• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከእሁድ እስከ እሁድ

December 24, 2012 04:14 am by Editor 1 Comment

ኢህአዴግን በኃይል ለማስወገድ ጥሪ ቀረበ

በኢትዮጵያ ያለውን አገዛዝ ለመጣል ይቻል ዘንድ ለቀድሞው ሰራዊት፣ አሁን በስራ ላይ ላሉት የመከላከያ አባላትና በአገር ውስጥና በውጪ ስደት ላይ ላሉ ዜጎች ሁሉ የትግል ጥሪ ቀረበ። “የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል” በሚል ስያሜ ጥሪውን ያስተላለፈው ክፍል ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሚመሩት ድርጅት ጋር ግንኙነት እንዳለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ እንዳልተሳካለት ኢሳት ዘወትር እሁድ በሚያቀርበው የሳምንቱ ዜናዎች ላይ አስታውቋል።

ኢሳት በሰበር ዜና ያቀረበው ይህ ዜና ከዋናው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ግንኙነት እንዳለውና እንደሌለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው ባይሳካለትም፣ በቅርቡ ግን መረጃዎችን በማሰባሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ የሚያቀርብ መረጃ ለመስጠት እንደሚተጋ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያለ ህዝብ ይሁንታ ላለፉት ሃያ አንድ ዓመታት በሃይል መንበሩን የተቆጣጠረው ኢህአዴግ ከስልጣን ሊወገድ የሚችለው በትጥቅ ትግል ብቻ እንደሆነ ያመለከተው የጥሪ መልዕክት የወያኔ ትዕቢት ሊተነፍስ የሚችለው በህዝባዊ ትግል በትጥቅ ብቻ እንደሆነ አስምሮበታል።

ለቀድሞው ሰራዊት አባላት፣ አሁን በስራ ላይ ያሉ የመከላከያ አባላትና ለሁሉም ወገኖች ጥሪ ሲያቀርብ ክብሩ ያልተነካ፣ ያልተዋረደ አትዮጵያዊ እንደሌለ አመልክቷል። በኢትዮጵያ እስር፣ ግድያና ስቃይ የሚወገደው ሙሉ በሙሉ ስርዓቱ ሲወገድ ብቻ እንደሆነ አስታውቋል። (ሐብታሙ ሂካ ያምቦ፤ Habtamu Hiikaa Yaamboo; habtamu@goolgule.com)

መድረክ ግንባር ሆነ

ዓረና፣ ኦፌዴን፣ ኦሕኮ፣ አንድነት፣ ኢሶዴፓና የደቡብ ኅብረት ፓርቲን አካቶ የያዘው መድረክ ግንባር ለመሆን ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አገኘ። የምርጫ ቦርድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወ/ሮ የሺ ፈቃደ ቦርዱ የግንባርነት ዕውቅና መድረክ ላቀረበው ጥያቄ መስጠቱን ለሪፖርተር አስታውቋል።

የፖለቲካ አጀንዳውንና የገንዘብ አቅሙን በመገምገም ብቁ ሆኖ በመገኘት መድረክ ያቀረበው ጥያቄ በቦርዱ ተቀባይነት ማግኘቱን ወ/ሮ የሺ ገልጸዋል፡፡ ቀደም ሲል በመድረክ ሥር የነበሩ ፓርቲዎች ስምንት ሲሆኑ ሁለቱ ባለመስማማት በመውጣታቸው ወደ ግንባር ለመሸጋገር የወሰኑት ስድስቱ ፓርቲዎች ናቸው፡፡

በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 39 እና መሬት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ ይሆናል በሚሉት ጉዳዮች አባል ፓርቲዎቹ የማይግባቡባቸው ቢሆኑም፣ እነዚህ ልዩነቶች ቢኖሩም ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን በማስፈን ነፃና ሰላማዊ ምርጫ በሚፈጠርበት ሁኔታ ላይ ያለ ልዩነት ለመሥራት ስምምነት መድረሱን ዶ/ር ነጋሶ ገልጸዋል፡፡ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ከተፈጠረ የተለያዩባቸው ነጥቦች ሕዝብ የሚያነሳቸው ጉዳዮች በመሆናቸው፣ ወደ ሕዝብ በማውረድ ወደፊት መነጋገር ይቻላል ብለዋል፡፡ ስምምነት ከተደረሰም ግንባሩ ተዋህዶ አንድ ፓርቲ እንደሚሆን ጠቁመዋል፡፡

ኖርዌይ በኤርትራ ኤምባሲዋን እንደምትዘጋ አስጠነቀቀች

የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስፔን ባዛር ኢድን ሰሞኑን ኢትዮጵያ ነበሩ። ሚኒስትሩ ከጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝና ከአዲሱ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር መምከራቸውን የኢህአዴግ የዜና አውታር ዜና አገልግሎት አስታውቋል። ዜናው እንዳስረዳው ኖርዌይ ኢትዮጵያን ለመርዳት መማሏን ይገልጽና በተመሳሳይ ኤርትራ ያለውን ኤምባሲዋን ለመዝጋት በዝግጅት ላይ መሆኗን ለዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም መንገሯን ያመለክታል።

የኖርዌዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርን ጠቅሶ ዜናው እንደዘገበው በሱማሊያ ያለው ወቅታዊ መረጋጋት ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዲያገኝና ኢትዮጵያ በአደራዳሪነት እየተከታተለች ያለውን የሁለቱን ሱዳን ጉዳይ ሀገራቸው ለመደገፍ “ቁርጠኛ” መሆኖን አስታውቋል። በመጨረሻም ኤርትራን በቀጠናው በማካሄድ ላይ ያለችውን የማተራመስ ድርጊት የማታቆም ከሆነ ሀገራቸው ኤምባሲዋን ዘግታ እንደምታወጣ ማስጠንቀቋን አመልክቷል። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ኤርትራ ሄደው ኢሳያስ አፈወርቂን ለማነጋገር እንደሚፈልጉ ባስታወቁበት ማግስት የመንግስት መገናኛ ይህንን ጉዳይ ርዕሰ ዜና ማድረጉ የጠ/ሚኒስትሩ የድርድር ጥያቄ የቀልድ ለመሆኑ አመላካች ነው።

አንድነት አዲስ የህዝብ ግንኙነት ሾመ

መሰረታዊ ለውጥ ያካሂዳል የተባለው አንድነት የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ቋሚ ሰብሳቢ የነበሩትን ዶ/ር ሃይሉ አርአያን በአዲስ አመራር በመተካትና አቶ ስዬ አብርሃ አሜሪካ ያላቸውን ጉዳይ ሲጨርሱ ወደ ፓርቲው መመለስ እንደሚችሉ በመጥቀስ ሰንደቅ ጋዜጣ የፓርቲው ምንጮቼ ነገሩኝ በማለት ስዬ ከፓርቲው ሊታገዱ ይችላሉ ሲል ያሰራጨውን ዜና አስተባብሏል።የፓርቲውን ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳን በመጥቀስ ሪፖርተር ይፋ ባደረገው ዜና ከፓርቲው የተነሳ አመራር የለም።

ከፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ስራ ጋር ለረዥም ጊዜ ቁርኝት የነበራቸው ዶ/ር ሃይሉ በሃኪም ምክር ምክንያት ረፍት ማድረግ ስላለባቸው በአቶ ዳንኤል ተፈራ መተካታቸውን ታውቋል።አዲሱ የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ወጣት፣ ትኩስ ሃይልና በሳል መሆናቸውን ዶ/ር ነጋሶ መስክረዋል። የድርጅቱ ምክር ቤት ይህንኑ ተቀብሎ ለአቶ ዳንኤል  ይሁንታውን ሰጥቷል። የአንድነት የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ አንዷለም አራጌ መሆናቸው ይታወሳል። እስር ላይ ያሉት አቶ አንዷለም ጠንካራ አቋም ያላቸው ኢህአዴግ አብዝቶ ከሚፈራቸው መካከል በግንባር ቀደም የሚጠቀሱ ፖለቲከኛ ናቸው።

አንዷለም አራጌ ስቃይ ላይ ናቸው

አቶ አንዷለም አራጌ በጨለማ ቤት ውስጥ መታሰራቸውና ወለል ላይ እንዲተኙ መደረጉ ቅዝቃዜው ጤናቸውን አሳሳቢ እንደሚያደርገው ለፍርድ ቤት አስታወቁ።  የመተንፈሻ ችግር እንዳለባቸው የገለጹት አቶ አንዷለም አራጌ በጠባብ ክፍል ውስጥ ስድስት ሆነው በመታጎራቸው፣  ከባለቤታቸውና ጥቂት ቤተሰባቸው ውጪ ሌሎች ጓደኞቻቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው እንዳይጎበኟቸው መደረጉን በቅሬታ አቅርበዋል።

አቶ አንዷለም ጠበቆቻቸው የማነጋገር እድል መከልከላቸውን የገለጹ ሲሆን ዳኛው የስነስርዓት ጥያቄ በማንሳት አስቁመዋቸዋል። ጠበቃቸው የይግባኝ የፍርድ ሂደት ሳይቋጭ ከፍተኛው ፍርድ ቤት  የተከሳሾችን ንብረት ለመውረስ መጣደፉን በመጠቆም ያቀረቡትን መቃወሚያ ሳይጨርሱ ፍርድ ቤቱ “በጽሑፍ ያቅርቡ” ሲል አስቁሟቸዋል፡፡ ጠበቃ አበበ ጉታ በበኩላቸው ደንበኞቻችን በአንድ የክስ መዝገብ ቢከሰሱም ቃሊቲ እና ቂሊንጦ ተበትነው በመታሰራቸው ለጠበቆች ጥየቃ እንዳልተመቻቸውና በበቂ መጎብኘትና ማነጋገር አለመቻላቸውን ለፍርድ ቤት አሳውቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን ለውሳኔ ለጥር 10 ቀን 2005 ዓ.ም በጊዜ ቀጠሮ ያሻገረ ሲሆን ክርክሩ በጽሑፍ ተገልብጦ እንዲቀርብለት አዟል፡፡ (ዘገባውን ያጠናቀረው ኢሳት ነው።)

አለቆቻቸውን ያጋለጡት ሚኒስትር ከስልጣን ወረዱ

ሰንደቅ ባለፈው ረቡዕ ባወጣው ዘገባ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ዳውድ መሐመድ ም/ጠ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት በተደረገ ግምገማ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን አስታውቋል። ሚኒስትር ዴኤታው የተነሱት በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ያለውን ብልሹ አሰራር እና ሙስና አስመልክቶ ከሳምንታት በፊት ዜናውን በዘገበው ጋዜጣ ላይ በግልጽ አስተያየት በመስጠታቸው ነው።

አቶ ዳውድ ህዳር 26 ቀን 2005 ዓ.ም የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር አቶ አሚን አብዱልቃድር እና ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ታደለች ዳለቾ ግንባር በመፍጠር በመ/ቤቱ ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራር እንዲሰፍን አድርገዋል በማለት ቅሬታቸውን ይፋ አድርገው ነበር። ከዚህም በተጨማሪ አለ ያሉትን አሳሳቢ ችግር ለከፍተኛ ሃላፊዎች ቢያቀርቡም መፍትሄ አለማግኘታቸውን አመልክተዋል። ይሀንኑ አስተያየታቸውን ተከትሎ በተደረገ ግምገማ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል። የሚኒስትር ዴኤታው ባልተጠበቀ ሁኔታ መነሳት ሌሎች ሙስናን ደፍረው እንዳይዋጉ ፍርሀትን ያነግሳል የሚል አስተያየት ተሰንዝሯል። መንግስት ሙስናን ለመዋጋት ቆርጦ መነሳቱን በተደጋጋሚ እየገለጸ ባለበት ሁኔታ ይህ መከናወኑ አስገራሚ እንደሆነም ተመልክቷል።

የኢትዮጵያዉን ሠራተኞች እሮሮ በሳዑዲ

በኮንትራት ሠራተኝነት ወደአረብ ሀገሮች የሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን የሚደርስባቸዉ በደል ከጊዜ ወደጊዜ መባባሱ ይሰማል። በቅርቡ ስዑዲ አረቢያ ዉስጥ ህይወታቸዉን ያጡና የአካል ጉዳት የደረሰባቸዉ እህቶች ጉዳይ የችግሩን አስከፊነት ያመለክታል።

ባሳለፍነዉ አንድ ዓመት ብቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉን ከስራ ጋር በተያያዘና በአሰሪዎች በሚደርስባቸዉ ጥቃት ከአካል መጉደል እስከህልፈተ ህይወት ለሚያደርስ ከፍተኛ አደጋ እንደተጋለጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ነብዩ ሲራክ ከጄዳ የላከው ዘገባ እንደሚያስረዳዉ ሁለት ኢትዮጵያዉያን የኮንትራት ሰራተኞች በአሰሪያቸዉ ጥቃት እንደተፈጸመባቸዉ ታዋቂ የሳዉዲ ጋዜጦች ሳይቀሩ በዝርዝር ዘግበዉታል። ግለሰቡ በስለት በሰነዘረዉ ጥቃት የአንዲቱን ህይወት ቀጥፏል፤ ሌላዋን ለጉዳት ዳርጓል ሲል የጀርመን ሬዲዮ ዘግቧል።

የመናገር ነፃነት ሽልማት ለኢትዮጵያውያን

አራት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ሄልማን ሃሜት የተባለው የአለም ዓቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሂዩመን ራይትስ ዋች ሽልማት ተሰጣቸው ። በእስራት ላይ ያሉት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ ውብሸት ታዮ እና ርዕዮት አለሙ እንዲሁም ከሃገር የተሰደደው ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ድርጅቱ ዘንድሮ ይህን ሽልማት ከሰጣቸው 41 ፀሃፊዎች መካከል ይገኙበታል።

የሸላሚው የአለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ የሂዩመን ራይትስ ዋች የአፍሪቃ ጉዳዮች ተመራማሪ ላቲሻ ቤደ እንዳሉት የሄልማን ሃሜት ሽልማት የሚሰጠው በየሃገሩ የመናገር ነፃነትን በማራመድ በግል ጥረት ላደረጉና ተምሳሌት ለሆኑ ፀሃፊዎች ነው። ሽልማቱም እንደ ተሸላሚው የሚለያይ የገንዘብ ስጦታን ያካትታል። በየአመቱ የሚበረከትው ይህ ሽልማት ዘንድሮ በአለም ዙሪያ ለሚገኙ 41 ፀሃፍት ተሰጥቷል። ድርጅቱ እነዚህን ጋዜጠኞች የሸለመበትን ምክንያት ላቲሻ ቤደ ለዶቼቬለ ተናግረዋል። «ሽልማቱ የተሰጣቸው በኢትዮጵያ የነፃ ጋዜጠኞችን እጣ ፈንታ አጉልቶ ለማሳየት ነው። 4ቱ ግለሰቦች በግልፅ እንደሚታወቀው የመገናኛ ብዙሃን ነፃነት እጅግ በተገደበበት ሃገር የመናገር ነፃነትን በማራመድ በግላቸው ብዙ ስቃይ ደርሶባቸዋል። ከዚህ በተጨማሪም በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ገፅታም አጉልቶ ለማሳየትም» መሆኑን የጀርመን ሬዲዮ ቅንብር ያስረዳል።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 24, 2012 10:36 pm at 10:36 pm

    DO THEY KNOW IT IS CHRISTMAS – journalists, politicians, religious leaders and even innocent civilians are languishing in woyane fascists torture chamber. It is really sad the home grown fascists who claimed to liberate Tigrai used their power for terrorizing and looting. How long can one rule by cheating, looting and terrorizing?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule