• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አልአሙዲ ያጠሩትን መሬት ተነጠቁ

December 12, 2012 11:11 am by Editor 2 Comments

የሼክ መሐመድ ሁሴን አልአሙዲ ኢንቨስትመንት ላይ ጥያቄ ያላቸው ጥቂት አይደሉም። የራሳቸውን ህንጻ ከመጨረስ ይልቅ በኪራይ አንድ ህንጻ የሚያሰራ ገንዘብ ለዓመታት ሲከፍሉ ማየትና መስማት የተለመደ ነው። የንግድ ሰዎች ይህንን ዝንባሌያቸውን ከነጋዴ የሚጠበቅ እንዳልሆነ ይናገራሉ። በዙሪያቸው ተሰባስበው ያሉትም ቢሆኑ አመቺ ቦታ ሲያገኙ በዚሁና በሌሎች ጉዳዮች ያሟቸዋል።

ናኒ ህንጻ

ጊዮን ሆቴል አጠገብ የተሰራው የናኒ ህንጻ ሲጀመር የተወለደ ህጻን አስራ ሁለት ዓመት ሲሞላው ነው ያለቀው። ከጊዮን ሆቴል ፊትለፊት ለአስራ ሁለት ዓመት ለህንጻው መጋዘን ሆኖ ሲያገለግል የነበረው የአዲስ አበባ ስታዲየም የመኪና ማቆሚያ ተገቢው ክፍያ ሳያገኝ ቢኖርም የሳቸውን ፎቶ በስታዲየም ውስጥ ለመለጠፍ ቀዳሚ ነው። አሁን መለስ መጡና አሳነሷቸው እንጂ ስታዲየሙ የእርሳቸው የሚመስልበት አጋጣሚም ነበር።

“መበደር፣ መጀመርና ማጠር እንጂ መክፈል፣ መጨረስና አጥር ማፍረስ አይወዱም” የሚባሉት ሼኽ መሐመድ፣ ግርግር ባለበት ቦታ መታየትና፣ አጋጣሚዎችን በመጠበቅ በሚያበረክቱት ስጦታ ስማቸው ከመነሳቱ ውጪ ከብድርና ከእዳ የጸዳ ፕሮጀክትም ሆነ ንብረት ባገር ውስጥ እንደሌላቸው የሚናገሩት ቀርበው የሚያውቋቸው ናቸው። በሌላ በኩል ብድር የሌለበት ንግድ ሊኖር አይችልም፣ ዋናው የተበደሩትን መክፍሉ ላይ ነው በሚል የሚደግፏቸውም አሉ።

በአዲስ አበባ በቦሌ፣ በልደታና በአራዳ ክፍለከተማ የያዟቸው መሬቶች በርካታ ቢሆኑም እንደ ሌሎች ባለሃብቶች ግንባታ አላከናወኑም በሚል ሲቀጡ አይሰማም። መሬታቸውም ሲወሰድ አይታይም። ባለስልጣናትም የእርሳቸው ድርጅቶች ላይ ውሳኔ ለመውሰድ አይደፍሩም። በተለይም መሃል ፒያሳ የታጠረው አጥር ላለፉት አስራ ሁለት አመታት እግረኞችን ጤና መንሳቱ እየታወቀ የተናገረ የለም። የአዲስ አበባ አስተዳደር አፍንጫው ስር ህዝብ መረማመጃ በማጣት ሲሰቃይ ተመልክተው ውሳኔ አለማሳለፋቸው አነጋጋሪ ነበር።

ከፕሮጀክቱ መጀመር በላይ ኩማ ደመቅሳ አዲስ አበባን ሲረከቡ አንድ ሚስጥር ይፋ ሆነ። የባለሃብቱ ድርጅት ከሆኑት መካከል አንዱ ሆነው ሁዳ ሪል ስቴት አዲስ አበባ መሃል ፒያሳ አራዳ የተሰጠው ሰፊ መሬት ከሊዝ ክፍያ ነጻ በስጦታ መሆኑ ታወቀ፤ አዲስ አበባ እምብርቷ ላይ ዘመናዊ የገበያ አዳራሽ (mall) ይሰራል ተብሎ ዲዛይኑ ቀረበ። ባለስልጣኖች ዲዛይኑን ሲመለከቱ የምርቃት ሪባን መቁረጥ ታያቸው። ከሊዝ ነጻ የተሰጠው ይህ ሰፊ መሬት ሳይገነባ አፈር ቁፋሮ እያካሄደ ዓመታትን አስቆጠረ።

ቀደም ሲል ጀምሮ የሚነገር ቢሆንም የአዲስ አበባ አስተዳደር ካለፈው ወር ጀምሮ ጠንካራ ርምጃ ለመውሰድ ማቀዱ፣ ባለፈው ሳምንት ደግሞ የዚሁ ርምጃ አካል የሆነው ውሳኔ ሃሳብ ጫፉ መነካቱን ሪፖርትር ለንባብ አብቅቶ ነበር። ሪፖርተር በነካ እጁ ሰሞኑን የባለሃብቱ አንድ ድርጅት የሆነው ሁዳ ሪል ስቴት ሜክሲኮ ዋቢሸበሌ ሆቴል አጠገብ ወስዶት ነበረውን መሬት እንደተነጠቀ አስነብቧል።

የሁዳ ሪል ስቴት መንትያ ሕንፃ ዲዛይን

በዚሁ ዜና መሰረት ሁዳ ህዳር 25 ቀን 2005 ዓ ም የተነጠቀው መሬት 6‚400 ካሬ ሜትር ሲሆን ቀደም ሲል ግንባታው ሳይጀመር ላለፉት ስምንት ዓመታት ታጥሮ የተቀመጠ ቦታ ነው።  ይኸው ቀደም ሲል የመኪና መለማመጃ የነበረው ቦታ ሁለት ዘመናዊ ባለ ሃያ ፎቅ (እስከ 25 ሊደርስም ይችላል) መንትያ ህንጻዎች ይገነቡበታል ተብሎ እቅድና ዲዛይን የቀረበበት ነበር።

የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮው በጻፈው ደብዳቤ ሁዳ ሪል ስቴት በገባው ውል መሥሪያ ግንባታ ባለመጀመሩ ለቦታ ባለቤትነት የተሰጠው ካርታ መምከኑን ሪፖርተር ጽፏል። አያይዞም ቁፋሮው በሚገባ ተከናውኖ ሕንፃውን መገንባት ባለማስቻሉና አስተዳደሩ በኩባንያው ተግባር ትዕግሥቱ በመሟጠጡ ዕርምጃ መውሰድ እንደቻለ ሪፖርተር የቢሮው የሥራ ኃላፊዎችን ጠቅሶ አስታውቋል።

የሁዳ ሪል ስቴት መንትያ ሕንፃ ዲዛይንን የሠራው ናሽናል ኮንሰልት ኩባንያ ነው፡፡ ግዙፉና ውበት የተላበሰው የሕንፃ ዲዛይን መሬት ላይ ባለማረፉ ፕሮጀክቱ እንዲመክን ተደርጓል፡፡ ሼክ መሐመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ በሚድሮክ ኢትዮጵያ፣ በሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕና በደርባ ሚድሮክ ግሩፕ ሥር በርካታ ኩባንያዎች አሏቸው፡፡ በእነዚህ ግሩፖች ሥር ሁዳ ሪል ስቴት፣ ሚድሮክ ኮንስትራክሽን፣ ሚድሮክ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤትና ሚድሮክ ፋውንዴሽን በኮንስትራክሽን ሥራዎች ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ናቸው፡፡

ሁዳ ሪል ስቴት በሚረከባቸው ቦታዎች ላይ ሚድሮክ ኮንስትራክሽንና ሚድሮክ ፋውንዴሽን የግንባታ ሥራዎችን የሚሠሩ ቢሆንም፣ ሚድሮክ ኮንስትራክሽን በሥራው ውጤታማ ባለመሆኑ ካለፉት ወራት ወዲህ ግንባታውን የማካሄዱን ሥራ ተነጥቆ በደርባ ሚድሮክ ግሩፕ ሥር ለሚገኘው ሚድሮክ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት እየተሰጠ ነው፡፡

ለሁዳ ሪል ስቴት የተሰጠው መሬት መነጠቁንና በቀጣይነት ሁዳ ሪል ስቴት ስለሚወስደው ዕርምጃ የደርባ ሚድሮክ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ኃይሌ አሰግዴ ቢጠየቁም፣ ከከተማ ውጭ በመሆናቸው ጉዳዩን እንዳልሰሙ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የሁዳ ሪል ስቴት የሜክሲኮ አደባባይን ፕሮጀክት መሬት የነጠቀው የአዲስ አበባ አስተዳደር፣ ሁዳ ሪል ስቴት በመሀል ፒያሳ ከከተማው አስተዳደር ሕንፃ ፊት ለፊት የተሰጠውን መሬትም እንደሚነጥቅ በቅርቡ አስጠንቅቋል፡፡

ፒያሳ የታጠረው ቦታ ከአትክልት ተራ በኩል

ኩባንያው ከ15 ዓመታት በፊት በመሀል ፒያሳ 36 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታ ቢሰጠውም በገባው ውል መሠረት ልማቱን ማካሄድ አልቻለም፡፡ በከንቲባ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው የከተማው አስተዳደር ሥልጣኑን እንደተረከበ ቦታውን ለመንጠቅ ሙከራ ቢያደርግም፣ ከንቲባ ኩማና የወቅቱ የከተማው አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ መኩሪያ ኃይሌ ከሼክ አልአሙዲ ጋር ባካሄዱት አንድ ሰዓት የፈጀ ውይይት፣ ኩባንያው በአሥራ አምስት ቀናት ውስጥ ግንባታውን እንዲጀምር ስምምነት ላይ ተደርሶ ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ግንባታውን አጓትቷል ከተባለው ሚድሮክ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቱ ተነጥቆ ለሚድሮክ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ተሰጥቶ ነበር፡፡

ነገር ግን ከዓመታት በኋላም ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ በተደረገው ስምምነት መሠረት ግንባታውን ሊያከናውን ባለመቻሉ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸው አምባዬ ኩባንያው ዕርምጃ ሊወስድበት እንደሚችል ፍንጭ መስጠታቸውን ባለፉት ሳምንታት የወጡ የዜና ጥንቅሮች ጠቁመዋል።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. TEWBEL says

    December 12, 2012 10:34 pm at 10:34 pm

    A good business person uses other peoples money, never his own.
    Al Amoudi is a very good busnessman he pratices the same. As to rents or expenses in Ethiopia he probably charges them as losses for his other numerous businesses.
    I wonder how much he owes local Ethiopian Banks ?

    Reply
  2. Henok says

    December 13, 2012 02:11 am at 2:11 am

    Why does he care? even weyane? There idea is to smuggle/embezzle the natural resource of Ethiopia and inorder to to mask the awarness, they create an image that reflects that they are making/ consturcting roads, bulidings and etc. Al-amudi is doing that, they all know that…and taking and giving is just part of their game: at night they drink togahter…
    This what the Apartide and the British in south africa doing. They created a mirrage, that shows that they are constructing the country. In the biggest univeristy of the country such as Wits, most black students are indirectly encouraged to study mining and if one studies mining then he will encourage anything related to it, and the idea is to make them mine their own land for external use. The same is happening here in Ethiopia….explotiation and slavery in its newness.
    Henoke Y.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule