• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኮሜርሻል ኖሚኒስ የሕወሓት ባለሥልጣናት ሕንፃዎችን ሊያስተዳድር መሆኑ ተነገረ

July 11, 2021 07:20 am by Editor Leave a Comment

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀው ሕወሓት ቡድን አባላት ሕንፃዎችን በገለልተኛ አካል እንዲተዳደር በወሰነው መሠረት፣ ሕንፃዎቹን ኮሜርሻል ኖሚኒስ ተረክቦ ሊያስተዳድር መሆኑ ተሰማ፡፡

በሰኔ 2013 ዓ.ም. አጋማሽ የሕወሓት ቡድን አባላት ንብረት የነበሩ ከ30 በላይ የንግድና የመኖሪያ ሕንፃዎች፣ በሰሜን ዕዝ ላይ ጥቃት ፈጽሟል በሚል በተከናወነ የወንጀል ምርመራና የሀብት ጥናት መሠረት በገለልተኛ አካላት እንዲተዳደሩ መወሰኑ ይታወሳል፡፡

እነዚህን ንብረቶች የማስተዳደር ጉዳይ አስመልክቶ ከጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጋር ንግግር እያደረገ መሆኑን ለሪፖርተር የተናገሩት፣ የኮሜርሻል ኖሚኒስ የቢዝነስ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ ገብረ ሕይወት ጌታሁን ናቸው፡፡

ንብረቶቹ የሕወሓት አመራሮችና ደጋፊዎች በተለያዩ መሠረተ ልማቶችና ሲቪል ተቋማት ላይ ላደረሱት ውድመትና ጉዳት ለማካካሻነት የሚውሉ በመሆናቸው፣ እንዲሁም የተጠርጣሪዎችን ንብረት የያዙ አካላት የሚፈጽሙትን ምዝበራ ለመከላከል ሲባል በተጠረጠሩበትና በተከሰሱበት ወንጀል ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ገለልተኛ አካል እንዲያስተዳድራቸው፣ ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤት አቤቱታ በማቅረቡ መሆኑን መገለጹ አይዘነጋም፡፡

የሰው ኃይል በማቅረብና ንብረት በማስተዳደር ከ35 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በአብዘኛው በጥበቃና በፅዳት የሥራ ዕድል በመፍጠር የተሰማራው ኮሜርሻል ኖሚኒስ፣ እያከናወናቸው ባሉ ሥራዎችና እየገጠሙት ባሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ምክክር አድርጓል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ከ30 በላይ ቅርንጫፍ ቢሮ ያለው ተቋሙ ሕንፃዎችን ማስተዳደር ጨምሮ፣ የሰው ኃይል በማቅረብና በሌሎች በ13 የሥራ ዘርፎች ተሰማርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።

ከጥቂት ወራት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ ጥናት ኮሜርሻል ኖሚኒስ በሥራ ላይ ላሰማራቸው ከ35 ሺሕ በላይ ሠራተኞች መንግሥት ያስቀመጠውን የ20/80 የደመወዝ ክፍያ አሠራር ተግባረዊ ባለማድረጉ ምክንያት፣ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2013 ዓ.ም. ያደረገውን የማስተካከያ ዕርምጃ ለምክር ቤት እንዲያቀርብ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

ተቋሙ አሁን ማሻሻያዎችን በማድረግ እየሄደበት ያለውን አሠራር ከሞላ ጎደል ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን በመጥቀስ፣ በሚቀጥለው ዓመት ለሠራተኞቹ የደመወዝ ማስተካከያ የማድረግ ዕቅድ እንዳለው አቶ ገብረ ሕይወት ተናግረዋል፡፡ (ሲሳይ ሳህሉ-ሪፖርተር)

(የአሸባሪው ህወሃት አባላት ቤት ፎቶዎች የተገኙት ከጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ፌስቡክ ገጽ ነው)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tigray

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule