• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጋምቤላና ቤንሻንጉል የትህነግ ተላላኪዎች እርምጃ ተወሰደባቸው

August 18, 2021 01:15 am by Editor Leave a Comment

በጋምቤላ ከተማ በአሸባሪዎቹ ህወሃት እና ሸኔ ተላላኪነት የተጠረጠሩ ሶስት ግለሰቦችን ከጦር መሳሪያና ሌሎች ቁሳቀሶች ጋር በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

የክልሉ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በቁጥጥር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል ሁለቱ የቀድሞውን የሀገር መከላከያ የደንብ ልብስና ጫማ እንዲሁም የሕክምናና ሌሎች ቁሳቁስ ይዘው ከጋምቤላ ከተማ ወደ ጫካ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸው ነው።

ቀሪው ተጠርጣሪ ደግሞ ከህዝብ በደረሰ ጥቆማ በቤቱ በተደረገ ፍተሻ አንድ ዘመናዊ የጦር ሜዳ መነጽርና አንድ ሽጉጥ ተገኝቶበት እንደሆነ አመልክተዋል።

ተጠርጣሪው ካሁን በፊትም ከአሸባሪው ህወሃት ጋር ግንኙነት እንዳለው ተጠርጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል።

በተጠርጣሪዎቹ ላይ እየተደረገ ያለው ተጨማሪ ምርመራ ሲጠናቀቅ ጉዳያቸው ወደ ፍርድ ቤት እንደሚላክ ምክትል ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

ክልሉ ጠረፋማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የህወሃትና ሌሎች የሽብር ቡድኖች ተላላኪዎች ሰርገው እንዳይገቡ የክልሉና የፌዴራል የጸጥታ አካላት የቁጥጥር ስራ እያካሄዱ እንደሚገኙም አመልክተዋል።

ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅና የአሸባሪ ቡድኖች ተላላኪዎችን አጋልጦ በመስጠት ረገድ የጀመረውን ተሳተፎ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ምክትል ኮሚሽነሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በክልሉ ከሶስት ቀን በፊት በተደረገው ክትትል የጸጥታ ስጋት ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 93 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር እንደዋሉ ይታወሳል።

በሌላ በኩል በሱዳን በኩል ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመግባት በክልሉ ሽብር ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ170 በላይ ጸረ ሰላም ኃይሎች ተደመሰሱ።

በሱዳን በኩል ሾልከው ወደ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ጉባ ወረዳ አልመሃል አካባቢ በመግባት ሽብር ለመፍጠር እና በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት ለማድረሰ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ጸረ ሰላም ኃይሎች ላይ በተወሰደ የተቀናጀ እርምጃ ከ170 በላይ የሚሆኑት መደምሰሳቸውን የክልሉ ሰላም ግንባታና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አቢዮት አልቦሮ በሰጡት መግለጫ፣ አሸባሪው የሕወሃት ቡድን በክልሉ እና ከክልሉ ወጪ ከሚንቀሳቀሱ ተባባሪዎቹ ጋር በመሆን በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ግጭት ለመፍጠር ሲሠራ መቆየቱን አስታውሰው፣ በእነዚህ ጸረ-ሠላም ኃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ በተጠናከረ ሁኔታ መወሰድ መጀመሩን ተናግረዋል።

በዚህም መከላከያ ሠራዊትና ፌደራል ፖሊስ ከክልሉ የጸጥታ አካላት እንዲሁም በክልሉ ከሚገኙት የደቡብ፣ የጋምቤላ እና የሲዳማ ክልሎች ልዩ ኃይል አባላት ጋር በመቀናጀት እስከትናንት በተወሰደው የህግ የማስከበር እርምጃ ከ170 በላይ የሚሆኑ ጸረ ሰላም ኃይሎች ተደምስሰዋል ብለዋል።

የተደመሰሱት ጸረ ሰላም ኃይሎች በሱዳን ድንበር በኩል በመግባት በመተከል ዞን የሕዳሴ ግድብ መገኛ በሆነው ጉባ ወረዳ አልመሃል ቀበሌን እንደ ማዕከል ተጠቅመው ወደ ግድቡ የሚወስደውን መስመር በመቁረጥና እንቅስቃሴን በማወክ ሥራውን ለማስተጓጎል ዓላማ የነበራቸው መሆኑን አቶ አብዮት ገልጸዋል። (ኢቢሲ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News, Politics Tagged With: operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule