉዳት በዝርዝር ያስረዳው ይኸው አስተያት ሰጪ፣ በአሽከርካሪዎችና በንብረት ላይ የደረሰውን ጉዳት በተመለከተ ሰሞኑን እስከ 70ና 80 የሚሆኑ አሽከርካሪዎች ከነተሸከርካሪዎቻቸው ለአማራ ክልል የተለያዩ … [Read more...] about ኦሮሚያን አቋርጠው የሚያልፉ የከባድ ጭነት ተሽከርካሪዎች ፈተና