
መሰላል
መሰላል ለመውጣት
አለው ትልቅ ብልሃት፡፡
የላዩን ጨብጦ፣
የታቹን ረግጦ፣
ወደላይ መመልከት፡፡
እጆችን ዘርግቶ በኃይል መንጠራራት፡፡
ጨብጦ መጎተት የላዩን!
ላዩ ታች እንዲሆን!
አንድ ባንድ እየረገጡ፣
መሰላል የወጡ፡፡
ብልሆች የማይጣደፉ፣
ሞልተዋል በያፋፉ!
ዘርግተው የጨበጡትን መርገጥ፣
የመውጣት ሕግ ነው የማይለወጥ
ሲወርዱ ግን ያስፈራል፤
የረገጡትን ያስጨብጣል፡፡
(መስፍን ወልደማርያም፣ እንጉርጉሮ፣ 1967)
yeKanadaw kebede “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ ላቀረቡት የግጥም ጨዋታ ዱባለ፣ በለው እና dawit ለጨዋታው ምላሽ ስለሰጣችሁ ከልብ እናመሰግናችኋለን፡፡ የጨዋታውን ደራሲ yeKanadaw kebede እንዲሁ፡፡ ስለ “መሰላል”ስ ምን ትላላችሁ? እስቲ ጨዋታውን አምጡታ!?
********************
መሰላልን የወጡ
እንዳይረሱ እንዴት እንደወጡ
ሲጀምሩ ጨብጠው እረግጠው
ግራ ቀኝ እጃቸውን ዘርግተው
የሚደርሱበትን እየማተሩ
አንገት ሳያዟዙሩ ይወጣሉ እንደፈሩ
ከጫፍ መድረስ አይቀር
ደግሞ ሲውርዱ ማቀርቀር
ከታች ደግፎ ያበረታታቸው
ይገረማል ይጨነቃል
ከላይ ወደታች ያዩታል
ቀስ ብላችሁ አይዟችሁ ውረዱ ይላቸዋል
እንደወጡ መቅረት የለ ተመልሶ ያገኛቸዋል
በእርግጥ ተጨብጦ የተረገጠው
ተረግጦ የተጨበጠው
የሁሉ መወጣጫ መሰላል የሆነው
በተራው ደስ አለው
ለካስ ይህ ሁሉ የተፈጥሮ ውጣ ውረድ ነው።
*************
ከሀገረ ካናዳ ከሰላምታና ምስጋና ጋር በለው!።
መስላል ነው መወጣጫ እላይ መስቀያ
ከጫፍ ሆኖ ሁሉን ማያ
እጅግ በጣም አርቆ ማስተዋያ
ለባለ እጅ ለአዋቂ ባለሙያ
ካላቆሙት አስተካክሎ በጠንካራ መደገፍያ
ለዝንጉ አይሆንም ለገልቱ ማረፊያ
ይስደዋል ወደ ታች ያወርደዋል ዘብጥያ
ለአላፊው ለአግዳሚው ለተረሳው መሳለቂያ::
አጉል መንጠላጠል በመሰላል መውጣት፤
ከሆነ ፈሊጡ ተሰቅሎ ለመቅረት፤
እንዲህ እንደዋዛ ሲቀናጡ የወጡት፤
ወደታች ሲጎትት የመሬቷ ስበት ፤
ሆኖ ያስቸግራል ቁልቁለቱ አቀበት ::
መሰላል የሚሉት መወጣጫ ነገር፤
ሲወጡ ይመቻል አያዳልጥ እግር፤
ግን !
ካልተስተካከለ እታች ካለው በምድር፤
መውረጃ ያሳጣል በድንገት ሲሰበር ::
መልካም መዳላድል ከተሠራላቸው
ምሣርና ሸክም ካላስመረራቸው
ሰውና መሰላል አንድ ባሕሪ አላቸው
መዶሻና ሚስማር የያዘውን ሁሉ
‘ምሁር ነው’
‘ጀግና ነው’
‘መላክ ነው’……እያሉ
ከዳመና በላይ ሰውን ይሰቅላሉ