ለቀድሞው የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስትር ለጊዜው ኳሷ በእሳቸው ቁጥጥር ስር እንደሆነች እና የኢትዮጵያ ህዝብን ፍላጎት ማክበር አለበለዚያም የኢትዮጵያ ህዝብ እና ታሪክ ጠላት ሆነው የመቀጠል ሁለት ምርጫ እንዳላቸው በኢትዮጵያ ምሁራን በየአቅጣጫው ቢነገራቸውም ፤ በማን አለብኝነት ኳሷን ባለማከፋፈል ችግር ፣ እኔ ብቻ በኳሷ እንደፈለኩ ከምፈልገው ወገን ጋር ልጫወትባት ፣ ስለ ኳሷ አትጠይቁኝ ፣ ወደ ኳሷም አትጠጉ በማለት ቀይ መስመር በማስመር እና እኔ ብቻ አውቃለሁ በማለት በ 80 ሚሊዮን ህዝብ ራእይ እና ተስፋ ላይ እንደቀለዱ ... (ሙሉውን ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about ዛሬ ነገ ሳንል መነሳት የዜግነት ግዴታችን ነው!
“ላለመማር መማር… ፤ ከ’ራስ ክህደት እስከ ሀገር ማፍረስ…”
በመጀመሪያ ‘ራሳቸውን ከዱ፣ ከዚያም በጥላቻ ታውሩ፣ ከዚያም ኢትዮጵያዊነትን ኢትዮጵያን አምርረው ጠሉ፣ ከዚያም በታሪካዊ ጠላቶቻችን እየተመሩና እየታገዙ፣ የገዛ ወገናቸውን ‘ርስ-በ’ርስ እያበጣበጡና እያለያዩ፣ ኢትዮጵያን እያፈራረሱ፣ ለባዕዳንና ለታሪካዊ ጠላቶቻችን እየቸበቸቡ አሁን ካሉበት ደረጃ ደረሱ። (ሙሉው ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “ላለመማር መማር… ፤ ከ’ራስ ክህደት እስከ ሀገር ማፍረስ…”
“… አንድ ኮማንዶ…”
ጊዜው የጠቅላይ ሚኒስትር መለሰ ዜናዊ ሕመማቸውና ሞታቸው በፈረቃ ተቃዋሚንም ሆነ ደጋፊን ዥዋዥዌ ሲያጫውቱት የነበረ ጊዜ ሲሆን፤ በተቃዋሚ በኩል መለስ ሲሞቱ ቢሯቸው ክፍት ስለሚሆን፤ ስልጣን የሚጠብቃት እረኛ በማጣቷ፤ ከቤተመንግሥስት ወጥታ ስትበር በወጥመድ ለመያዝ ያሰፈሰፈ ይመስል ነበር ቢባል፤ ብዙ የሚያሳማ ግንዛቤ አይመስለኝም። በዚያው ሰሞንም ነበር ጥምረትና ኦነገ (የጄ/ል ከማል ገልቹም) አሊያንስ ፈጠሩ ተብሎ የተወራው፤ ነገር ግን ወሬውን አጣጥመን ሳንጨርስ፤ በነሃሴ 1ቀን 2004 ዓ.ም. የተቋቋመው ስብስብ (ሰንጠረዥ ‹‹ለ››) ውስጥ ሁለቱ የአሊያንስ አባል ድርጅቶች ተነጣጥለው ገብተው እናገኛቸዋለን፤ ከዚያ ወዲህም የአሊያንስ ጉዳይ ኮሽታው ይጠፋል። (ሙሉው ጽሑፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “… አንድ ኮማንዶ…”
ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!
“ላለፉት ሶስት ዓመታት ማንም ሳያውቀን ታስረናል። አሁን ጉዳያችን ለዓለም መድረሱን ሰማን።የተፈታን መስሎናል” የሚሉት እስራኤል ራምሌ በሚባ እስርቤት ከሶስት ዓመት በላይ ታስረው ያሉት ወገኖች ናቸው። ይህ የሆነው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር በርዕስ ለእስራኤል ጠ/ሚኒስትር በግልባጭ ደግሞ ከጉዳዩ ጋር አግባብ ላላቸው ለተለያዩ የአገሪቱ ባለስልጣናት፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የመገናኛዎች አውታሮች ያሰራጩትን ደብዳቤ ተከትሎ በእስር ላይ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ በመንቀሳቀሱ ነው። በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማኅበር ሊቀመንበር አቶ ሳሙኤል አለባቸው አድማሱ ለጎልጉል እንዳስታወቁት ከእስር ቤት በስልክ ያነጋገሯቸው ወገኖች የደብዳቤውን መልዕክት ሰምተው አስታዋሽ በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል። አቶ ኦባንግ ሜቶ … [Read more...] about ከሲና የተረፉት የሲኦል ነዋሪዎች ጩኸት!!
Impediments of Good Governance in Ethiopia (part 2)
In the first part of the article, I outlined the major policy framework constraints that prevented the emergence of well functioning system of good governance in Ethiopia. The second and last part of the article attempts to sort out the major challenges that have prevented the realization of good governance in Ethiopia during the reign of EPRDF in the last two decades. The most important challenge that has been witnessed in the last two decades is particularly related to the gap between the … [Read more...] about Impediments of Good Governance in Ethiopia (part 2)
ህልመኛው
ህልመኛው ህልመኛ ነው እርሱ ሳያልም አያድርም፤ ኑሮው ማለም እንጂ ህልሙን ኖሮ አያውቅም፡፡ የሚለውን የቃልኪዳንን ግጥም ፌስቡክ ላይ ያነበበው ታምራት አወቀ (ሚራ) “እሱ” እያለች የገለጸችው እርሱን መስሎት በመባነኑ ከያኔዎቹ ህልሞቹ አንዱን እንካችሁ ብሏል፡፡ ፍሬ አልባ አዝመራ ሕልሜን ከእውኑ ጋር አገናኝቶ ‘ሚያሳይ መሄጃ ጎዳና አቅጣጫ እንጂ የጠፋኝ የሕልም የሕልምማ ተጋድሜ ውዬ፣ ተኝቼ እያደርኩኝ ብዙ ያመረትኩት፣ ሁሌ ‘ሚናፍቀኝ ለሚዛን የሚከብድ፣ ፍሬ ያላፈራ፣ የሕልም አዝመራ አለኝ:: ታምራት አወቀ (ሚራ) 2003 ዓ.ም እናንተስ ምን ትላላችሁ? የምታካፍሉት “የህልም አዝመራ” አላችሁ? ወይስ ሌላ የምትሉት አለ? ባለፈው ኑረዲን ዒሳ እኔ ምን አገባኝ በሚል ርዕስ ላቀረበው ግጥም ምላሽ የሰጣችሁትን Tsinat፤ ሰማኸኝ፤ yeKanadaw kebede (ሁለት … [Read more...] about ህልመኛው
የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!
ከሳምንታት በፊት የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!! ወርቃችን እንዴት አላሙዲ እጅ ገባ? በሚል ርዕር ላቀረብነው ጽሑፍ የድረገጻችን አንባቢ አሥራደው የሚከተለውን በግጥም የተከሸነ መልዕክት ልከውልናል፡፡ ተናገር መጋዶ ተናገር ሻኪሶ፤ ወርቅ ወዴት ተጋዘ ላንተ አፈሩ ደርሶ፤ ተናገር ሃዲማ ደግሞም ኡላኡሎ፤ እነማን ዘረፉት የወርቁን አሎሎ?! የወርቁን ቡችላ የለገ ደንቢውን፤ ደብዛውን ንገሩን የደረሰበትን?! እነማን ዘረፉት ? ማንስ ከበረበት?! እነማን ተዝናኑ? ማንስ ጨፈረበት?! ድሃ በደከመ ድሃ በሞተበት፤ ጦሙን እንደዋለ አፈር ተንዶበት:: አካፋና ዶማ ይዘው ሳይቆፍሩ፤ ጨለማ መግፈፊያ ሻማ ሳያበሩ፤ ጠብ ሳይል ላባቸው ባቋራጭ ከበሩ፡ ያገር አንጡራ ሃብት እየመዘበሩ:: በገዛ መሬቱ በተወለደበት፤ ዕትብቱ ተቆርጦ ለተቀበረበት፤ ለወርቁ ባለቤት ምንም ሳይሰሩለት … [Read more...] about የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!
የእህቶቻችን ሰቆቃ በአረብ ምድር
ይህ የምትመለከቱትን ፎት ያነሳሁት በጅዳው አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ በሚገኝ የጸጥታ አስከባሪ ፖሊሶች አንድ ጽህፈት ቤት ውስጥ ነው፡፡ ይህች የምታይዋት እህትም ምን እዚያ አመጣት እንዳትሉ ! ከአንድ ወር ከሳምንት በፊት በኮንትራት ስራ ከሀገር ቤት የመጣች መሆኗን ሳውዲው የእድሜ ባለጸጋ አሰሪዋ ተነገረውኛል፡፡ እኔም ሆንኩ ይህንን ጉድ አብረውኝ የሚመከቱ እህቶቸ ሁላችንም ወደ ሃገር ቤት የሚሸኙ ዘመዶቻችንና ወዳጆቻችን አጅበን ነና የመጣነው የዚህች እህት ወደ አየር መንገዱ ለምን እንዳመጣች መጠየቅ አላስፈለገኝም ፡፡ በሰውነቷ ላይ ባረፈውን እስራትና ድብደባ ከመገለ እጇና ገላዋ ላይ ሰንበር የመሰለ የጉዳት ምልክት ይታያል፡፡ (ሙሉው ታሪክ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about የእህቶቻችን ሰቆቃ በአረብ ምድር
ጥፋቱ የማን ነው?
ኤርትራዊ ሆነው በኢትዮጵያ ከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት የተሸከሙት አቶ በረከት ስምዖን በኢትዮጵያ ላይ የሚፈርድ፣ ዜጎችን የሚያሸማቅቅ፣ ለአገራቸው የተሰውትን የሚያናንቅና በተለይም በውድ አገራቸው የሚመኩ ወገኖችን የሚያኮስስ ንግግር ማድረጋቸው በህወሃት ነባር ታጋዮች ዘንድ ቅሬታ ማስነሳቱ ታወቀ። አቶ ስዬ አብርሃ፣ አቶ ገብሩ አስራት፣ እነ አቶ ተወልደን በስም በመጥራት በኤርትራ ጉዳይ ላይ ጥፋተኛ ያደረጉት አቶ በረከት “አንድነትና አንድ አገር” የሻዕቢያ መዝሙር መሆኑን በመናገር ኢትዮጵያ ውስጥ መገንጠል ለሚፈልጉ ጊዜው ሲደርስ እንደ ኤርትራ መገንጠል መብታቸው መሆኑን ተናግረዋል። በሚኒስትር ማዕረግ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ በረከት ይህንን የተናገሩት Eritrean Oppositions Arabic Paltalk በሚሰኝ የኤርትራ ተቃዋሚዎች የፓልቶክ መወያያ ክፍል … [Read more...] about ጥፋቱ የማን ነው?
ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!
ይቺ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስንት የመከራ ወንዞችን ተሻግራለች! ገና ስንት ትሻገራለች! ስንት የግፍ ተራራዎችን አቋርጣለች! ገና ስንት ታቋርጣለች! ስንት የበደል ሰይፎችንና ጦሮችን አምክናለች! ገና ስንት ታመክናለች! ስንት የውጭ ኃይሎችን አሳፍራለች! ገና ስንቱን ታሳፍራለች! ስንት አምባገ- ነኖችን እያለቀሰች ቀብራለች! ገና ስንቱን ትቀብራለች! ጭቆና ከኢትዮጵያውያን ደም ሙልጭ ብሎ ወጥቶ በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በዳኝነት በጠራ ደም እስቲተካ ድረስ “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ” ትጸልያለች! እግዚአብሔርም ቃል ኪዳን አለበት ይሰማታል! የኃያላን ኃያል ኢትዮጵያ እንድትፈርስ አይፈቅድም! የኢትዮጵያን መፈራረስ የሚመኙ ግለሰቦችም መንግሥቶችም ሞልተዋል፤ ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ የሚመኙ ጭንጋፍ ልጆችም አሏት፤ ማኅጸንዋ እየደማ እየረገማቸው ሰላምና እንቅልፍ አጥተው … [Read more...] about ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!