... የአገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት በዚህ ዐመት በዚህ መጠን ጨምሯል፡ አልጨመረም እያሉ ሙግት ውስጥ እምብዛም መግባት የሚያስፈልግ አይደለም። ምክንያቱም ስለአንድ አገር ዕድገት በቁጥር ከተደገፈ ማሰረጃ ይልቅ ሁኔታው የበለጠ በቂ ማስረጃ ስለሚሆን ነው። በሌላ ወገን ደግሞ በኢኮኖሚ ዓለም ውስጥ የሚያወናብዱ ብዙ ሁኔታዎች አሉ። የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የብዙ አፍሪቃ አገር ኢኮኖሚዎችንም በሚመለከት እነ ዓለም ባንክ ሁሉ ሳይቀሩ የዓለም የፊናንስና ኢኮኖሚ ቀውስ ከመከሰቱ በፊት በዕድገት እንደመነጠቁ ሊያሳምኑን ሞክረው ነበር። ይህ በጥሬ ሀብት ጥያቄና ሽያጭ ላይ የተሰመሰረተ ዕድገት የዓለም ኢኮኖሚ ሲዳከም በዚያው መጠንም ዕድገቱ ወደታች እያለ እንደመጣና፣ ይህ ዐይነቱ ዕድገት ደግሞ ለምን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ሊባል እንደማይችል በብዙ ማስረጃ በተደገፈ መልስ ተሰጥቶበታል።ሙሉው ጽሁፍ … [Read more...] about የሚያድግ ኢኮኖሚ ነገር ግን የማይታይ የማይዳሰስ!
የዳምጠው አየለ ጥሪ!!
“ሰው ናፈቀኝ፣ ልጆቼና አገሬ ታወሱኝ፣ ባህሌና ልማዴ የት ገባ….?” የሚሉት የአንድ ስደተኛ ጥያቄዎች ለመቶ አለቃ ዳምጠው አየለ ተረት ሆነውበታል። አርቲስት ዳምጠው አየለ ከሁርሶ የመኮንኖች ማሰልጠና ማዕከል የመኮንንነት ትምህርት ተከታትሏል። ለሰላሳ ሁለት ዓመታት በምድር ጦር የሙዚቀኛ ሻለቃ አገልግሏል። በተለይም በባህላዊና አገር በሚያሞካሹ ዜማዎቹ የሚወደደው ዳምጠው አገሩን፣ ሁለት ልጆቹንና ባለቤቱን ጥሎ በስደት ኖርዌይ ከገባ ሰባት ዓመታት አሳልፏል። የስልሳ ሶስት ዓመቱ ዳምጠው ያጋጠመውን ጊዚያዊ ችግር አስመልክቶ ከጎልጉል የአውሮፓ ዘጋቢ ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። ዳምጠው ችግር እንዳጋጠመው ሲሰማ አስቸኳይ ድጋፍ ላደረጉ ወገኖች፣ ድርጅቶች፣ ማህበሮች፣ ላደረጋችሁት በአርአያነት የሚጠቀስ ተግባር የዝግጅት ክፍላችን በዚህ አጋጣሚ ለማመስገን ይወዳል። “… አዎ፤ እኔም ራሴን … [Read more...] about የዳምጠው አየለ ጥሪ!!
The Ethiopians and moral conduct.
I dreamt about my uncle. He has been dead for over ten years so I was wondering what brought him to my conscious now. It was a vivid dream and I woke both sad and happy. So all day long I kept wondering what is it that made me dream about him. I really think I was able to come up with a reasonable explanation why this memory was triggered in my brain. I believe it is due to what I have been reading lately that woke up this memory about service, integrity and today’s Ethiopia. The night before … [Read more...] about The Ethiopians and moral conduct.
ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!!
ኢህአዴግ ከዓለም ባንክ ያገኘውን 600 ሚሊዮን ዶላርና በተመሳሳይ ፕሮጀክት ወደፊት ሊያገኝ የሚችለውን ከፍተኛ ገንዘብ በተመለከተ አደጋ ውስጥ መውደቁ ተሰማ። ኢንስፔክሽን ፓናል (Inspection Panel – IP) የተሰኘ ተቋም ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው ኢህአዴግ የቀረበበት ውንጀላ ከተረጋገጠ የሚያጣው ገንዘብ በቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ታውቋል። ይፋ የሆነውን መረጃ አስመልክቶ ከኢህአዴግ ወገን እስካሁን በይፋ የተሰጠ ምላሽ የለም። ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትን፣ በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጽሙ ወንጀሎችን መረጃዎችን በስፍራው በመገኘትና ከመሠረቱ ዘልቆ በመግባት አደራጅቶ ተጠያቂ የሚያደርገው ኢንክሉሲቭ ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል Inclusive Development International (IDI) ከሰለባዎቹ ውክልና ተሰጥቶታል። ተቋሙም በውክልናው መሰረት … [Read more...] about ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!!
ወግድልኝ ወዲያ!
አሥራደው (ከፈረንሳይ) ሲጭኑህ አጋሰስ፤ ሲጋልቡህ ፈረስ፤ ጠምደው ሲያርሱህ በሬ _ _ _ ስትታለብ ጥገት፤ በቁም ሲያርዱህ ሙክት፤ ሲጣልልህ ውሻ - የጅ ዕባሽ ናፋቂ፤ እዳሪ ለሆዱ - ክብሩን አስነጣቂ፤ ጫንቃህ የደለበ - ለመሸከም ቀንበር፤ እንቢኝን የማታውቅ - ከእሽታ በቀር፤ እንዳህያ ጭነት - ሸክም ያስለመዱህ፤ ሲገፉት ነፃነት - የማይበርደው ገላህ፤ አጎንባሽ ለመጣው - የሞትክ ነህ በቁም፤ ወግድልኝ ወዲያ ጭራሽ አላውቅህም! እንዳንተ ያለውን አገሬ አትናፍቅም:: የአያት የቅድም አያት - ጀግንነቱ ቀርቶ፤ ሽለላ፤ ፉከራው - ዕምቢልታ ቀረርቶ፤ በጦር ደረት መብሳት - በጋሻ መክቶ፤ አሻፈረኝ ማለት - ለበደል ለጥቃት፤ በጀግንነት መሞት - ላገር ለነፃነት፤ መሆኑ ቀረና፤ የጀግና ልጅ ጀግና፤ ሰብዕናህ ተገፎ - ዝቅ ብለህ ወደታች፤ ባይተዋር ያገሩ - … [Read more...] about ወግድልኝ ወዲያ!
አዜብ መስፍን ፈርተዋል!!
መለስ የሚያቆላምጧቸው ወ/ሮ አዜብ ለመቀማጠልና ለደኅንነታቸው በመስጋት ቤተመንግሥቱን “አልለቅም” ማለታቸውን የጎልጉል ምንጮች አረጋገጡ። የአዲስ አበባ መረጃ አቀባዮቻችን እንደሚሉት ከሆነ የቀድሞዋ “ቀዳማዊት እመቤት” ሶስት ቪላዎች እንዲያማርጡ ቢለመኑም አሻፈረኝ በማለት ባነሱት የደኅንነት ጥያቄ ገፍተውበታል። ከህወሓት መከፈል በኋላ አቶ መለስ ህወሓትን በመዳፋቸው ውስጥ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ገንነው የወጡት ወ/ሮ አዜብ የተባረሩት፣ የተባረሩት ደጋፊዎችና የህወሓት ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ኢህአዴግ ውስጥ ጥርስ የነከሱባቸው ይበረክታሉ። የሥልጣን እርከን በመጣስ ከሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት በተጨማሪ ለሚያካሂዱት የንግድ ስራ ሲሉ መመሪያ በመስጠት፣ የማይፈልጉትንና አልታዘዝ የሚሉዋቸውን ባለሥልጣናት በማስገደድ፣ በተለይም ተወላጅ ሳይሆኑ በህወሓት አመራሮች ላይ ሲያሳዩ … [Read more...] about አዜብ መስፍን ፈርተዋል!!
ያልተመጣጠነ ግጥሚያ
ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ታመዋልም ሞተዋልም በሚማልበት ሰአት ሎጋው ሽቦ ተዘፈነ … የርዕሰ ብሄር መለስ ዜናዊ ሞት ይፋ በሆነበት ሰአት ደግሞ ብር አንባ ሰበርልዎ ተብሎ ሲዘፈን በሰፊው ተሰማ… ኃይለማርያም ደስ አለኝ ቦታው ተፈቅዶላቸው ሀገር ወከሉ ተብሎ ሲታወጅ አስገራሚው ዘፈን አላቆመም የቤተ ዘመዱ ይታያል ጉዱ ይባል ተገባ… ***************************************************************************************************** አጋጣሚ የፈጠረውን ፖለቲካዊ ግርግር በጥበብ ተጠቅሞ በፖለቲካው እንቅስቃሴ ውስጥ የመደራደሪያ አቅም በማበጀት ወይም አቅም በመገንባት አማራጭ ሀይል መሆንን ከማሳየት ፋንታ በቀረርቶና በሽለላ የጨዋታውን ህግ ለመቀየር መመኘት የምኞት ሁሉ መናኛ ቢባል ያስነውር ይሆን? በትግል … [Read more...] about ያልተመጣጠነ ግጥሚያ
ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር
“… ከሁሉ አስቀድሞ ማሸነፍ የሚኖርብን በውስጣችን ያለውን ፍርሃት ነው። ለህወሃት/ኢህአዴግ ታማኝ ሊሆኑ የሚችሉት የጦርና የፀጥታ ኃይሎቹ እንዲሁም የስለላ ተቋሙ የህዝብ ድጋፍ የሌላቸው የጥቂት ዘረኞች ስብስብ በመሆኑ የሕዝብ እምቢተኝነት ሲጠናከር በቀላሉ ይመክናሉ። አመራሮቹ አስተሳሰባቸው በጣም ጠባብ፤ ብቃታቸውም እጅግ ዝቅተኛ ነው። በመሆኑም እነዚህ ኃይሎች ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠሩት አድርጎ ማሰብ ራስን ማዋረድ ነው። ስለዚህም መሸሽ ሳይሆን በየጊዜው ልንፈታተናቸው፣ ልንጎነትላቸውና ልንፋለማቸው ይገባል። ስለሆነም ካሁን በኋላ ሥራው ህወሃት/ኢህአዴግን ከውስጥ ሆኖ የመበታተንና የማፍረስን ሥራ ነው። የነጻነት ኃይሎችም መዋቅራቸውን በማስፋትና በርካታ ህዋሶችን በመፍጠር በትጋት እየሠሩ ይገኛሉ። የህወሃት/ኢህአዴግን የመዋቅር ስፋት በነፃነት ኃይሎች የመዋቅር ስፋት መጋፈጥ ይቻል ዘንድ … [Read more...] about ከሞት በፊት እውነተኛ ክብር
በለገጣፎ ገሃነምና ገነት አየሁ!
“የኦሮሞ እንግዴ ልጅ” በሚል ስያሜ የሚጠራው ኦህዴድ በ1997 መስቀለኛ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር። ጥያቄውን ያቀረቡት አንድ በዕድሜ ጠና ያሉ አዛውንት ነበሩ። ጥያቄው የቀረበው አዳማ /ናዝሬት/ ቀበሌ 11 አዳራሽ ውስጥ ነበር። ተጠያቂው የወቅቱ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ሳዶ ሲሆኑ ስብሰባው የተጠራው “ለምን አልመረጣችሁንም” በሚል ኦህዴድ ከህዝብ ጋር ያለውን ችግር ለመፍታት ታስቦ ነበር። “ኦነግ ኦሮሞ ነው። እናንተም ኦሮሞ ከሆናችሁ ለምን አንድ አትሆኑም? እናንተ አንድ ብትሆኑ ልጆቻችን አይታሰሩም፣ አይገረፉም፣ አይሰቀሉም፣ የደረሱበት እየጠፋ ሃዘን አንቀመጥም፣ ኦሮሞ እስከመቼ ይታሰራል?” የሚል ጥያቄ ያቀረቡት አባት ንግግራቸውን መጨረስ አልቻሉም ቤቱ በጭብጨባ ተናወጠ። “በኔ ዘመን የኦሮሞ ልጆች እንዳይታሰሩ አድርጌያለሁ። በድሬዳዋና በቦረና በኩል የገቡትን ኦነጎች … [Read more...] about በለገጣፎ ገሃነምና ገነት አየሁ!
ከኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል የተላከ ጥሪ
በመከለኛው ምሥራቅ ሃገሮች በቤት ውስጥ አገልጋይነት ለሚሠሩ ሴቶች ድጋፍ የሚደረግ የእግር ጉዞ በዓለምአቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያን ሴቶች መብቶች ለማስከበር የተቋቋመው ድርጅት የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል (የኢሴመማ) ለኢትዮጵያዊያት ሴቶች ድጋፍ የእግር ጉዞ አዘጋጅቷል።የጥሪው ሙሉው ቃል እዚህ ላይ ይገኛል የአማርኛ በራሪ ወረቀት እዚህ ላይ ይገኛል Click here for the English flyer … [Read more...] about ከኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማዕከል የተላከ ጥሪ